Mizan Media and Communication - MMC

Mizan Media and Communication - MMC ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን የማህበረሰባችንን የዕለት ተዕለት ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አስተማማኝ መረጃዎችን የሚያቀርብ ገለልተኛ የሚዲያ ተቋም ነው።
(2)

በሚዛን አማን ከተማ የስማርት ሲቲ የፕላን ጥናት ላይ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነውየሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ዘመናዊና ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችላትን የስማርት ሲ...
20/08/2026

በሚዛን አማን ከተማ የስማርት ሲቲ የፕላን ጥናት ላይ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ዘመናዊና ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችላትን የስማርት ሲቲ የፕላን ጥናት ስራ አስመልካች ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የከተማዋ ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊን ጨምሮ የዞን፣ የከተማና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በመድረኩ ላይ የሚዛን አማን ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊ፤ ስማርት ሲቲ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎችን ህይወት ቀላል፣ ጤናማና ቀልጣፋ የሚያደርግ ዘላቂ የልማት ስልት መሆኑን ገልጸዋል።

ከተማዋ እያሳየች የሚገኘውን ፈጣን የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ታሳቢ በማድረግ በጋቸብ፣ እድገትና አማን ስትራቴጂካዊ አካባቢዎች ላይ ሰፊና ጥልቅ የስማርት ሲቲ ጥናት መካሄዱን ከንቲባው ጠቁመዋል።

አያይዘውም በመልእክታቸውም፤ የከተማዋን ሀብት በብቃት ለመጠቀም፣ የኃይል ፍጆታን ለመቀነስና ቢሮክራሲን በማቃለል ፈጣን የህዝብ አገልግሎት ለመስጠት የጥናቱን ውጤት ወደ ተግባር መቀየር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለእቅዱ ስኬታማነትም የሁሉም ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎና ባለቤትነት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

በመድረኩ በምን ያምር አማካሪ ድርጅት በኩል የተሰሩ የጥናት ውጤቶችና ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች በድርጅቱ ስራ አስኪያጅ በኢንጂነር ፋናዬ ታደሰና በዘርፉ ባለሙያዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።

ተማሪ ሱመያ ነሰሩ የ8ኛ ክፍል ፈተና ባስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የእንኳን ደስ አለሽ መልእክት አስተላለፈ።በቤንች ሸኮ ዞን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍ...
19/08/2026

ተማሪ ሱመያ ነሰሩ የ8ኛ ክፍል ፈተና ባስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የእንኳን ደስ አለሽ መልእክት አስተላለፈ።

በቤንች ሸኮ ዞን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበችው ተማሪ ሱመያ ነሰሩ ሙሳ የቤንች ሸኮ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የእንኳን ደስ አለሽ መልእክት አስተላልፏል።

ተማሪ ሱመያ በ2018 የትምህርት ዘመን በዞኑ ከተፈተኑ አጠቃላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል የላቀ የትምህርት አፈጻጸም በማሳየት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ችላለች። በዚህም መሠረትም ጠቅላላ ውጤት 569.17 ሲሆን መካከለኛ ውጤት: 94.86% በፐርሰንታይል 99.98% በማስመዝገብ በዞኑ ቀዳሚ ከሆኑ ተማሪዎች አንዷ ለመሆን በቅታለች።

የቤንች ሸኮ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ተማሪ ሱመያ ነሰሩ ላስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት የተሰማውን ደስታ ገልጾ፤ ለቀጣይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷም ስኬትን ተመኝቷል።

ምክር ቤቱ ሌሎች ተማሪዎችም ከተማሪ ሱመያ አርዓያነት ያለው ስኬት በመቅሰም፣ ትምህርታቸው ላይ በትኩረትና በትጋት በማንበብ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ጥሪውን አስተላልፏል። መረጃው የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ነው።

