የሌተ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አድናቂ

የሌተ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አድናቂ ምን ግዜም ስለፍትሕ፣ እውነት፣ ነፃነት፣ እኩልነት፣ ሳልሰለች በታማኝነት እናገራለሁ!!!!

የኢሕአፓው ተስፋዬ ደበሳይ የደርግ ወታደሮችን ሸሽቶ አንድ ዶክተር ጓደኛው ቤት ህቡዕ ገብቶ(ተደብቆ) እየኖረ ነው። አንድ ቀን ተስፋዬ ለዶክተሩ ጓደኛው ቄስ አጎቱ ከገጠር ሊጠይቁት እንደሚመጡ...
12/07/2025

የኢሕአፓው ተስፋዬ ደበሳይ የደርግ ወታደሮችን ሸሽቶ አንድ ዶክተር ጓደኛው ቤት ህቡዕ ገብቶ(ተደብቆ) እየኖረ ነው። አንድ ቀን ተስፋዬ ለዶክተሩ ጓደኛው ቄስ አጎቱ ከገጠር ሊጠይቁት እንደሚመጡ ይነግረዋል። ጓደኛውም በሀሳቡ ይስማማ እና ቄሱ ወደ ቤታቸው ተስፋዬን ለማየት ይቀላቀላሉ። የተስፋዬ ደበሳይ አጎት ጠዋት እና ማታ ዳዊት ከመድገም እና ለማዕድ ሲቀርቡ ቆርሶ ባርኮ ከመስጠት ውጪ ብዙ የማይናገሩ ዝምተኛ ቄስ ነበሩ። ሲያወሩ የንግግር ዘዬያቸው የሚያምር የባላገር አይነት ነው። በዚህ ሁኔታ ጥቂት ቀናት ይቆያሉ። ተስፋዬም አጎቱን እያጫወተ መፅሀፍ እያነበበ እና ከጓደኛው ጋር ቼዝ እየተጫወተ ጊዜውን ያሳልፋል። አንድ ቀን ምሽት ላይ እንደተለመደው ተስፋዬ ደበሳይ እና ዶክተሩ ጓደኛው ቼዝ እየተጫወቱ ቄሱ ዝም ብለው ይመለከታሉ። ጨዋታውም እየተጋጋለ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ይደርሳል። ዶክተሩ ጓደኛው ተስፋዬን ለማሸነፍ ከጫፍ ደርሷል። ተስፋዬም ላለመሸነፍ በከፍተኛ ተመስጥኦ ውስጥ ሆኖ ያሰላስላል። ቄሱም እንደተጫዋቾቹ ተመስጠው ቼዙ ላይ አፍጥጠዋል።እንዴት ቢሄድ ከመሸነፍ እንደሚድን ሲያብሰለስል የነበረው ተስፋዬም በጭንቀት አንዱን የቼዝ ፈረስ በዘፈቀደ አንስቶ ይሄዳል።ይሄኔ በተመስጦ ሲያዩ ከነበሩት የባላገር ቄስ ከአፋቸው አንድ ቃል ይወጣል "wrong move"🤝
ተስፋዬ እና ዶክተሩ ጓደኛው በከፍተኛ ድንጋጤ ወደ ባላገሩ ቄስ ይዞራሉ። ቄሱም ደንግጠው መልሰው ያፈጣሉ። እኚያ ቄስ ትክክለኛ ቄስ ሳይሆኑ የኢህአፓው ታጋይ የነበረው ሊቁ ጸጋዬ ገብረመድህን(ደብተራው) ነበር። ተስፋዬ የትግል አጋሩን ዶክተር ጓደኛው ቤት ለመደበቅ ከደብተራው ጋር ተመካክረው ያወጡት እቅድ ነበር።


እግረ መንገድ

የዘፋኝ ኩሩ ኤፍሬም ታምሩ!!!ደግሞ ጀመረኝ፣ አስታውስሻለው፣ አማነሽ ወይ፣ ሰላም ለበለው እና ሌሎች አስደማሚ ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ ማነው?ከአቶ ታምሩ አመራ እና ከወይዘ...
29/06/2025

የዘፋኝ ኩሩ ኤፍሬም ታምሩ!!!

ደግሞ ጀመረኝ፣ አስታውስሻለው፣ አማነሽ ወይ፣ ሰላም ለበለው እና ሌሎች አስደማሚ ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ ማነው?

