ኑረኢዝ ኑር

ኑረኢዝ ኑር ያንተ የሆነን ነገር አትጠይቅ

05/09/2025

ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱት በመካ የበኒ ሐሸም ሸለቆ ውስጥ በረቢዐል አወል ወር በዕለተ ሰኞ ማለትም እውቁ የታሪክ ተመራማሪ ሙሐመድ ሱለይማን መንሱር ፉሪና የሥነ ፈለክ ምሑራን ማሕሙድ ባሻ እንዳረጋገጡት በወርሃ ኤኘሪል 571 (ዓ.ል) የዝሆኑ ክስተት በተፈጸመ በዐመቱ፣ ኪስራ አኑሽረዋን በነገሠ በአርባ ዐመቱ ነው። ኢብን ሰእድ እንደዘገቡት የነቢዩ ሙሐመድ እናት ስለዚያች እለት ሲገልጹ፦ “ሙሐመድን በወለድኩ ጊዜ ከማሕጸኔ ብርሃን ወጥቶ የሶሪያን አብያተ መንግሥታት በብርሃኑ አደመቀ” ብለዋል።

ነቢዩ እንደተወለዱ እናታቸው ወደ አያታቸው ወደ ዐብድል ሙጦሊብ የብሥራት መልእክት ላከች። አያታቸውም በደስታ ተሞልተው መጡ። ሕጻኑንም ወደ ካእባ ይዘውት ገቡ፡፡ ዱዓ አደረጉለት፡፡ አላህንም ኣመሰገኑ፡፡ ሙሐመድ የሚል ሥም መረጡለት። ይህ ሥም ከዚህ ቀደም በዐረቦች ዘንድ የሚታወቅ አልነበረም። ዐረቦች እንደሚያደርጉት በሰባተኛው ቀን ገረዙት፡፡ እንደተወለዱ ከእናታቸው ቀጥሎ ያጠባቻቸው ሴት ሱወይባህ የተባለች የአቡ ለሐብ አገልጋይ ናት፡፡ አሳዳጊያቸው ነቢዩ ሙሐመድን ከሐሊማ ዘንድ በነበሩ ጊዜ አጥብታቸዋለች።

ሐሊማ ስለ ነቢዩ ሙሐመድ በረከታማነት ድንቃ ድንቅ ታሪኮችን አውግታለች። ኢብን ኢስሐቅ እንዲሀ ማለቷን ዘግበዋል፤ የማሳድገው ልጅ ፍለጋ ከትንሹ ልጄና ከባሌ ጋር በመሆን ከበኒ ሰእድ እንስቶች ጋር ወጣሁ። ዐመቱ የድርቅ ዓመት ነበር። ምንም ነገር አልነበረንም። ቦቃማ አህያ ተፈናጥጨ መጣሁ፡፡ ግመልም ነበረችን። ልጃችን ከረሃብ የተነሳ ስለሚያለቅስ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ በዓይናችን ሳይዞር ይነጋ ነበር። ጡቴ የሚያጠግብ ወተት አልነበረውም፡፡

ግመሏም የሚታለብ ወተት አልነበራትም፡፡ ግና አንዳች በጎ ነገር ተስፋ እናደርግ ነበር። አህያ እየጋለብኩ ረዥም መንገድ ተጓዝኩ። ድካም አልፈሰፈሰን። መካ ደርሰን የምናሳድገው ልጅ ፈለግን። የአላህን መልእከተኛ ያገኙ እንስቶች ሁሉ የቲም መሆናቸው ሲነገራቸው ሊወስዷቸው ፈቃደኛ አልሆኑም። ምክንያቱም ልጅ የምናሳድገው ከአባቱ በነ ውለታን በመፈለግ ነበር። የቲም ከሆነ ግን፡ “እናቱ እና አያቶቹ ምን ሊፈይዱልን?” እንል ነበር። በዚሀ ምክንያት የቲም መውሰድ አንፈልግም ነበር። አብረውኝ የመጡ እንስቶች በሙሉ የሚያሳድጉት ልጅ አገኙ። ልንመለስ በመዘጋጀት ላይ እያለን ለባለቤቴ፣ “በአላሀ እምላለሁ፣ የማሳድገው ልጅ ሳልይዝ ባዶ እጄን መመለስ ኣልፈልግም። ያን የቲም ልጅ ይዠው እመስሳለሁ” አልኩት። “ይሁን፣ ያዥው። አላህ በረከት ያደርግልን ይሆናል” አለኝ። ሄድኩና ያዝኩት፡፡

