11/04/2026
በዌራ ወረዳ በአለምጤና ቀበሌ በሞግዶላ ብልፅግና ህብረት እየለማ የሚገኝ 7.5 ሄ/ር የሚሸፍን ነባር የቡና ማሳ ምልከታ ተደረገ ።
በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በአለምጤና ቀበሌ በሞግዶላ ብልፅግና ህብረት እየለማ የሚገኝ 7.5 ሄ/ር የሚሸፍን ነባር የቡና ማሳ የፌዴራል የክልል የዞን የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፍዎች ምልከታ አድርጓል ።
የቡና ልማትና ግብይት ዉጤታማነት ህብረተሰቡ ተገንዝበው ሁሉም ማህበረሰብ ቡናን የመትከል ባህል በማሳደግ እያንዳንዱ አርሶአደር በየማሳው በመትከልና የተተከሉ ችግኞች ውጤታማና ፍሬያማ እንዲሆኑ ልያንካባክብ እንደሚገባ ተገልፀዋል ።
ይህንኑ በመገንዘብ ቡና ለአንድ አከባቢ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኢኮኖሚ ምንጭ መሆኑንም በመገንዘብ ሁሉም አርሶአደር የተሻሻላ የቡና ችግኝ በመትከል ምርትና ምርታማነት በማሰደግ ቡናን ከገበያ ሰይሆን ከጓሮው መጠቀም እንደሚገባ ተገልጸዋል
የአካባቢውን የተፈጥሮ ጸጋ በአግባቡ በመለየትና በመጠቀም ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም አመራሮቹ ተናግረዋል ።
በመርሐግብሩ ላይ የኢፌዴሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴዔታ ወ/ሮ ሕክማ ኬይረዲን፣ የስራና ክህሎት ሚንስቴር ሚኒስትር ዴዔታ ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድናስር፣ በኢፌዴሪ ፓርላማ የሀላባ ተወካይ ዶ/ር ነጃት ግርማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ-ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑርዬ፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባዔ ወ/ሮ መነቴ ሙንድኖ፣ የክልሉ ሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሀላፊና የአሰሪና ሠራተኛ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ በይዴ ሙንድኖ፣ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን፣ የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲና የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አቶ መሐመድከማል ኑርዬ፣ የሀላባ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ የተከበሩ መሐመድአሚን መህዲ፣ የዞንና የዌራ ወረዳ አስተባባሪዎች እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል።
✍️በአስራሩ ጀማል