Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ

Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
ኤፌ 1: 4 we are a servant of God

የደከምንበትን "አባካኙ ልጅ" ፊልም ሊለቀቅ ነዉ!!ዘማሪት ቤተልሔም ተዘራሊቪንግ ዊትነስ አገልግሎት ከሚሰራችው ሰራዎች መካከል አንዱ የሆነውን እና ያለፉትን ረጅም ወራት የደከምንበትን "አባካ...
12/07/2025

የደከምንበትን "አባካኙ ልጅ" ፊልም ሊለቀቅ ነዉ!!
ዘማሪት ቤተልሔም ተዘራ

ሊቪንግ ዊትነስ አገልግሎት ከሚሰራችው ሰራዎች መካከል አንዱ የሆነውን እና ያለፉትን ረጅም ወራት የደከምንበትን "አባካኙ ልጅ" የተሰኘ፤ በመዝሙር የታጀበ አጭር ፊልም ወደ እናንተ ልናመጣ ጥቂት ቀናት ቀርተውናል።
በዝማሬ የታጀበው አጭር ፊልም በሉቃስ 15 ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን ከግሩም መልዕክት ጋር አንጋፋ እና አዲስ ተዋንያን ተሳትፈውበታል። በእግዚአብሔር እርዳታ የፊታችን ሐሙስ ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ እናንተ ይደርሳል።

ከዘንድሮ ተመራቂዎች መሃል !! " የክርስቶስ አንባሳደሮች" የሚል መልዕክት ያስተላለፉ ተማሪዎች። ተባረኩ
23/06/2025

ከዘንድሮ ተመራቂዎች መሃል !! " የክርስቶስ አንባሳደሮች" የሚል መልዕክት ያስተላለፉ ተማሪዎች። ተባረኩ

✍️ ሃያ አንዱ ማኅበራዊ ሕግጋት    𝐓𝐡𝐞 𝟐𝟏 𝐒𝐨𝐜𝐢𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐦𝐦𝐚𝐧𝐝𝐬    C̳R̳E̳D̳I̳T̳ ̳T̳O̳:- 𝓜𝓲𝓱𝓲𝓻𝓮𝓽  𝓓𝓮𝓫𝓮𝓫𝓮 (𝓓𝓻)❶.  #ይሰለቹሃል አስሬ አትደውል፤ ሰዎች ጋር...
19/06/2025

✍️ ሃያ አንዱ ማኅበራዊ ሕግጋት
𝐓𝐡𝐞 𝟐𝟏 𝐒𝐨𝐜𝐢𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐦𝐦𝐚𝐧𝐝𝐬
C̳R̳E̳D̳I̳T̳ ̳T̳O̳:- 𝓜𝓲𝓱𝓲𝓻𝓮𝓽 𝓓𝓮𝓫𝓮𝓫𝓮 (𝓓𝓻)