እንድወስደው ያስገደደኝ ሌላ ልጅ አለማግኘቴ ብቻ ነበር። ይዠው ወደ ማረፊያችን ተመለስኩ። ከጭኔ ላይ ሳስቀምጠው ጡቶቹ ወተት ያፈሱ ጀመር። እስኪጠግብ ድረስ ጠጣ። ወንድሙም እንደዚሁ እስኪጠግብ ጠጣ። ሁለቱም ተኙ። ከዚያ ቀን በፊት በልጄ ለቅሶ ምክንያት ተኝተን አናውቅም ነበር፡፡ ባለቤቴ ወደ ግመሏ ሲሄድ ጋቷ ሞልቶ አገኛት። አልቦ አመጣና እስክንጠግብ ድረስ ጠጣን፡፡ መልካም ሌሊትም አላለፍን፡፡

ሲነጋ ባለቤቴ፤ “ሐሊማ ሆይ፣ የያዝሽው ልጅ በረከታማ ነው” አለኝ። “በአላህ እምላለሁ፣ እኔም እንደዚያ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ” ኣልኩት። ጉዟችንን ቀጠልን። ከአህያዬ ላይ ከልጁ ጋር ተፈናጠጥን። የሁሉንም አህያ ቀድማ ገሰገሰች። ባልንጀሮቼ ተገረሙ። “የመጣሽበት አህያ አይደለምን? እባክሽን አትሩጭብን” ይሉኝ ጀመር። እኔም፡ “እርሷው ናት” ስላቸው፡ “የገጠማት አንዳች ነገር አለ” ይሉኝ ነበር። ከአገራችን ከበኒ ሰእድ ምድር ደርሰን አረፍን። እንዲያ ያለ ድርቅ አይቼ አላውቅም። ግና ከተመለስን በኋላ (ቤታችን በረከታማ ሆነ)፡፡ ፍየሎች ውለው ሲገቡ ጠግበውና ጋታቸው ሞልቶ ነው። እነርሱን እያለብን እንጠጣለን። ሌሎች ሰዎች ግን ከፍየሎቻቸው ጋት ጠብታ ወተት አያገኙም። የመንደሩ ሰዎች ለልጆቻቸው፡- “አደራችሁን፣ የአቢ ዙአይብ ልጅ (የሐሊማ) ፍየሎች ከሚስማሩበት አሰማሩ” በማለት ያዙ ጀመር። ይህም ሆኖ የነርሱ ፍየሎች ጋት ጠብታ ወተት አይቋጥሩም። የኔዎቹ ግን ጋታቸው ሞልቶ ይፈሳል። በዚህ ሁኔታ የአላህን በረከት እያገኘን ሁለት ዐመታትን አሳለፍን። ልጁም እያደግ ሄደ። ጨዋታው እንደሌሎች ልጆች አይደለም፡፡ ሁለት ዓመት ሲሞላው ጎበዝና ጠንካራ ልጅ ሆነ። ከእናቱ ዘንድ ወሰድነው፡፡ በረከታማ ከመሆኑ አኳያ አብሮን እንዲቆይ ስለፈለግን እናቱን፡ “የመካን ወባ ስለምንፈራለት ከኛ ዘንድ ጥቂት እስኪጎብዝ ይቆይ” ስንል ተማጸንናት። አብሮን እንዲመለስ ፈቀደችልን።

