Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ

Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
ኤፌ 1: 4 we are a servant of God

እማማ ባሎቴ ይባላሉ፤ ከባለቤታቸው ለወንጌል ከተሰው ወንጌል አርበኛ ኦሞጨ ኡኩለ ጋር ወንጌልን ይዞ ከወላይታ ወደ ጎፋ የሄዱ የመጀመሪያ ሴት ወንጌላዊት ናቸው ። ከባለቤታቸው ጋር ወንጌልን እ...
10/04/2025

እማማ ባሎቴ ይባላሉ፤ ከባለቤታቸው ለወንጌል ከተሰው ወንጌል አርበኛ ኦሞጨ ኡኩለ ጋር ወንጌልን ይዞ ከወላይታ ወደ ጎፋ የሄዱ የመጀመሪያ ሴት ወንጌላዊት ናቸው ። ከባለቤታቸው ጋር ወንጌልን እየሰበኩ እያሉ ባለቤታቸው በወንጌል ምክንያት በሰው እጅ ከተገደለ በኋላ ወደ ቤት እንዲመለሱ ተጠይቆ እንብ እንደ ባለቤቴ ለወንጌል መሞትን እመርጣለሁ በማለት ወንጌልን ያስቀጠሉ ጀግና የወንጌል አርበኛ ናቸው። እንደ ደመና ስለከበቡን ወንጌል አርበኞች ክብር ለጌታ ይሁን!
ከቃለ ሕይወት ታሪክ ማህደር የተገኘ ፎቶ፤

09/04/2025



ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አ...
28/03/2025

ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።

ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አገልጋይ ማጀብ እንደ ወንጌል አማኝ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው ከአስተምሮት ውጪ መሆኑን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል እወቁልኝ ብሏል።

የካውንስሉ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ፓስተር
ጌትነት ለማ በሰጡት መግለጫ የመንግስት አካላት ለአንድ አገልጋይ ፖሊስ አሰልፈው፣ መሳሪያ አስታጥቀው፣ አጀብ ፈጥረው ግርግር በማድረግ የሆነ አካል ወደ ከተማው የገባ የሚያስመስሉት ነገር ተገቢ እንዳልሆነ ተናግሯል።

እጀባው ትርጉም አልባ ነው ከመፅሐፍ ቅዱስ ውጪ ነው በጦር መሳሪያ መታጀብ ትርጉሙ ሌላ ነው ፍርሃት ሲኖር ነው መታጀቡ የሚመጣው፣ አገልጋዩ ከህዝብ የተበደረው ገንዘብ ሲኖር ችግር የሚፈጥርብኝ ህዝብ ይኖራል ብሎ ሲፈራ ነው በፖሊስ የሚታጀበው እንጂ ወንጌል ለመስበክ ከሆነ እጀባ አያስፈልገውም ብለዋል።

በተደጋጋሚ እንደዚህ የሚያደርጉ አገልጋዮች በፅሁፍ፣ በአካል ማስጠንቀቂያ ሰጥተናል በቅርቡ እርምጃ ወስደን መግለጫ እንሰጣለን ብለዋል።

መጋቢት 11 ቀን ነብይ ኢዩ ጩፋ ወደ ሀዋሳ ሲመጣ የመንግሥት ፖሊስ እና ሙሉ ማርሻ ባንዱ አቀባበል ማድረጉ "መንግሥት እና ሀይማኖት የተለያዩ ናቸው" የሚለውን የህገመንግስት ድንጋጌ ጥሷል በሚል አነጋጋሪ እንደነበር ይታወሳል።

 ።
28/03/2025

መጋቢ ተከስተ ጌትነት እግዚአብሔር ይባርክህ🙏
24/03/2025

መጋቢ ተከስተ ጌትነት እግዚአብሔር ይባርክህ🙏

.... ምክንያቴ ብዙ ነው... 🙏🙏
23/03/2025

.... ምክንያቴ ብዙ ነው... 🙏🙏

ግዮን ሆቴል 🏨 አሁን ⌚
23/03/2025

ግዮን ሆቴል 🏨 አሁን ⌚

"ቃለ ሕይወት" የሚለውን ስያሜ የሰጡ እና የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ/ያን የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት የነበሩት የወንጌል አርበኛ አባባ ባንጫ ያያ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖❖አ...
21/03/2025

