Feta Daily / ፈታ ዴሊይ

Feta Daily / ፈታ ዴሊይ ወቅታዊ መረጃዎችን ወደናንተ እናደርሳለን፡፡

28/11/2025
22/11/2025

ዘመድ የሌለው ከንቱ ነው

💪💪💪ከድሉ ጀርባ ያሉ እጆች 💪💪💪
23/10/2025

💪💪💪ከድሉ ጀርባ ያሉ እጆች 💪💪💪

20/10/2025

ገሎ ማልቀሱን ተክናቹበታል

ሰበር መረጃ“በግፍ ያጣናው የባህር በር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር መመለሱ አይቀርም”  ኮሞዶር ተገኝ ለታ፤ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ“በግፍ ያጣናው የባህር በር የጊዜ ጉዳይ ካልሆ...
20/10/2025

ሰበር መረጃ

“በግፍ ያጣናው የባህር በር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር መመለሱ አይቀርም” ኮሞዶር ተገኝ ለታ፤ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ

“በግፍ ያጣናው የባህር በር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር መመለሱ አይቀርም” ሲሉ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ አስታወቁ። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላምና መረጋጋት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ምክትል ባሕር ኃይል አዛዡ ገልጸዋል።

ምክትል አዛዡ ይህን የተናገሩት ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በመከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር “የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፣ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ” በሚል ዐቢይ ርዕስ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ የኢትዮጵያ ወደብ አልባ መሆን በሀገሪቱ ላይ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ ሊኖረው የሚችለው ኢኮኖሚዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ መዘዝን መረዳት ተገቢ መሆኑንም አጽኖት ሰጥተው ተናግረዋል።

“የወደብ ጉዳይ መንግስታዊ አጀንዳ ሆኖ ቀርቧል” ያሉት የባህር ኃይል ምክትል አዛዡ፤ በቀይ ባሕር ቀጣና እየታዩ ናቸው ያሏቸው ጂኦ ፖለቲካዊ ለውጦች ኢትዮጵያ ከቅርብ ባሉት ነገር ግን በውል ካልጠቀሱት ጊዜ ወዲህ በቀይ ባህር ላይ ያላት ጥያቄ ቀዳማዊ ብሔራዊ አጀንዳ ለማድረጓ ገፊ ምክንያት መሆናቸውን ጠቁመዋል። በከፍተኛ ደረጃ እያደገ ያለው የሎጂስቲክስ ፍላጎት ለጥያቄው መነሳት አንደኛው ምክንያት መሆኑንም አመላክተዋል።

እንደምክትል አዛዡ ገለጻ፤ የባሕር በር ያስፈለገበትን ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ከትናንሽ እስከ ትላልቅ ያሏቸው ነገር ግን በስም ያልጠቀሷቸው ሀገራት በቀጣናው የጦር ሰፈር መገንባታቸው ነው።

“በመሆኑም የጦር ሰፈሮች በቀጣናው መኖራቸው ይዟቸው የሚመጡ ችግሮችን ቀድሞ በመተንበይ፣ በመዘጋጀት፣ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ላይ ያተኮረ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል” ብለዋል።

የወደቡ ጉዳይ ዕልባት አለማግኘት ከቀጠለ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንዲፈጠር በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ አስተዋጽዖ ማድረጉ የማይቀር መሆኑን በማመለካት አስፈላጊነቱን እና ሊያመጣ የሚችለውን አሉታዊ ውጤትም አስገንዝበዋል።

በሰሜናዊ ሕንድ ውቅያኖስ እና ቀይ ባህር ላይ የሚታዩ ውንብድናዎችንና ግጭቶችን ለመከላከል ጠንካራ የባህር ኃይል አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት እየተሰራ ስለመሆኑም ምክትል አዛዡ ተናግረዋል።

የባሕር በር አስፈላጊነትን፣ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን በግፍ መነጠቋን እንዲሁም መመለሱ አይቀሬ መሆኑን ሲናገሩ ምክትል አዛዡ የመጀመሪያው አይደሉም።

በመከላከያ ሚኒስቴር የውጪ ግንኙነት እና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል ተሾመ ገመቹ የባህር በር እየጠየቅን ያለነው “ዝም ብለን ከመሬት ተነስተን አይደለም” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