የአላህ መልእክተኛ በዚህ አኳኋን ከበኒ ሰእድ አገር ቆዩ። እድሜያቸው አራት ወይም አምስት ዓመታት ሲሞላቸው ድንቅ ነገር ተከሰተ። ሙስሊም አነስን ዋቢ በማድረግ እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ ከልጆች ጋር በመጫወት ላይ እያሉ ጅብሪል መጣና ያዛቸው፡፡ ከመሬት ላይም ጣላቸው፡፡ ደረታቸውን በመቅደድም ልባቸውን አወጣው። የተላመጠ ስጋ የሚመስል አንዳች ነገር ከውስጡ አወጣና፡ “ከአንተ ውስጥ የሰይጣን ድርሻ ነው” ካለ በኋላ በወርቅ ሳህን ላይ አስቀምጠ በዘምዘም ውሃ አጠበው። ከዚያም ወደነበረበት ቦታ መለሰው፡፡ ልጆች ወደ እናታቸው ዘንድ እየሮጡ በመሄድ፡ ‹‹ሙሐመድ ተገደለ» ሲሉ ነገሯት። ከነርሱ ጋር ስትመጣ የነቢዩ ፊት ተለዋውጦ አገኘቻቸው። አነስ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፡ “የዚህን ክስተት ፋና ከደረታቸው ላይ እመለከት ነበር።” (ሚንበር ቲቪ)

ምንጭ፡ ረሒቀል መኽቱም

★ ★ ★ Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000 !

29/08/2025

የሐጅ ተጓዦች በክልል አየር ማረፊያዎች ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ በቀጥታ በረራ እንዲስተናገዱ መንግሥት አቅጣጫ አስቀመጠ

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን፤ እንደ ሐጅ እና ኡምራ ዐይነት ሃይማኖታዊ ጉዞዎች በሚካሄዱበት ወቅት በረራሮችን ከክልሎች ቀጥታ ለማድረግ የመንግሥት አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዕቅዱ በሒደት ላይ እንደሚገኝ ለ“ሚንበር ቲቪ” ተናግረዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ይህን የገለጸው በ2018 የክልል አየር ማረፊያዎችን አቅም በማጎልበት መንገደኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ ጥረት እንደሚደርግ በገለጸበት ወቅት ነው፡፡ በባለሥልጣኑ መረጃ መሠረት፤ በተለይ እንደ ሐጅና ዑምራ ዐይነት ሃይማኖታዊ ጉዞዎች በሚካሄዱበት ወቅት የክልል አየር ማረፊያዎች በተለይ ከባሌ ሮቤ፣ ከጅግጅጋ፣ ከአሶሳ፣ ከሰመራ እና ድሬዳዋ ከተሞች በርካታ ተጓዦችን ወደ አዲስ አበባ በማሳፈር፤ ከመዲናዋ ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ የሚያደርጉት ጉዞ “አላስፈላጊ መጉላላትን የሚያደርስ ብቻ ሳይሆን በአየር መንገዱ ላይ አላስፈላጊ ጫና” የሚፈጥር ነው፡፡

በመሆኑም ጉዞውን በማሳጠር ተጓዦች “ካሉበት ክልል በቀጥታ ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ ጉዞ ማድረግ የሚችሉበት መንገድ ማመቻቸት አስፈላጊ መሆኑን” ያስታወቀው ባለሥልጣኑ፤ “የመንግሥትም አቅጣጫ ጭምር በመሆኑ” ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በተጨማሪ ከጉምሩክ፣ ከኢምግሬሽንና ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መንግሥታዊ ተቋማት ጋር “በመነጋገርና መግባባት ላይ በመድረስ” ጉዳዩ እልባት እንደሚያገኝ መሥሪያ ቤቱ ያለውን እምነት ገልጿል።

የበረራውን ዕቅድ በተመለከተ ለ“ሚንበር ቲቪ” የተናገሩት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ሐጂ ዐብዱልፈታህ ሙሐመድ፤ የምክር ቤቱ ኃላፊዎች ስለ ጉዳዩ መረጃ እንዳላቸው አረጋግጠዋል፡፡

