Adugna Buba Official Media

Adugna Buba Official Media Gospel

01/08/2023

መርዶክዮስ በንጉሱ በር ላይ ተቀምጦ እግዚአብሔር ያዘዘለትን እና ያዘጋጀለትን ቀን ይጠባበቅ ነበር እግዚአብሔርም በቀጠረው ጊዜና ሰዓት ለመርዶክዮስ መጣለት መርዶክዮስንም ከፍከፍ አደረገው የመርዶክዮስን ውድቀትና ሞት የሚጠባበቁ የመርዶክዮስ እና የአይሁድ ጠላቶች የመርዶክስን እና የአይሁድን ውድቀት እና ሞት አላዩም በተቃራኒው የእነሱን ከፍታ ነው ያዩት እግዚአብሔር ግን ለምንድነው መርዶክዩስን ከፍከፍ ያደረገው? እግዚአብሔር ሁለም ቅን ፈራጅ ነው የተዋረዱትን ማንሳት ልምዱ ነው ።

አስቴር 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ሐማም ገባ፤ ንጉሡም፦ ንጉሡ ሊያከብረው ለሚወድደው ሰው ምን ይደረግለታል? አለው። ሐማም በልቡ፦ ንጉሡ ከእኔ ይልቅ ማንን ያከብር ዘንድ ይወድዳል? አለ።
⁷ ሐማም ንጉሡን እንዲህ አለው፦ ንጉሡ ያከብረው ዘንድ ለሚወድደው ሰው እንዲህ ይደረግ፤
⁸ ንጉሡ የለበሰው የክብር ልብስ፥ ንጉሡም የተቀመጠበት ፈረስ ይምጣለት፥ የንጉሡም ዘውድ በራሱ ላይ ይደረግ፤
⁹ ልብሱንና ፈረሱንም ከንጉሡ አዛውንት በዋነኛው እጅ ያስረክቡት፤ ንጉሡም ያከብረው ዘንድ የሚወድደውን ሰው ያልብሱት በፈረሱም ላይ አስቀምጠውት በከተማይቱ አደባባይ ያሳልፉት፤ በፊቱም፦ ንጉሡ ያከብረው ዘንድ ለሚወድደው ሰው እንዲህ ይደረግለታል ተብሎ አዋጅ ይነገር።
¹⁰ ንጉሡም ሐማን፦ ፍጠን፥ እንደ ተናገርኸውም ልብሱንና ፈረሱን ውሰድ፤ በንጉሡም በር ለሚቀመጠው አይሁዳዊ ለመርዶክዮስ እንዲሁ አድርግለት፤ ከተናገርኸውም ሁሉ ምንም አይቅር አለው።

ጠላቶቻቹ ሞታቹን እና ውድቀታቹን የሚጠባበቁ የናንተን ክብር እና ከፍታ ሳያዩ አይሞቱም።
ሐማ የመርዶክዮስን ክብር እና ከፍታ በአይኑ ካዬ በኋላ ለመርዶክዮስ በዘጋጀው ግንድ ላይ ተሰቅሎ ሞተ።

አስቴር 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ንጉሡም አርጤክስስ ንግሥቲቱን አስቴርን፦ ይህን ያደርግ ዘንድ በልቡ የደፈረ ማን ነው? እርሱስ ወዴት ነው? ብሎ ተናገራት።
⁶ አስቴርም፦ ያ ጠላትና ባለጋራ ሰው ክፉው ሐማ ነው አለች። ሐማም በንጉሡና በንግሥቲቱ ፊት ደነገጠ።
⁷ ንጉሡም ተቈጥቶ የወይን ጠጅ ከመጠጣቱ ተነሣ፥ ወደ ንጉሡም ቤት አታክልት ውስጥ ሄደ። ሐማም ከንጉሡ ዘንድ ክፉ ነገር እንደ ታሰበበት አይቶአልና ከንግሥቲቱ ከአስቴር ሕይወቱን ይለምን ዘንድ ቆመ።
⁸ ንጉሡም ከቤቱ አታክልት ወደ ወይን ጠጁ ግብዣ ስፍራ ተመለሰ፤ ሐማም አስቴር ባለችበት አልጋ ላይ ወድቆ ነበር። ንጉሡም፦ ደግሞ በቤቴ በእኔ ፊት ንግሥቲቱን ይጋፋታልን? አለ። ይህም ቃል ከንጉሡ አፍ በወጣ ጊዜ የሐማን ፊት ሸፈኑት።
⁹ በንጉሡም ፊት ካሉት ጃንደረቦች አንዱ ሐርቦና፦ እነሆ ሐማ ለንጉሡ በጎ ለተናገረው ለመርዶክዮስ ያሠራው ርዝመቱ አምሳ ክንድ የሆነው ግንድ በሐማ ቤት ተተክሎአል አለ። ንጉሡም፦ በእርሱ ላይ ስቀሉት አለ።
¹⁰ ሐማንም ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው ግንድ ላይ ሰቀሉት፤ በዚያም ጊዜ የንጉሡ ቍጣ በረደ።

ኢየሱስ ጌታ ነው!!
04/10/2022

ኢየሱስ ጌታ ነው!!

እርሱም በኛ አላፈረም
ኢየሱስ ብቻውን ጌታ ነው!!