19/08/2026

አዲስ አበባ የፌዴራል መንግስት ተጠሪ እንድትሆን ከስምምነት ሲደረስ፣ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ትሁን" ለሚለው ሁለት አማራጮች ቀርበው የአዘጋጅ ቡድኑ ቃለጉባዔ ተነበበ።35ኛ ቀኑን ባስቆጠረው...
19/08/2026

አዲስ አበባ የፌዴራል መንግስት ተጠሪ እንድትሆን ከስምምነት ሲደረስ፣ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ትሁን" ለሚለው ሁለት አማራጮች ቀርበው የአዘጋጅ ቡድኑ ቃለጉባዔ ተነበበ።

35ኛ ቀኑን ባስቆጠረው ዋናው የምክክር ጉባዔ በ10፣ 50፣ 250፣ 500 ሰዎች በያዙ ቡድኖች ተመካካሪዎች ሲመክሩባቸው የነበሩ ምክረ ሀሳቦች 500 ሰዎች ከያዘው ቡድን ከደረሱ በኋላ ቡድኑ ተመካክሮባቸው ከስምንቱም ቡድኖች ለተመረጡ 120 አባላት ላሉት ምክረ ሀሳቦች አዘጋጅ ቡድን መቅረባቸው ይታወሳል።

120 አባላት ያሉት ምክረ ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን ከባለ 500ው ቡድን የተቀበላቸውን የተመካካሪዎች ምክረ ሀሳቦች ካጣጣመ፣ የሚያቃረኑ ነገሮች እንዳይኖሩ ከተጠነቀቀ፣ ወደ አንድ ወጥ ምክረ ሀሳብ እንዲመጡ ካደረገ በኋላ 500 ሰዎች ለያዙ ለእያንዳንዱ 8 ቡድኖች አቅርቦ ከተመካካሪዎች ሰሞኑን ግብዓት ሰብስቧል።

በዛሬው መርሃ ግብር ደግሞ፣ 120 አባላት ያሉት ቡድን ያዘጋጀውና ግብዓት የሰበሰበበት ቃለጉባዔ ለእያንዳንዱ 500 ሰዎች ለያዙ 8 ቡድኖች ተነቧል። እያንዳንዱ 8 ቡድኖች ሲመክሩ የቆዩት በአንድ፣ አንድ አጀንዳ ሲሆን፣ ዛሬ በተነበባቸው ቃለጉባዔ የተመካከሩበትን አጀንዳ ጨምሮ ያልተመካከሩባቸው የ7ቱ አጀንዳ ምክረ ሀሳቦችም በአዘጋጅ ቡድኑ ተዘጋጅተው ቀርበውላቸዋል።

አከራካሪ ሆኖ በቆየው የአዲስ አበባ ጉዳይ ዛሬ በተነበበው ቃለጉባዔ ምን ተባለ ?

ስምንቱ ዝርዝር ሀሳቦች ከያዙ ዋና አጀንዳዎች መካከል በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፥ የአዲስ አበባ እና የድሬዴዋ ጉዳይ አንዱ ነው። በዚህም በተለይ የአዲስ አበባ ህጋዊ ጉዳይ በተመካካሪዎች በኩል ብርቱ ክርክር፣ ጭቅጭቅ፣ ምክክር ሲያስተናግድ ሰንብቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ከምክክሩ ተሳታፊዎች እንደተረዳው፣ አዲስ አበባ ተጠሪነቷ የፌዴራል ከተማ ይሁን የሚለው ጉዳይ ተመካካሪዎችን ያስማማ በሚል በቃለባዔው ተቀምጧል።

ልዩ ጥቅም የሚለው ደግሞ "የጋራ ጥቅም" በሚለው ተተክቶ አስማምቶ ቀርቧል። ከተማዋ የፌዴራል ከተማ መሆኗ እንዳ ሆኖ፣ ሌሎች ከተሞች ይጨመሩ የሚል ምክረ ሀሳብም ተቀምጧል።

የኦሮሚያ ክልልን የወከሉ ተሳታፊዎች "አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ እንድትሆን ሕገመግስቱ እውቅና ይስጥ" ሲሉ፣ ሌሎች ተመካካሪዎች ደግሞ፣ "አዲስ አበባ የብሔር ብሔረሰቦች ናት። ለአንድ ክልል ብቻ አትሰጥም" በሚል ተከራክረው ሀሳቡ በልዩነት ተይዞ እንደነበር ይታወቃል።