❶. #ይሰለቹሃል አስሬ አትደውል፤ ሰዎች ጋር ከሁለቴ በላይ አይደወልም። ተሰልቺ ትሆናለህ!
❷. ' #ሼም ነው' የሚከፍለው ሌላ ሰው ነው ብለህ ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ምግብና መጠጥ አትዘዝ!
❸. #አይባልም "... እንዴ እስካሁን አላገባሕም? ለምንድነው እስካሁን ያልወለድሽው? እንዴት ዲግሪሽን እስካሁን ሳትይዢና ሳትይዝ ወዘተ..." አይባልም።
4. #ክፈል አብሮህ ላለው ሰው ታክሲ ላይም ሆነ የትም ቦታ አግባብ ነው ብለህ ስታምን ቀድመህ ክፈል። ገና ለገና ይከፍላል ብለህ ከሱ ስትጠብቅ ደምህን እያሯሯጥክ ትሰቃያለህ።
5. #ነውር ነው ሰው እየበላም ይሁን በማንኛውም ሰዓት ከሰዎች ጋር ካለህ ጥርስህን አትጎርጉር፣ አፍንጫህንና ሌሎች ያልተገቡ ቦታዎችንም አትነካካ።
6. #አታቋርጥ ግዴለህም አብሮህ ያለው ሰው አውርቶ ይጨርስ። ጥልቅ እያልክ አታቋርጥ።ከባሕልም ከስልጣኔም ውጪ ነው።
7. #አታብሽቅ ሆን ብለህ የማናደድ ባሕሪ ካለህ ተው። ሰዎች ለመባል የማይወዱትን ተው።ሰዎች ብዙ የማይናገሩትና የተሸከሙት የራሳቸው ብሽቀት ስላለባቸው ለተሻለውና ለሚበረቱበት ሕይወታቸው አድናቆት ስጥ።
8. #አመሥግን ለተደረገልህ ማንኛውም ቅንጣት ነገር አመሥግን።
9. ሰዎችን በይፋ አድንቃቸው፣ መልካም ያልሆነ ነገራቸውን ግን በግል አውራቸው።
10. ቆጥብ ያልሆነ ነገር ብታይ እንኳን አፍህ በበጎ ቃላት ይቀይረው። ወፍሮ ያየኸውን ሰው ኤጭ ተዝረጠረጥክ ከማለት ተቆጠብ።
11. ሰዎች የሕክምና ቀጠሮ ሄደው መምጣታቸውን ነግረውህ ይሆናል። የውጤቱን
ምንነት ለማወቅ ግን በጥልቀት አትጠይቅ። በነገሩህ ልክ መልካሙን ተመኝላቸው። በቻልከው መጠን በመረጃና በጥቆማ አግዛቸው እንጂ ድንበር አትዝለል።
12. #ስነ- #ስርዓት ሰዎች ከስልካቸው ላይ ፎቶ እንድታይ ቢሰጡህ ከፈቀዱልህ ውጪ ሌላ ፎቶ ካላየሁ ብለህ ስልክ አትፈትሽ። ሁሉም ሰው ታልፎ እንዲገባበት የማይፈልገው የራሱ አጥር አለው።
13. #ክብር ለሁሉም ከላይ ጫፍ ላለ የሥራ ኃላፊና ከታች ዝቅ ባለ ስራ ላይ ለሚገኘው ሰው እኩል ክብር ስጥ። እንደውም ከላይ ካለው ይልቅ ታች ላለው ሰው የሰጠኸው ክብር ብዙ እውቅና አለው። ለንቀትህ ግን የማንንም አድናቆትና ጭብጨባ አታገኝም።
14. ሰዎች በቀጥታ ላንተ እያወሩ ስልክህን የምትነካካ ከሆነ ቀሽምነት ነው። ከሰው
ሰራሹ ይልቅ ራሱ ሰው ትልቅ ዋጋ አለው።
15. #አድብ ሰዎች ካልጠየቁህና ካልፈቀዱልህ በስተቀር በራሳቸው ሕይወትና ሥራ ጣልቃ አትግባባቸው።
16. #ተቆጠብ ከረጅም ጊዜ በኋላ ያገኘሃቸውን ሰዎች አስጨናቂ ጥያቄ አትጠይቃቸው። ሰዎች ቆይታቸውን እንዲሁም ዕድሜና ደሞዛቸውን ጨምሮ የመናገርና ያለመናገር ብቸኛ ባለመብት ራሳቸው እንደሆኑ እወቅ።
17. ከሰዎች ጋር በዓይንህ አውራ። ከማንም ጋር በመንገድ ላይ ተገናኝተህ ስታወራ መነጽርህን ከዓይንህ ማንሳት እንዳለብህ አስታውስ። ክብርም ነው!
18. #አትሳሳት በድኅነት አስተሳሰብ ሆነህ ስለሀብታሞች ምንነትና ማንነት አታውራ፤ ልጅ ሳይኖርህ ስለልጅና ልጅ ስላላቸው ሰዎች ባሕሪ አትፍረድ።
19. በስልክህ የጽሑፍ መልዕክት ሲደርስህ አንብበህ ዝም ማለት ነውር ነው።ተገቢውን ምላሽ በበጎነት ቃል መመለስን ልማድህ አድርገው።
20. የወሰድከውን ማንኛውም ቁስ ባለቤቱ ሳይጠይቅህ በፊት ቶሎ መልስ።
21. ። ሌሎች እንዲወያዩበትና እንዲተቹት ክፍት አድርገው፤ አንተም ሐሳብህም ትጎለብታላችሁ። ነገርህን ደገፉትም አልደገፉት ምንጊዜም ቢሆን ላነሳኸው ሐሳብ ጥሩ ግብዓት አይጠፋም። ልክ አልሆን ወይ እያልክ ወይም ሐሳቤ ያንስ ይሆን ወይ ብለህ አትሸማቀቅ፤ ተሸማቀህ ትቀራለህ!