እርሱም በኛ አላፈረምኢየሱስ ብቻውን ጌታ ነው!!
04/10/2022

እርሱም በኛ አላፈረም
ኢየሱስ ብቻውን ጌታ ነው!!

02/10/2022

በመከራና በችግር ጊዜ የማይለይክ እርሱ እግዚአብሔር ነው!!
መሳፍንት 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ በዖፍራ ባለችው ለአቢዔዝራዊው ለኢዮአስ በነበረችው በአድባሩ ዛፍ በታች ተቀመጠ፤ ልጁም ጌዴዎን ከምድያማውያን ለመሸሸግ በወይን መጥመቂያው ውስጥ ስንዴ ይወቃ ነበር።
¹² የእግዚአብሔርም መልአክ ለእርሱ ተገልጦ፦ አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው አለው።
¹³ ጌዴዎንም፦ ጌታዬ ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን? አባቶቻችንስ፦ እግዚአብሔር ከግብፅ አውጥቶናል ብለው ይነግሩን የነበረ ተአምራቱ ወዴት አለ? አሁን ግን እግዚአብሔር ትቶናል፥ በምድያማውያንም እጅ አሳልፎ ሰጥቶናል አለው።
¹⁴ እግዚአብሔርም ወደ እርሱ ዘወር ብሎ፦ በዚህ በጕልበትህ ሂድ፥ እስራኤልንም ከምድያም እጅ አድን፤ እነሆ፥ ልኬሃለሁ አለው።

27/05/2022

ኢየሱስ አብሮክ መኖሩን ከተረዳክ አትናወጥም (አትፈራም)
ማርቆስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ በዚያም ቀን በመሸ ጊዜ፦ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው።
³⁶ ሕዝቡንም ትተው በታንኳ እንዲያው ወሰዱት፥ ሌሎች ታንኳዎችም ከእርሱ ጋር ነበሩ።
³⁷ ብርቱ ዐውሎ ነፋስም ተነሣና ውኃ በታንኳይቱ እስኪሞላ ድረስ ማዕበሉ በታንኳይቱ ይገባ ነበር።
³⁸ እርሱም በስተኋላዋ ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበር፤ አንቅተውም፦ መምህር ሆይ፥ ስንጠፋ አይገድህምን? አሉት።
³⁹ ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም፦ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ።
⁴⁰ እንዲህ የምትፈሩ ስለ ምን ነው? እንዴትስ እምነት የላችሁም? አላቸው።
⁴¹ እጅግም ፈሩና፦ እንግዲህ ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው? ተባባሉ።

27/05/2022

If you know that Jesus is with you, you will not be afraid!!
Mark 4 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ And the same day, when the even was come, he saith unto them, Let us pass over unto the other side.
³⁶ And when they had sent away the multitude, they took him even as he was in the ship. And there were also with him other little ships.
³⁷ And there arose a great storm of wind, and the waves beat into the ship, so that it was now full.
³⁸ And he was in the hinder part of the ship, asleep on a pillow: and they awake him, and say unto him, Master, carest thou not that we perish?
³⁹ And he arose, and rebuked the wind, and said unto the sea, Peace, be still. And the wind ceased, and there was a great calm.
⁴⁰ And he said unto them, Why are ye so fearful? how is it that ye have no faith?
⁴¹ And they feared exceedingly, and said one to another, What manner of man is this, that even the wind and the sea obey him?

27/05/2022

Welcome to Adugna Buba official media

27/05/2022

If you believe jesus is Lord he will change your history

09/05/2022
09/05/2022

አስቴር 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አዳር በሚባለውም በአሥራ ሁለተኛው ወር ከወሩም በአሥራ ሦስተኛው ቀን፥ የንጉሡ ትእዛዝና አዋጅ ሊፈጸምበት በነበረው ቀን፥ የአይሁድ ጠላቶች ሊሠለጥኑባቸው በነበረው ቀን፥ አይሁድ በጠላቶቻቸው ላይ እንዲሠለጥኑ ነገሩ ተገለበጠ።
² አይሁድም ክፋታቸውን በሚሹት ሰዎች ላይ እጃቸውን ይዘረጉ ዘንድ በንጉሡ በአርጤክስስ አገሮች ሁሉ በነበሩ ከተሞቻቸው ውስጥ ተሰበሰቡ፤ እነርሱንም መፍራት በአሕዛብ ሁሉ ላይ ወድቆ ነበርና እነርሱን የሚቃወም ሰው አልነበረም።
³ መርዶክዮስን መፍራት በላያቸው ስለ ወደቀ በየአገሩ የነበሩ አዛውንትና ሹማምቶች አለቆችም፥ የንጉሡንም ሥራ የሚሠሩቱ ሁሉ አይሁድን አገዙ።
⁴ ያ ሰው መርዶክዮስ ከፍ ከፍ እያለ ስለ ሄደ በንጉሡ ቤት ታላቅ ሆኖ ነበርና፥ የመርዶክዮስም ዝና በየአገሩ ሁሉ ተሰምቶ ነበርና።

06/05/2022

Address

Wellega
Shambu
-

Telephone

+251988888888

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adugna Buba Official Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Adugna Buba Official Media:

Share