ዛሬ በተነበበው የስምንቱንም አጀንዳ ምክረ ሀሳቦች አጣጥሞ የቀረበው ቃለጉባዔ፥ "አዲስ አበባ ከተማ የኦሮሚያ ክልል ዋና መቀመጫ" እንድትሆን በቀረበው ምክረ ሀሳብ ሁለት አማራጭ ምክረ ሀሳቦች እንደተቀመጡለት ተገልጿል።

አንደኛው፥ "ሁሉም ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን መምረጥ ይችላሉ" የሚለው በሕግ ይደንገግ የሚል ነው።

ሁለተኛው፥ በአንቀጽ 49/5 አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በከተማዋና በክልሉ መካከል ያለው ግንኙነት በሕግ ይደንገግ የሚል መሆኑ ተመልክቷል።

የድሬዳዋ ከተማን ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ፣ ተጠሪነቷ ለፌዴራል መንግስቱ እንዲሆን፣ ሕገመንግስቱ እውቅና በሰጠው ቻርተው እንድትተዳደር በቃለጉባዔው ተነቧል።

ዛሬ የተነበበው የተነበበው ቃለ ጉባዔ ነገ በ4ሺሕ ጉባያኞች ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት ውጤታማነቱን እያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሠራርን በቴክኖሎ...
19/08/2026

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት ውጤታማነቱን እያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሠራርን በቴክኖሎጂ በመደገፍና ግለሰባዊ ንክኪዎችን በመቀነስ ለዜጎች የተቀላጠፈና ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን የክልሉ የመሶብ አንድ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አስራት አደሮ ተናግረዋል።

ከሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጋር ቆይታ ያደረጉት ሥራ አስፈጻሚው አቶ አስራት እንደገለጹት፤ 44 ተቋማት 206 የአገልግሎት ዓይነቶችን ወደ አሠራሩ ያስገቡ ሲሆን፣ እስካሁንም ከ44 ሺህ በላይ ተገልጋዮች በአካልና በኦንላይን በክልል ደረጃ አገልግሎት ማግኘት ችለዋል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ 9 ሺህ 535 የሚሆኑት አገልግሎቱን ያገኙት በኦንላይን አማካኝነት እንደሆነ ጠቅሰዋለ።

በክልል ማዕከል የክልል መሶብ አገልግሎት ሲጀመር 9 ተቋማት 28 የአገልግሎት ዓይነቶችን ይሰጡ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ የተቋማቱን ቁጥር ወደ 10 እንዲሁም የአገልግሎቶቹን ዓይነት ወደ 50 ማሳደግ ተችሏል። ከተሰጡ 6 ሺህ 211 አስተያየቶች በመነሳትም የ99.4 በመቶ በላይ የአገልግሎት እርካታ መመዝገቡን አቶ አስራት አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅት 5 ዞኖች ግንባታቸውን አጠናቀው ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን፤ 15 ከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች ደግሞ የሥራ እድገታቸውን አጠናቀው በመስከረም ወር ተመርቀው አገልግሎት እንደሚጀምሩ ይጠበቃል። በእነዚህ ማዕከላትም 30 ተቋማት አገልግሎት እንደሚሰጡ አመላክተዋል።

በ2019 ዓ.ም 56 የመሶብ ማዕከላት አገልግሎቶችን ለማቅረብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አስራት፤ እንደ ክልል 1፣ በዞን 6፣ በከተማ አስተዳደር 20 እና በወረዳ 41 በድምሩ 68 ማዕከላት የሚጠበቁ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 6ቱ ወደ ሥራ መግባታቸውንና ቀሪዎቹ 56 ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረግ አብራርተዋል።