ከአቶ ታምሩ አመራ እና ከወይዘሮ አትገኝ ብዙነህ በባህርዳር ከተማ የተወለደው እውቁ ድምጻዊ ኤፍሬም ታምሩ አባቱ የፖስታ ቤት ስራ አስኪያጅ ሰለነበሩ ለስራ ወደ ባህር ዳር ባቀኑበት ወቅት ነበር ኤፍሬም የተወለደው፡፡..
ኤፍሬም የባህርዳር ቆይታው እስከ አንደኛ ክፍል ብቻ ነበር አባቱ በስራ ምክንያት በመቀየራቸው ወደ ደብረ ማርቆስ ከወላጆቹ ጋር አቅንቷል ከዛም ወደ ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት የአሁኑ ዲላ ማለት ነው እዛ በመሄድ ተምሯል፡፡..
ኤፍሬም የአምስተኛ ክፍል ትምህርቱን እስከ ግማሽ አካባቢ የተማረው አዲስ አበባ ይሁን እንጅ አባቱ በገጠማቸው የመኪና አደጋ ምክንያት ወደ ደጀን ለመመለስ ተገዷል፡፡ የኤፍሬም ታሪክ እና የሙዚቃ ህይወት የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው በወቅቱ ደጀን
ላይ እስከ 8ተኛ ክፍል ብቻ ትምህርት ይሰጥ የነበረ በመሆኑ ኤፍሬም ወደ ደብረማርቆስ ተጉዞ እስከ 10ኛ ክፍል ትምህርቱን ተከታተለ፡፡..
የኤፍሬም ቤተሰቦች የቤተክህነት ሰዎች በመሆናቸው የሙዚቃ ፍላጎቱ ተቀባይነት አልነበረውም ይሁን እንጅ ኤፍሬም ከቤተሰቦቹ በመደበቅ አርብ አርብ በትምህርት ቤቱ በነበረው የሙዚቃ ዝግጅት ይሳተፍም ነበር፡፡ አስፋው ክበበው ከተባለ የሙዚቃ ሰው ጋር በመሆንም ጊምቢ ወለጋ ጅማ እና የተለያዩ የሃገሪቱ ቀጠናዎችን ከ12 አመቱ ጀምሮ መዞር ጀመረ። ኤፍሬም በአውራጃዎች የሙዚቃ ውድድር ወቅት በዘመናዊ ሙዚቃ አንደኛ መውጣትም ችሏል። በኋላ ላይ ደግሞ ከአያሌው መስፍን ጋር በመቀናጀት መስራትም ችሏል፡፡ በዚህ ጊዜ እውቅናን ማግኘት ጀምሮ ነበር፡፡ አባቱ ግን የእሱን ዝነኛ መሆን ሳያዩ አርፈዋል፡፡ ..
የኤፍሬም የህይወቱ ምእራፍ ሁለት የጀመረው በአዲስ አበባ ሲሆን ከ9ኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል በምስራቅ አጠቃላይ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የጨረሰ ሲሆን የሙዚቃ ህይወቱ ደግሞ ማረፊያ የነበረው "ዛምቤዚ" የተባለ ክለብ ነበር ከዛም አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ እውቅ ሆቴሎች ሰርቷል፡፡
የድምጻዊ አሊ ቢራን ስራዎች ይወዳቸው እንደነበር ኤፍሬም ይናገራል በአሊ ቢራ ተፈትኖ ተወዳጅነትንም አግኝቷል፡፡..
የኤፍሬም የመጀመሪያ ስራ የአያሌው መስፍን "ጋሜ" የሚል መጠሪያ የነበረው ሙዚቃ ሲሆን ብዙም አልተደመጠለትም ነበር፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት ደግሞ በወቅቱ ታላላቅ አንጋፋ ሙዚቀኞች በመኖራቸው ለጀማሪ ሙዚቀኞች ትኩረት የሚሰጥ ባለመኖሩ ነበር፡፡ ኤፍሬምን ከህዝብ ጋር እንዲተዋወቅ ያደረገው ነይልኝ የሚለው ስራው ነበር :: ኤፍሬም ለብቻው ያስቀረፃቸው ካሴቶች ቁጥር 12 ሲሆን፣ በተጨማሪም ከሌሎች ድምፃውያን ጋር በመሆን በርካታ የሙዚቃ ስራዎችን ሰርቷል፡፡..
ኤፍሬም በ1974 ስለኪነት አጀማመሩ ቃለ መጠይቅ በተደረገለት ወቅት እንደተናገረው ከሆነ ለሱ የኪነጥበብ መጀመር ሁነኛ ሚና የተጫወተው በ1960 ዓ.ም. አካባቢ ደጀን በተባለ ቦታ በትምህርት ቤቱ ውስጥ ሙዚቃ መጀመሩ የነበረ ሲሆን። ከዛ በበለጠ ለሱ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣለት ግን በ1963 ዓ.ም. ወደ ደብረ ማርቆስ ሄዶ በሙዚቃ ውድድር ማሸነፉ ነበር። ይህም ከአጠቃላይ ጎጃም አንደኛነትን ያስገኘለት ሲሆን በዚሁ የኪነጥበብ ሥራ እንዲተጋ ደሞ አይነተኛ አስዋፅኦ እንደነበረውም ገልጿል።..
ኤፍሬም በሃገራችን ከፍተኛ አድናቆትና ተወዳጅነትን ያተረፈ አርቲስት ሲሆን ይህን ዝና ያስገኙለት ደሞ የሰራቸው 12 አልበሞች ናቸው። በተለይም "ነይልኝ" የሚለውን አልበም ባወጣ በአመቱ "ልመደው" የተሰኘውን አልበም ይዞ መምጣቱ ይበልጥ ተወዳጅ አድርጎታል። በሙዚቃ አፍቃሪያን ከተወደዱለት ዜማዎቹ ጥቂቶቹን ብናነሳ እንኳ ጀማዬ ነይ ነይ ፣ አንቺዬ ጎጃም እንዴት ነሽ ፣ ሸግዬ ፣ አካል ሸጋ ፣ የሰማይ ላይ ኮከብ ፣ ሙሉ ጎጃም ፣ ሸግዬ ፣ ተከልከይ በዓዋጅ ፣ ልኑር ካንቺ ጋር ፣ ቢልልኝ ፣ ደሞ ጀመረኝ እና ሌሎች ግሩም ስራዎቹ ናቸው።

እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዘፈኖቹን ደስ እያለኝ የምሰማው ሰው ኤፍሬም ታምሩ 😊

በጣም የምወደው ድምፃዊ ነው ሁሉንም በሚባል መልኩ የሱን ሙዚቃዎች አውቃቸዋለሁ ይበልጥ ደሞ ሰማኒያዎቹ ውስጥ የሰራቸው ዘፈኖቹ ይለዩብኛል የድሮ ስራውን ከሮሃ ባንድ ጋር እንደገና ከሰራ በኋላ ጠፍቷል እንደተለመደው በአዲስ እና አስደማሚ ስራ ይመጣል በሚል ተስፋ እናደርጋለን።

ደብረታቦር እና ወልደያ ሕዝባዊ ትዕይንት!!
29/06/2025

ደብረታቦር እና ወልደያ ሕዝባዊ ትዕይንት!!

ኢትዮጵያ ጦርነት ጠማቂም ሆነ፣ ጦርነት በትንኮሳ ጀምራ አታውቅም! ሻዕቢያ ደግሞ ከፍርሀቱ የተነሳ ዘው ልበል እያለ ነው። ያው ሻዕቢያ ፕሮጀክት መርቆ ከማስጀመር ጦርነት ባርኮ መጀመር ይቀናዋ...
29/06/2025

ኢትዮጵያ ጦርነት ጠማቂም ሆነ፣ ጦርነት በትንኮሳ ጀምራ አታውቅም! ሻዕቢያ ደግሞ ከፍርሀቱ የተነሳ ዘው ልበል እያለ ነው። ያው ሻዕቢያ ፕሮጀክት መርቆ ከማስጀመር ጦርነት ባርኮ መጀመር ይቀናዋል።😂

የሻዕቢያ የጦርነት ዝግጅት በትግራይ ክልል ተሟሙቆ ቀጥሏል። እነ ደብረፂዮን ጦርነት ለኩሰው መኖሪያቸውን ናቅፋና አስመራ ለማድረግ ተቻኩለዋል።