ለዚህም አራት ምክንያቶችን የጠቀሱ ሲሆን እነዚህም ኢትዮጵያ ከአሰብ ጋር ያላት ታሪካዊ ትስስር፣ መልካም ምድራዊ ቅርበት፣ የህልውና ጥያቄ እና የጸጥታ ስጋቶች መሆናቸውን መናገራቸው ይታወሳል። ሌሎች ወታደራዊ መኮንኖችም ተመሰሳሳይ አስተያየት ሲያንጸባርቁ መክረማቸው አይዘነጋም።

ለእኔ ወንድ አያቴ ነበሩ 😥😥😥😥ወደህክምና ልገባ ስል ሀሙስ ቀን ማታ ላይ ሳውዲ እያለሁ ከኢትዮጵያ ደውለው ልጄ እኔ የእምነት አባትሽ ባልሆንም እንደ ወንድ አያትሽ አርገሽ ቁጠሪኝ እኔ አንቺ...
20/10/2025

ለእኔ ወንድ አያቴ ነበሩ 😥😥😥😥
ወደህክምና ልገባ ስል
ሀሙስ ቀን ማታ ላይ ሳውዲ እያለሁ ከኢትዮጵያ ደውለው ልጄ እኔ የእምነት አባትሽ ባልሆንም
እንደ ወንድ አያትሽ አርገሽ ቁጠሪኝ እኔ
አንቺን እንደ ልጆቼ ልጄ ብዬሻለሁ
የዛሬው ዱአዬ ሁሉ ላንቺ ይሁን ድነሽ ቆመሽ እንደ እድሜሽ ከእኩዮችሽ እኩል ስቀሽ ያኑርሽ
ልጅነትሽን አይቀማሽ ልመርቅሽ አሉ
አላህ በጤና ይመልስሽ የአፉያ ካባውን ያልብስሽ አሉ ።እኛ በሀዘኔ ሰአት ያበረቱኝ አባቴ
አዎ እኛ ወንድ አያቴ ዛሬ አረፉ
💔💔💔አፈሩን ገለባ ያርግሎት
አባቴ ሀጂ 😥😥

ህይወት መስፍን 🖋️🖋️🖋️

18/10/2025

ሻዕቢያ ህወሀትን ቀብሮታል !!!

‹ኢሳያስ አፈወርቂ ከአገር ይኮበልላሉ››ቲቦር ናጂየቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ሻብያን ነክሰው ይዘዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም ፈርጥጠ...
17/10/2025

‹ኢሳያስ አፈወርቂ ከአገር ይኮበልላሉ››

ቲቦር ናጂ

የቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ሻብያን ነክሰው ይዘዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም ፈርጥጠው ከአገር ይወጣሉ ይህም በቅርብ ይሆናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

የአሰቡ ዘመቻ ከተጀመረ ኢሳያስ ከስልጣን ይወገዳሉ የሚል ትንተና እየተሰጠ ባለበት በዚህን ወቅት አምባሳደሩ ያሰሙት ጉዳይ ሻብያን ያስደነገጠ እና ያሸበረ ሆኗል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ከጸረ ሻብያ ቡድኖች ጋር አምባሳደሩ በአሜሪካ እንደመከሩም ታውቋል፡፡

የቀድሞው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ቲቦር ናጂ የአስመራውን መንግስት በተመለከተ አነጋጋሪ አስተያየቶችን መስጠት ቀጥለዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም ከጸረ ሸብያ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ እያሳደጉ ይገኛል፡፡

አምባሳደሩ በትናንትናው እለትም ከብርጌድ ንሓምዱ የሰማያዊ ማዕበል ንቅናቄ መሪዎች ጋር በአሜሪካ መወያየታቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

ከሰማያዊ ማእበል ንቅናቄ መሪዎች ጋር መወያየታቸውን በገለጹበት የኤክስ ልጥፋቸው ላይ፣ ‹‹ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከዚህ ቀደም እንደነበሩ አምባገነኖች ሁሉ ከአገር ይኮበልላሉ›› ብለዋል፡፡

አምባሳደሩ ከዚህ ቀደም በአለም ላይ ያለፉ እንደ መንግስቱ ኃይለማሪያም እናጋዳፊ ያሉ አምባገነን መሪዎችን በመጥቀስ የኢሳያስ አፈወርቂም እጣ ከዚህ የሚለይ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

Address

Holeta
Shewa

Telephone

+251955418273

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Feta Daily / ፈታ ዴሊይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Feta Daily / ፈታ ዴሊይ:

Share