06/11/2025
*“የማንም እርዳታ ሳያስፈልግን መክተን አጥቅተን ጠላትን የማጥፋት ብቃት ላይ እንገኛለን” ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ*‼️
📌ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እውነትን ይዘን ህግን ተከትለን በጋራ ሃሳብ አብረን መኖር እንፈልጋልን”
አይ እኛ ህግን አንፈልግም፣አንከተልም ፣ሰላምን እና በጋራ አብር መስራት አንፈልግም በማለት ሌሎች ሀይሎችን በመተማመን በጉልበት፣በሃይል እና መሳሪያ በማወዛወዝ ማምጣት የምትፈልጉት ነገር ካለ እኛ ወልቃት ላይ ነን ብሏል
እኛ የወልቃይት ዘቦች እንደሌሎች በትንሽ ሳንቲም እና በህወሃት ፕሮፖጋንዳ ተታለን የአማራን ህዝብ የምንሸጥ አይደለንም የሚለው ኮሎኔል ደመቀ የተከዜ ዘብ ለሁሉም ነገር ዝግጁ ነው ብሏል ።
የተከዜ ዘብ የሕዝብ ዘብ ነው።ከህወሃት የአፋር ክልል ትንኮሳ ጋር ተያይዞ ወደ ወልቃይትም እንደሚመጣ እናውቃለን ለዚህ ደሞ የአማራ ታጋይ ነን እያሉ ለህወሃት የተገዙ አሉ እኛ ግን የህዝብን መብት ለማስጠበቅ ከበቂ በላይ ተዘጋጅተናል ብሏል።