ዘማሪት አስቴር አበበ👇👇👇👇👇👇👇👇".......ሰዎች ሲናገሩ ጥሩ ፀሀፊ ማለት ስለሚጽፈው ርዕስ በቂ ጥላቻ ወይም በቂ ፍቅር ያለው ሰው ነው ይላሉ።  ከጠላው ደህና አድርጎ አጥላልቶ ይጽፈዋል ...
16/06/2025

ዘማሪት አስቴር አበበ

👇👇👇👇👇👇👇👇

".......ሰዎች ሲናገሩ ጥሩ ፀሀፊ ማለት ስለሚጽፈው ርዕስ በቂ ጥላቻ ወይም በቂ ፍቅር ያለው ሰው ነው ይላሉ። ከጠላው ደህና አድርጎ አጥላልቶ ይጽፈዋል ፤ ከወደደውም ደግሞ አመስግኖ እንዲወደድ አድርጎ ይጽፈዋል። ስሜት አልባና ግድ የለሽ ከሆነ ግን በዚያ ርዕስ ጥሩ ጽሁፍ ማቅረብ አይችልም 🤔

👆🏽ይህ ሀሳብ አልፋና ኦሜጋ ከሚለው በፓድተር ዶክተር ተስፋ ወርቅነህ ከተፃፈው የዮሐንስ ራዕይ መፅሀፍ 📚ትንታኔ ከገፅ 146 📖ከመጀመሪያው አንቀፅ ሳነብ ያገኘሁት ነው። የእግዚአብሄርን ስራ በቸልተኝነት የሚሰራ እርሱ የተረገመ ይሁን የሚል የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል አንብቤአለው ወይ ተሰብኬአለው። ስላነበብኩት ወይ ስለ ሰማሁት ቃል ራሱ እርግጠኛ አለመሆኔ በፍቅር ያለማንበቤን ወይም ለብ ያልኩ አንባቢ መሆኔን ያሳብቃል። እቤቴ ተጀምረው ያላለቁ ትኩስ አንባቢ ባለመሆኔ በጅምር የቀሩ የመፅሀፍት ብዛት አፍ ቢኖራቸው ቅርስነታቸው ቀርቶ በትክክለኛ ትኩስ አንባቢያን እጅ በገቡና ለንባብ በበቁ ነበር። በራድ አንባቢ ፣ በራድ ፀሎተኛ ፣ በራድ ዘማሪ ፣ በራድ አምላኪ ፣ በሁሉም አቅጣጫ ይህን አንቀፅ ሳነብ ሎዶቅያ ሳትሆን ሌላኛዋን የዘመኔን ሎዶቅያ ( ለብ ያለችዋን ዘማሪት አስቴር አበበን ) አግኝቻታለሁ። ቃሉ ሲገለጥ ብርሀን ነውና ጨለማችንን ያሳብቅብናል። ሁሉን ከልብ ከአንጀት ማድረግ እንድንችል ጌታ ይርዳን።
መፍትሄውን ለሎዶቅያ የተፃፈውን ሙሉውን ክፍል አንብቡት"
👇🏾
“ቀዝቃዛ ወይም ትኵስ እንዳልሆንህ ሥራህን አውቃለሁ፤ ቀዝቃዛ ወይም ትኵስ ብትሆን በወደድሁ ነበር። እንግዲህ ለብ ያልህ ብቻ እንጂ ትኵስ ወይም ቀዝቃዛ ስላልሆንህ ከአፌ አውጥቼ ልተፋህ ነው።”
‭‭ራእይ‬ ‭3‬:‭15‬-‭16‬ ‭

ቸር ቆዩኝ በትኩሱ እወዳችኋለሁ❤! ዘማሪት አስቴር አበበ

   #በአሜሪካን 🇺🇸 ሀገርእስኪ እንባርካቸው🙏
15/06/2025

#በአሜሪካን 🇺🇸 ሀገር

እስኪ እንባርካቸው🙏

 "አገልግሎት የችሎታ ውጤት አይደለም" እንደተሰጠን ፀጋ መጠን እንሮጣለን እንጂ። ስናገለግል የሚበልጠንም የምንበልጠውም ሰው የለም ። አገልግሎት  ለእግዚአብሔር ክብርና ለሰው ጥቅም ለቤተክር...
14/06/2025



"አገልግሎት የችሎታ ውጤት አይደለም" እንደተሰጠን ፀጋ መጠን እንሮጣለን እንጂ። ስናገለግል የሚበልጠንም የምንበልጠውም ሰው የለም ። አገልግሎት ለእግዚአብሔር ክብርና ለሰው ጥቅም ለቤተክርስቲያን መታነፅ ነው ። ስለቻልን ሳይሆን እሱ በኛ ውስጥ ችሎ ስለተገኘ ነው የምንቀጥለው የምናካፍለው ነገር የበዛልን እኮ ከጌታ የምንቀበለው ነገር ስላለ ነው ስለዚህ ዋና ትኩረታችን ለሁሉ እንደወደደ ልዩ ልዩ ፀጋ በሚሰጠው በፀጋው ባለቤት በኢየሱስ ላይ ይሁን እግዚሐብሔር በዚ መንፈስ ይጎብኘን !!!