ነገር ግን ምስኪኑ ለጥቂት ግለሰቦች ህይወቱን ሲገብር የኖረው ኢትዮጵያዊው የትግራይ ህዝብ የዚህ ጉዳይ አካል አይደለም። በእነዚህ የደም ነጋዴዎች ከማንም በላይ በሻዕቢያ ተላላኪዎች ለዘመናት ዋጋ የከፈለው የሰሜኑ ኢትዮጵያዊ ነው።

የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ግዛቱን የሚከላከለው ከዚሁ ለዘመናት የደም ዋጋ ከከፈለው የትግራይ ክልል ህዝብ ጋር ሆኖ ነው።
ጉዳዩ አሁን ላይ የተለየ ነው ፣ ትናንት ዛሬ አይደለም። ህዝብ ማን ጠላቱ እንደሆነ ከገጠር እስከ ከተማ ጠንቅቆ አውቋል።
የነ መንጆሪኖ መጋጋጥ የአሰብን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ከማፍጠን ውጪ ሌላ ውጤት የለውም ።

አንዲት ጥይት ኢትዮጵያ ውስጥ ከተተኮሰ በነጋታው የኢትዮጵያ ጦር አሰብ ላይ ይገኛል ! ቀጥሎ አስመራ።

ገዳይ አሻንጉሊቶች ፨፨፨፨ተጫዋች ነው ። እረፍት የለሽ ። ደፋር ነው ። ወጣቶች እወዳለሁ ፣ አእምሮዬን ያሠሯታል ይላል ። ምንም ይሁን ምን መጫወቻ መስራት የምፈልገው ። ለምንም አይነት ነገ...
28/06/2025

ገዳይ አሻንጉሊቶች
፨፨፨፨
ተጫዋች ነው ። እረፍት የለሽ ። ደፋር ነው ። ወጣቶች እወዳለሁ ፣ አእምሮዬን ያሠሯታል ይላል ። ምንም ይሁን ምን መጫወቻ መስራት የምፈልገው ። ለምንም አይነት ነገር ይዋል ፣ የእኔ መጨረሻ መጫወቻዎችን መስራት ነው ይላል ። አብረሃም ከሪም ።
የዛሬ 75 ዓመት ግድም በኢራቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ተጀመረ ። ይህ እንቅስቃሴ የአረብ ብሔረተኝነት ነበር ። የ1948 ዓ.ም የእስራኤል ዳግም ምጽኣት ተከትሎ ይህ የአረብ ንቅናቄ በረታ ። በተለይም ቀደምት ክርስቲያኖች (አሲርያን አይሁዶች) ላይ ከፍተኛ ጥቃት ይፈጸም ጀመረ ። ነገሮች እየተባባሱ ሄደው አይሁዶች ከሥራ ፣ ከንግድ ፣ ከህዝባዊ እንቅስቃሴ በይፋ ታገዱ ። ነገሮች ከፉ ።
የአሲርያን አይሁዶች በኢራቅ እህል ውሃቸው አለቀ ። ከናዚ ጭፍጨፋ በሗላ ዳግም ሌላ የክፋት አረንቋ ውስጥ ዳግም ላለመግባት የቆረጡበት ነው ።
በዘመቻ እዝራና ነህሚያ 120 ሺ ኢሲርያን አይሁዶች ከኢራቅ ወደ እስራኤል ተጋዙ ።
በ1951 እ.ኤ.ኣ ወደ እስራኤል ከነጎዱት መካከል አብረሃም ካሪም እና ቤተሰቦቹ ነበሩ ። አብረሃም እስራኤል ሲደርስ 14 ዓመቱ ነበር ። ባለልዩ ክህሎቱ አብረሃም ፣ ትንንሽ የአውሮፕላን ሞዴሎች እየሠራ ይጫወት ነበር ።
አይሁዳውያን የሥርየት ሳምንት(ዮም ኪፑር) የሚሉት በዓል አለ ። በመስከረም ወር መጨረሻ ወይም ጥቅምት መጀመሪያ ላይ ይውላል ። በዚህ ሳምንት ውስጥ ፀሎት ፣ ፆም ፣ ፈጣሪን ማወደስ ፣ ባስ ሲልም ምንም አይነት ሥራ አይሰሩም ። የመጨረሻው እለትም ለ24 ሠዓት ፆመውና ከሥራ ታቅበው የሥርየት ቀን በዓልን ያከብራሉ ።
ታዲያ በዚህ ቀን 1973 እ.ኤ.ኣ ግብጽና ሦሪያ በቀጥታ ፣ ሌሎች አረብ ሀገራት በድጋፍ የተሳተፉበት አስደናቂ ጥቃት እስራኤል ላይ ፈጸሙ ። የግብጽ ጦር የስዌዝን ሸጥ ተሻግሮ ፣ እስራኤል ትመካባቸው የነበሩ ምሽጎችን ጥሶ ገባ ።የሦሪያ ሠራዊት በአስደናቂ ፍጥነትና ብዛት የጎላን ተራራ ሽቅብ ወጣ ።
የእስራኤል ጦር ለዮም ኪፑር በዓል ወደ ቤተሰቦቻቸው በተመለሱ ወታደሮች ምክንያት ተመናምኖ ነበር ። በፍጹም ሊቆጣጠራቸው አልቻለም ።ለእስራኤል ዱብ እዳ ነበር ፣ ዓለምም ተገርሞ ።
የዚህ ግዜ ነበር የእስራኤል የጦር አባል የነበረው አብረሃም ከሪም ከመጫወቻዎቹ ጋር ወደ መድረኩ የመጣው ። አብረሃም መጫወቻ ብሎ የሚጠራቸው ፣ ዛሬ ድሮን የሚምንላቸው በራሪ አካላት የመጀመሪያ ሞዴሎች ነበር ። በዮም ኪፑሩ ጦርነት የአብረሃም መጫወቻዎች የጠላትን ቦታ ለመለየት ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል ።
ከዚህ ጦርነት በሗላ አብረሃም ከሪም ፣ ወደ አሜሪካ በመጓዝ የራሱን ድርጅት አቋቋመ ። በዚያም GNAT-750 የተሰኙ ሠው አልባ በራሪ አካላትን ፈለሰመ ። እነዚህ በራሪ አካላት MQ-1 Predator የተሰኙ የመጀመሪያው የጦር መሳሪያ የታጠቁ ድሮኖች ቀዳሚ ሞዴሎች ነበሩ ። የአብረሃም መጫወቻ የመሥራት አባዜ ፣ ዛሬ የዓለም አቀፍ የውጊያ መርሆችን የለወጡ ሆኖነዋል ። አብረሃም ካሪም በነዚህ ፈጠራዎቹ ምእንያት " የድሮን አባት " የሚል ሥያሜ ተሠጥቶታል ። ዛሬም በ88 ዓመቱ በአሜሪካ ይኖራል ።