የማዕከሉ ዋና ዓላማ የተማከለ የመሶብ አገልግሎት መስጠት፣ በባስ ተንቀሳቃሽ አገልግሎትን ማቅረብ እና ህብረተሰቡ ባሉበት ሆኖ በስልክ አገልግሎት የሚያገኝበትን «ዩኒፋይድ» አሠራር መተግበር እንደሆነ ገልፀዋል።

አገልግሎቱ የገቢዎች፣ ንግድ፣ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ፣ መሬት ልማት፣ ኢንተርፕራይዝ፣ ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ በርካታ ተቋማትን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም ለአቅመ ደካሞችና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የዜጎችን ጊዜና ሀብት ከመቆጠቡም በላይ እንግልትን ማስቀረቱ ጠቅሰዋል።

ይህ ስራ የመደመር መንግሥት ፍልስፍናን መሠረት ያደረገ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በመደመር መጽሐፍ ገጽ 130 ላይ እንደሰፈረው የመንግሥት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚያዩና አገልጋይነትን የተላበሱ እንዲሆኑ ከሚጠበቅበት ዕሳቤ ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።

አሠራሩ ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት እንዲሸጋገሩ በማድረግ፣ አገራዊ የብልፅግና ጉዞን የሚያፋጥንና የዜጎችን አመኔታ የሚያጠናክር እንደሆነ አመላክተዋል።

የማዕከላዊ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ምስረታ 3ኛ ዓመታቸውን አስመልክተው ፤ ርዕሰ መስተዳድሮቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻ...
19/08/2026

የማዕከላዊ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ምስረታ 3ኛ ዓመታቸውን አስመልክተው ፤ ርዕሰ መስተዳድሮቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የክልሎቻቸውን ምስረታ 3ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለመላው የክልሎቹ ሕዝቦች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ርዕሰ መስተዳድሮቹ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፤ ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በሕዝቦች ይሁንታና ሕገ-መንግስታዊ ሂደትን ተከተለው በአዲስ መልክ የተደራጁት ሁለቱ ክልሎች፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት የሕዝቦችን የመዋቅርና የልማት ጥያቄዎች በመመለስ ዘርፈ-ብዙ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልፀው የክልሉ የኢኮኖሚ ዕድገት በ2016 በጀት ዓመት ከነበረበት 7 በመቶ በ2018 ወደ 10.2 በመቶ አድጓል። የክልሉ ዓመታዊ በጀትም በ2016 በጀት ዓመት ከነበረበት 25.4 ቢሊዮን ብር በ2019 በጀት ዓመት ወደ 67 ቢሊዮን ብር ገደማ ከፍ ብሏል።

የውስጥ ገቢ አሰባሰብ በ2016 ከነበረበት 10.8 ቢሊዮን ብር በ2018 ወደ 26.6 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ ከቀድሞው ክልል ከተላለፉት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ እዳዎች ውስጥ ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ መከፈል ተችሏል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ።

በ2018 በጀት ዓመት ብቻ ለ464 ሺህ በሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሰባቱም የክላስተር ማዕከላት የቢሮ ህንጻዎች ግንባታና በሆሳዕና ከተማ የርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት እና የቤተ-መንግስት ግንባታዎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋልም ብለዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች መካከል አሳታፊ የፖለቲካ ባህልና ነባር ሀገር በቀል የሰላም ግንባታ ተቋማትን በመጠቀም ክልሉን ከግጭት አዙሪት በማውጣት አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ተደርጓል።

የሕዝቡን አቅም በማስተባበር በሰው ተኮር ተግባራት፣ በኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በአረንጓዴ ልማት ኢንሼቲቮች አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

ሁለቱም ርዕሰ መስተዳድሮች ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠል፣ የሕዝቦችን አዳጊ ፍላጎቶች በመመለስ፣ የኑሮ ውድነትን በመቀነስ እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን በመደገፍ ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በጋራና በትብብር መስራት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

በቤሮ ወረዳ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ የአረቄ ምርት በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲወገድ ተደረገበምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ በገበያ ግምቱ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ህገ...
17/08/2026