ዕቅዱ በቀዳሚነት የተነሳው በ2016 ተግባራዊ በተደረገው ሁሉም የክልል ተመዝጋቢ ምዕመናን በመኖሪያ አቅራቢያ በተከፈቱ ጣቢያዎች እንዲስተናገዱ በተደረገበት ወቅት እንደነበር በማስታወስ፤ በተለይ በሐጅ ወቅት በርካታ የቁጥር ድርሻ ያላቸውን የጅግጅጋ እና ጎዴ ተመዝጋቢዎች ለማስተናገድ እንደ እቅድ ቀርቦ ነበር ብለዋል፡፡ ዕቅዱን አሁንም ተግባራዊ ለማድረግ በሒደት ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት ኃላፊው፤ ሲጠናቀቅ ሊጀመር እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

እንደ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ከሆነ፤ በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በተጨማሪ የባሕር ዳር፣ የመቀሌ፣ የድሬዳዋ አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ ተብለው የተለዩ ናቸው፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

በድረ ገጽ ያንብቡ፡- https://minbertv.com/?p=10758

★ ★ ★
Minber TV
| EthioSat | 11545 | H | 45000
!

?
28/08/2025

?

28/08/2025

የሀላባ ዞን የመጅሊስ መርጫ ከዚህ በባሰ መልኩ ነው ምርጫው በግለሰቦች የተጭበረበረው
ዳግም እንዲታይልን እንሻለን::

Federal Majlis Election Board የፌዴራል መጅሊስ ምርጫ ቦርድ

27/08/2025
27/08/2025

“ምርጫውን ለማዘግየት እና ለማስቀረት ግፊት ተደርጓል” - ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ፤ የምክር ቤቱን የ2017 ምርጫ “ለማዘግየት እና ለማስቀረት ግፊት ተደርጓል” ሲሉ የተደመጡት ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 21/2017 እየተካሄደ በሚገኘው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ነው፡፡ ፕሬዝዳንቱ ምርጫውን ለማዘግየት እና ለማስቀረት ግፊት ቢደረግም “በጠቅላላ ጉባዔው አባላት ቆራጥነት” ተሳክቷል ብለዋል፡፡

ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ምርጫውን ለማዘግየት እና ለማስቀረት ግፊት ተደርጓል ቢሉም ይህን አድርገዋል ያሏቸውን አካላት ግን በሥም አልጠቀሱም፡፡ “ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በነቂስ ወጥቶ የተረባረበበት ነው” ሲሉ በገለጹት ምርጫም፤ “ታሪካዊ ሥራ ተሠርቷል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የ2017 ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ ነሐሴ 9 እና 11/2017 ባካሄደው የምክር ቤቱ ምርጫ ከ13 ሚሊየን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን ቢገልጽም፤ በምርጫው ድምጽ የሰጡ ምዕመናን ቁጥር ስንት እንደሆነ እስካሁን ድረስ ይፋ አላደረገም፡፡ የቦርዱ አባላት በሰጧቸው መግለጫዎች ምርጫው “በተሳካ መልኩ” መጠናቀቁን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
!

01/06/2025
22/04/2024

ኢና ሊላሂ ወዒና ኢለይሂ ራጂዑን

የመናዊው እውቅ አሊም የነበሩት ሼይኽ አብዱልመጂድ ቢን አዚዝ አዘንዳኒ በ82 አመታቸው ወደ አኼራ ሄደዋል::

ሼይኽ አብዱልመጂድ ቢን አዚዝ አዘንዳኒ በ1942 በሰሜናዊ የመን የተወለዱ ሲሆን በአባታችን መልካም አስተዳደግ ኢስላማዊ እውቀትን በተያዩ የሀገራቸው አሊሞች ተዘዋውረው ቀስመዋል:: በሀገረ ግብፅም ከኢስላማዊ እውቀት በተጨማሪ ኬሚስትሪ እና ባዬሎጂን አጥንተዋል::