"ቃለ ሕይወት" የሚለውን ስያሜ የሰጡ እና የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ/ያን የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት የነበሩት የወንጌል አርበኛ አባባ ባንጫ ያያ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
❖አባባ ባንጫ ያያ "ቃለ ሕይወት" የሚለውን ስያሜ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰጥተዋል።

❖እንዲሁም "ወልድ ያለው ሕይወት አለው" የሚለዉ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን መሪቃል በተከፈተ መጽሐፍ ላይ "logo" ወይም አርማ እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀሳብ የሰጡም ናቸው።

❖ስያሜውም የጸደቀው በዎላይታ ቀጣና ጠረጴዛ የዎላይታ ቃለ ሕይወት ዋና ጽ/ቤት ነበር።

❖አባባ ባንጫ ያያ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ዋና ፕረዚዳንትም ነበሩ።

❖አባባ ባንጫ በዎላይታ ቀጣና የጫራቄን ክፍለ ማህበርን ከ 40 ዓመታት በላይ በዋና ጸሐፊነት አገልግለዋል።

❖ከእርሳቸው በኋላ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻሉ የወንጌል አርበኛ አባቶች እነ ሾንጋንና ዳልኬ የመሳሰሉትን የሰበኩ እና የጠመቁ ነበሩ።
❖የክርስቶስን ወንጌል ከዎላይታ ውጭ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ዞረው ሰብከዋል።

❖በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ/ያን የበላይ ጠባቂ ሆኖ ሌሎች በእርሱ ስር እንዲተዳደሩ የወጣውን አዋጅ የተቃወሙ ጀግና አባት ነበሩ።

❖በዚህም ምክንያት በቀዳማዊ ኃይሌ ስላሴ ዘመነ መንግሥት ታስረዋል፣ ተገርፈዋል፣ ተንገላተዋል።

❖አባታችን አባባ ባንጫ ያያ በፖለቲካውም ዘርፍ በመሳተፍ የቀድሞ ዎላይታ አውራጃን መርተዋል።

✔አባባ ባንጫ የተወለዱት በዎላይታ ዞን ዳሞት ጋሌ ወረዳ ሞኮኒሳ ወይጌ ቀበሌ ነበር።
✔ወንጌል ወደ ዎላይታ በ1919 ዓ.ም ሲገባ እርሳቸው የ 32 ዓመት ወጣት ነበሩ።
✔አባባ ባንጫ በተወለዱ በ 137 ዓመታቸው ወደ አገለገሉት ጌታ በክብር ተሰብስበዋል።

እግዚአብሔር ለመላው ዎላይታ ቀጣና መጽናናትን ይስጥ!

👗❤🙏
15/03/2025

👗❤🙏

ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ-ክርስቲያናት ካውንስል የተሰጠ መግለጫ ።💧 ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ ወደ ምድራችን የሚመጡ የንስሐ ግቡ ሐልዕክቶች ሰለሆኑ ባላፈው ዓመት ታላቅ የአገራዊ ንስሃ ...
12/03/2025

ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ-ክርስቲያናት ካውንስል የተሰጠ መግለጫ ።

💧 ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ ወደ ምድራችን የሚመጡ የንስሐ ግቡ ሐልዕክቶች ሰለሆኑ ባላፈው ዓመት ታላቅ የአገራዊ ንስሃ ጊዜን በአደባባይ አከናውነናል። ይህንን ንስሃ መቀጠል ስለታመነበት የአገራዊ ንስሃ የሚያስተባብር ግብረ ኃይል በወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ይሁንታ ተቋቁሞ ተግባሮቹን በተሻለ መንገድ ለመወጣት በመሥራት ላይ ይገኛል።

ስለዚህ ፦

1.ከሚያዝያ 6 እስከ 11/2017 ዓ.ም ከሰኞ- ቅዳሜ በሉት የህማማቱ ሳምንት በመላው አገሪቱ ባሉ ማህበር ምዕመናን ቢቻልም በከተሞች አመቺ በሆኑ በተመረጡ አብያተክርስቲያናት በአንድነት በመሰባሰብ የኑዛዜና የንስሐ ቀናቶች እንዲሆኑ።