በቤሮ ወረዳ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ የአረቄ ምርት በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲወገድ ተደረገ

በምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ በገበያ ግምቱ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ህገ-ወጥ የአረቄ ምርት በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲደፋ እና እንዲወገድ መደረጉ ተገለጸ።

የወረዳው ፖሊስ ባወጣው መረጃ፤ የህብረተሰቡን ጤና እንዲሁም የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ህገ-ወጥ የምርት እንቅስቃሴዎችንና ዝውውሮችን ለመግታት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻና የክትትል ሥራ ምርቱ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

ህገ-ወጥ ምርቱ እንዲደፋ እና እንዲወገድ በተደረገበት ወቅትም የወረዳው ፖሊስ መርማሪዎች፣ የወረዳው አቃቤ ህግ፣ የቀበሌ ሥራ አስኪያጅ፣ የከተማዋ ነዋሪዎችና ታዛቢዎች በተገኙበት ግልጽነትና ህጋዊ አሰራርን በተከተለ መልኩ በይፋ እንዲወገድ ተደርጓል።

የወረዳው ሳጅን ጌታሁን ክፍሌ እንደገለጹት፤ ህገ-ወጥ አረቄ ማዘጋጀትና ማሰራጨት በማህበረሰቡ ጤና ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ በወረዳው የወንጀል ድርጊቶች እንዲበራከቱና በህጋዊ የንግድ ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ነው።

ሳጅን ጌታሁን አክለውም መሰል ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን የመቆጣጠር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፤ ህብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት እና ከጸጥታ አካላት ጋር የሚያደርገውን አጋርነት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በቤንች ሸኮ ዞን በበጀት ዓመቱ ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ3.4 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለጸበቤንች ሸኮ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ3.4 ቢሊየን...
17/08/2026

በቤንች ሸኮ ዞን በበጀት ዓመቱ ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ3.4 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለጸ

በቤንች ሸኮ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ3.4 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለጸ።

ይህን የገለጹት እየተካሄደ በሚገኘው የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የፈጻሚ ተቋማትን የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ናቸው።

ዋና አስተዳዳሪው በገቢ ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ዙሪያ በሰጡት ማብራሪያ፤ በበጀት ዓመቱ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ 3.7 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 3.4 ቢሊየን ብር ገደማ ወይም የዕቅዱን 90.87 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

በዚህም በመደበኛ ገቢ 3 ቢሊየን 299 ሚሊየን 558 ሺህ 491 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 3 ቢሊየን 085 ሚሊየን 855 ሺህ 883 ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል። ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ደግሞ 479 ሚሊየን 060 ሺህ 991 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 347 ሚሊየን 611 ሺህ 553 ብር መሰብሰቡን አስረድተዋል።

አቶ ሀብታሙ አክለውም በበጀት ዓመቱ የተሰበሰበው አጠቃላይ ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ1 ቢሊየን 401 ሚሊየን 597 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለው አመላክተዋል።

በቤንች ሸኮ ዞን በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ከ111 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተይዞ 16.9 ሚሊየን ብር የመንግስት ገቢ ሆነበቤንች ሸኮ ዞን በበጀት ዓመቱ 38 ሺህ 533 ሊትር ቤን...
17/08/2026

በቤንች ሸኮ ዞን በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ከ111 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተይዞ 16.9 ሚሊየን ብር የመንግስት ገቢ ሆነ

በቤንች ሸኮ ዞን በበጀት ዓመቱ 38 ሺህ 533 ሊትር ቤንዚን እና 73 ሺህ 116 ሊትር ናፍጣ በድምሩ 111 ሺህ 649 ሊትር ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ ተይዞ፣ ከሽያጩ የተገኘ 16.9 ሚሊየን ብር የመንግስት ገቢ መደረጉ ተገለጸ።

ይህን የገለጹት እየተካሄደ በሚገኘው የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት የፈጻሚ ተቋማትን አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ናቸው።