ሼይኹ ከጥልቅ የምርምር ስራዎቻቸው በተጨማሪ ሁለገብ አሊም ነበሩ::

ሼይኽ አብዱልመጂድ ቢን አዚዝ አዘንዳኒ በእስልምና ውስጥ ያሉ ሳይንሳዊ ተዓምራቶች ዙሪያ በርካታ ጥናቶችን በማድረግ ለንባብ ያበቁ ሲሆን በዚህ ስራቸውም በመላው አለም ለሚገኙ ቁጥራቸው በርካታ ለሆኑ ሳይንቲስቶች እና ተመራማሪዎች ወደ እስልምና እንዲገቡ ሰበብ መሆን ችለዋል::

በሳውዲ አረቢያ በቆዩበት ዘመንም ከሳኡዲ አረቢያ ሙፍቲ ከሼይኽ አብዱልአዚዝ ኢብኑ ባዝ እና ከሼይኽ መሐመድ ቢን ሷሊህ አልኡሰይሚን ጋር መገናኘት የቻሉ ሲሆን ለሰሯቸው በርካታ ኢስላማዊ ስራዎች እና የኢስላማዊ ድንጋጌዎች ብያኔዎችን በብዛት እንደ ማጣቀሻ ሁለቱን አሊሞች ይጠቀሙ እንደነበር ይነገራል::

ሼይኽ አብዱልመጂድ ቢን አዚዝ አዘንዳኒ የአለም ኡለማዎች ምክር ቤትን ከመሰረቱት ኡለሞች መካከል ሲሆኑ በቁርኣን እና በሳይንስ ዙሪያ የሚያካሂዱትን የምርምር ስራ የሚያግዝ በየመን የኢማን የኒቨርሲቲንም ማቋቋም የቻሉ አሊም ነበሩ::

በተለይ በሰው ልጅ አፈጣጠር እና በፅንስ እድገት ዙሪያ ቁርኣን ውስጥ የሚገኙ አንቀፆችን በማብራራት ከሳይንሱ በፊት ቁርኣን ምን ያህል ለሰው ልጆች ሂደቱን እንዳብራራ በማስተማር በርካታ እውቅ ተመራማሪዎችን ወደ ኢስላም ማስገባት ችለዋል::

በሳኡዲ አረቢያም በጅዳ በሚገኘው የንጉስ አብዱልአዚዝ ዩኒቨርሲቲ ስር የተቋቋመው የሙዓሰሳ አልኢጃዝ አልኢልሚ ሱፕርቫይዘር በመሆን ያገለገሉ ሲሆን በቁርዓን ሳይንሳዊ ተዓምራት ዙሪያ በበርካታ የሳኡዲ አረቢያ ዩኒቨርሲቲዎች እና ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ማቅረብ ችለዋል::

የአለም ሙስሊሞች ሊግም እንዲመሰረት ምክረ ሃሳብ ያቀረቡ አሊም ሲሆኑ በተቋሙ ስር የምርምር ክፍሉን በመምራት የመጀመሪያው ለመሆን በቅተዋል::

በርካታ መፅሃፍቶችንም ለህትመት በማብቃት ለንባብ ያበቁ ሲሆን ከስድስት ያላነሱ ያልታተሙ መፅሀፍቶችንንም አበርክተዋል::

እኚህ ታላቅ አሊም በተወለዱ በ82 አመታቸው በሀገረ ቱርክዬ ወደ አኼራ የሄዱ ሲሆን በህይወት ዘመናቸው ለኢስላም ያበረከቱት አስተዋፅኦ ትውልዱ ዘወትር የሚዘክራቸው ይሆናል::

ሼይኽ አብዱልመጂድ ቢን አዚዝ አዘንዳኒ አላህ ይዘንላቸው፣ ማረፊያቸውንም በጀነተል ፊርዶስ ያድርግላቸው

Ⓞ➁
22/04/2024

Ⓞ➁

Address

Alaba K'ulito
001

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኑረኢዝ ኑር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ኑረኢዝ ኑር:

Share