2. ከሚያዝያ 19 እስከ ግንቦት 17/2017 ዓ.ም ባሉት ሳምንታት ኑዛዜ ያደረግንባቸው ጉዳዮችን ወደ ፍሬ እንዲመጡ በየአጥቢያው የንስሐ አቅጣጫዎች የትምህርት እና ንስሃውን ከሕይወት ጋር የምሰናዛምድባቸው ጊዜያቶች እንዲሆኑ።

3.ግንቦት 24 ቀን 2017ዓ.ም በሁሉም ከተሞችና አካባቢዎች የማጠቃለያ የንሰሐ ጊዜ መሪዎች በየክልሎቻቸው የካውንስል እና የኀብረቶች አደረጃጀቶች እንዲያደርጉና በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ለአገር አቀፉ የማጠቃለያ የንስሐ ጊዜ ከልሉን የሚወክሉ መሪዎችን ወክለውና በክልሉ ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሥልጣን ጸልየውላቸው ወደ አዲስ አበባ እንዲልኩ።

4.ከግንቦት 25 አስከ 27 2017 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ከመላው ኢትዮጵያ ክልሎች እና ከዲያስፖራ በክልሎች ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሰልጣን በሚወከሉ መሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ማጠቃለያውን በተወከሉ መሪዎች የንስሐ ጊዜ በማድረግ የንሰሐ ማጠቃለያ እንዲሆን ታቅዷል።

በመላው ኢትዮጵያ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የወንጌላውያን አማኞች ሁሉ በዚህ በወጣው ፕሮግራም መስረት አሰተባባሪ ግብር ኃይል በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች በሚያሰራጫቸው የንስሐ አቅጣጫዎች እና የኑዛዜ የጸሎት ርዕሶች አየታገዛቸሁ የንስሐ ጊዜውን አብረን በጋራ እንድናከናውን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

“ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ጕበኞችን በቅጥርሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ ቀንና ሌሊት ከቶ ዝም አይሉም፤ እናንተ እግዚአብሔርን የምታሳስቡ፥ ኢየሩሳሌምን እስኪያጸና በምድርም ላይ ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ አትረፉ ለእርሱም ዕረፍት አትስጡ።”ትንቢተ ኢሳይያስ 62፥6-7

ልዑል አግዚአብሔር አገራችንን ኢትዮጵያን ይባርክ!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ

መጋቢት 3/2017 ዓ.ም

"ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ዝለፍና ገሥጽ ምከርም።" 2ኛ ጢሞ 4: 2
11/03/2025

"ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ዝለፍና ገሥጽ ምከርም።"
2ኛ ጢሞ 4: 2

ሻሎም ተወዳጅ ያገሬ ልጆች:: እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በከተማችን እምብርት ላይ እግዚአብሔርን በድንቅ ሁኔታ ለማመስገን ከ Holy Beat አገልግሎት ጋር በብዙ መሰጠት እየተዘጋጀን እንገኛለ...
11/03/2025

ሻሎም ተወዳጅ ያገሬ ልጆች:: እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በከተማችን እምብርት ላይ እግዚአብሔርን በድንቅ ሁኔታ ለማመስገን ከ Holy Beat አገልግሎት ጋር በብዙ መሰጠት እየተዘጋጀን እንገኛለን::በዚህ ሁኔታ ለጌታችን ምስጋናን እንድናቀርብ እድልን ስላገኘን ደስ ብሎናል::ስለ እናንተ አምላኬን አመሰግናለሁ::የምትወዱን ሁሉ ይሄንን ማስታወቂያ በማጋራት ለብዙዎች እንዲደርስ አብራችሁን ታገለግሉ ዘንድ በፍቅር ትጠየቃላችሁ:: በቀረው እግዚአብሔር በመገኘቱ መፅናናትና በረከት እንዲያድለን በፀሎት ከኛጋ ቁሙ:: ቡሩካን ናችሁ::

Address

Gibrina To Rift Valley Road
Shashemene

Telephone

+251911527330

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Christian Page , ክርስቲያን ፔጅ:

Share

Category