እግዚአብሔር ይባርክሽ!!

 #ተፈጸመየዘማሪት የምስራች ስምዖን የቀብር ስነስርዓት በትውልድ ከተማዋ አርባምንጭ ተፈጽሟል ።
04/06/2025

#ተፈጸመ
የዘማሪት የምስራች ስምዖን የቀብር ስነስርዓት በትውልድ ከተማዋ አርባምንጭ ተፈጽሟል ።

እግዚአብሔር አዋቂ ነው በስራውም ትክክል ነው። እርሱ የወደደውን ያደርጋል ማንምም ተሳስተሃል አይለውም። እግዚአብሔር ለሁሉ መፅናናትን ይላክ😭!
03/06/2025

እግዚአብሔር አዋቂ ነው በስራውም ትክክል ነው። እርሱ የወደደውን ያደርጋል ማንምም ተሳስተሃል አይለውም።
እግዚአብሔር ለሁሉ መፅናናትን ይላክ😭!

እማማ ባሎቴ ይባላሉ፤ ከባለቤታቸው ለወንጌል ከተሰው ወንጌል አርበኛ ኦሞጨ ኡኩለ ጋር ወንጌልን ይዞ ከወላይታ ወደ ጎፋ የሄዱ የመጀመሪያ ሴት ወንጌላዊት ናቸው ። ከባለቤታቸው ጋር ወንጌልን እ...
10/04/2025

እማማ ባሎቴ ይባላሉ፤ ከባለቤታቸው ለወንጌል ከተሰው ወንጌል አርበኛ ኦሞጨ ኡኩለ ጋር ወንጌልን ይዞ ከወላይታ ወደ ጎፋ የሄዱ የመጀመሪያ ሴት ወንጌላዊት ናቸው ። ከባለቤታቸው ጋር ወንጌልን እየሰበኩ እያሉ ባለቤታቸው በወንጌል ምክንያት በሰው እጅ ከተገደለ በኋላ ወደ ቤት እንዲመለሱ ተጠይቆ እንብ እንደ ባለቤቴ ለወንጌል መሞትን እመርጣለሁ በማለት ወንጌልን ያስቀጠሉ ጀግና የወንጌል አርበኛ ናቸው። እንደ ደመና ስለከበቡን ወንጌል አርበኞች ክብር ለጌታ ይሁን!
ከቃለ ሕይወት ታሪክ ማህደር የተገኘ ፎቶ፤

09/04/2025



ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አ...
28/03/2025

ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።

ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አገልጋይ ማጀብ እንደ ወንጌል አማኝ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው ከአስተምሮት ውጪ መሆኑን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል እወቁልኝ ብሏል።

የካውንስሉ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ፓስተር
ጌትነት ለማ በሰጡት መግለጫ የመንግስት አካላት ለአንድ አገልጋይ ፖሊስ አሰልፈው፣ መሳሪያ አስታጥቀው፣ አጀብ ፈጥረው ግርግር በማድረግ የሆነ አካል ወደ ከተማው የገባ የሚያስመስሉት ነገር ተገቢ እንዳልሆነ ተናግሯል።

እጀባው ትርጉም አልባ ነው ከመፅሐፍ ቅዱስ ውጪ ነው በጦር መሳሪያ መታጀብ ትርጉሙ ሌላ ነው ፍርሃት ሲኖር ነው መታጀቡ የሚመጣው፣ አገልጋዩ ከህዝብ የተበደረው ገንዘብ ሲኖር ችግር የሚፈጥርብኝ ህዝብ ይኖራል ብሎ ሲፈራ ነው በፖሊስ የሚታጀበው እንጂ ወንጌል ለመስበክ ከሆነ እጀባ አያስፈልገውም ብለዋል።

በተደጋጋሚ እንደዚህ የሚያደርጉ አገልጋዮች በፅሁፍ፣ በአካል ማስጠንቀቂያ ሰጥተናል በቅርቡ እርምጃ ወስደን መግለጫ እንሰጣለን ብለዋል።

መጋቢት 11 ቀን ነብይ ኢዩ ጩፋ ወደ ሀዋሳ ሲመጣ የመንግሥት ፖሊስ እና ሙሉ ማርሻ ባንዱ አቀባበል ማድረጉ "መንግሥት እና ሀይማኖት የተለያዩ ናቸው" የሚለውን የህገመንግስት ድንጋጌ ጥሷል በሚል አነጋጋሪ እንደነበር ይታወሳል።

 ።
28/03/2025

Address

Gibrina To Rift Valley Road
Shashemene

Telephone

+251911527330

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ:

Share

Category