ዋና አስተዳዳሪው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ አፈጻጸም ዙሪያ በሰጡት ማብራሪያ፤ በበጀት ዓመቱ የነዳጅ ስርጭትና ቁጥጥር ሥራን ውጤታማ ለማድረግ ከ12 ዙር በላይ ክትትል መደረጉን ጠቁመዋል።

በዚህም በ15 የነዳጅ ማደያዎች 3 ሚሊየን 976 ሺህ 436 ሊትር ቤንዚን እንዲሁም 15 ሚሊየን 601 ሺህ 052 ሊትር ናፍጣ—በድምሩ ከ19 ሚሊየን ሊትር በላይ ነዳጅ—ለህብረተሰቡ ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።

አስተዳዳሪው አክለውም በዞኑ የነዳጅ እጥረትና ህገ-ወጥ ግብይትን ለመግታት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚህም ሶር ኩጃ፣ ሀበሻ ጌንጃ እና ሀበሻ ሚዛን አማን የተባሉ ሶስት አዳዲስ የነዳጅ ማደያዎች አስፈላጊው የልኬታ (ካሌብሬሽን) ሥራ ተሰርቶላቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል።

የምሽት ህገ-ወጥ ግብይትን ለመግታትም የነዳጅ መጠኑ ጠዋት ተለክቶ አገልግሎት እንዲጀምር፣ ማታ ደግሞ ተለክቶ እንዲዘጋ በማድረግ ጥብቅ ቁጥጥር ሲደረግቆይቷል።

በተጨማሪም ዕለታዊ የነዳጅ መረጃዎችን በቀን ሁለቴ በቴሌግራም እና በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች ለህዝብና ለኃላፊዎች በማሰራጨት ግልጽነት ለመፍጠር የተሰራ ሲሆን፤ ለመኪና 750፣ ለሞተር 261 እና ለባጃጅ 785 በድምሩ 1 ሺህ 796 ኩፖኖችን በመስጠት ስርጭቱን ፍትሃዊ ማድረግ ተችሏል።

በሌላ በኩል፣ በዞኑ የገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥ በተደረገ ቁጥጥር ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ፣ ምርት የደበቁ፣ ባልታደሰና ያለ ንግድ ፈቃድ ሲሰሩ የተገኙ እንዲሁም ከደረጃ በታች የሆኑ ምርቶችን ሲሸጡ የነበሩ የንግድ ድርጅቶች መታሸጋቸውን አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል። በእነዚህ አካላት ላይም ከ2.34 ሚሊየን ብር በላይ አስተዳደራዊ የገንዘብ የተቀጣ መሆኑን አስረድተዋል።

ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን ከተማ እያካሄደ ነው።የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ጉባኤ በዞኑ ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ  እየተካሄደ ይገኛል።...
17/08/2026

ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን ከተማ እያካሄደ ነው።

የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ጉባኤ በዞኑ ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል።

የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ ጌዲዮን ኮስታብ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ ከመሆናቸው ባሻገር ለህዝቡ ሰላም ፣ ልማትና ዕድገት ቁልፍ ተቋማት ናቸው ብለዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ጌዲዮን ኮስታብ ጉባኤውን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ምክር ቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ ከመሆናቸው ባሻገር ለህዝቡ ሰላም ፣ ልማትና ዕድገት ቁልፍ ተቋማት ናቸው ብለዋል።

ባለፉት አመታት በዞኑ በሰላም ፣ በልማት ፣ በዲሞክራሲ ግንባታና በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ውጤቶች ተመዝግበዋል ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው በተዋረድ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመሰረተ ልማትና መሰል የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በፍጥነት ምላሽ እንዲያገኙም ምክር ቤቶች በትኩረት ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመዋል።

ጉባኤው ቀጥሎ እየተካሄደ ሲሆን የዞኑ ምክር ቤት የ2018 አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ በምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ በተከበሩ በአቶ ተካልኝ ሺፈራው እየቀረበ ይገኛል። ቤሸቴ

Address

Mizan Aman
Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mizan Media and Communication - MMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share