የተወለደችው በጎንደር፣ ደራ ፎገራ አውራጃ፣ ልዩ ስሟ ሀሙሲት በምትባል አነስተኛ መንደር ነው። በቤተሰቦቿ የሥራ ዝውውር ምክንያት ለአጭር ጊዜ አሰላ ከዛም አዲስ አበባ ኖራለች። በትምህርቷ በ...
25/06/2025

የተወለደችው በጎንደር፣ ደራ ፎገራ አውራጃ፣ ልዩ ስሟ ሀሙሲት በምትባል አነስተኛ መንደር ነው። በቤተሰቦቿ የሥራ ዝውውር ምክንያት ለአጭር ጊዜ አሰላ ከዛም አዲስ አበባ ኖራለች። በትምህርቷ በጣም ጎበዝ (ቀለም) ከሚባሉት ተማሪዎች ተርታ የምትመደብ ተማሪ ነበረች።

ለሙዚቃ በነበራት ከፍተኛ ፍቅርና ፍላጎት ድምፃዊ ለመሆን ወደ ፖሊስ ኦርኬስትራ በመሄድ ያደረገችው የመጀመሪያ ሙከራ "ድምፃዊ መሆን አትችይም" በሚል መራር ውሳኔ ተደመደመ።

እንደማስተዛዘኛ ግን በተወዛዋዠነት እድሏን እንድትሞክር ተፈቅዶላት ፖሊስ ኦርኬስትራን ለ7ወር በተወዛዋዥነት በነፃ በማገልገል ኪነጥበብን ተቀላቀለች።

ከ7 ወር ግልጋሎት በኋላም በነፃ ዝውውር ወደ አንጋፋው የሀገር ፍቅር ቲያትርቤት በመዘዋወር ከ1965 እስከ 1967 ዓ.ም በተወዛዋዠነት አገለገለች።

በዚህ እልህ አስጨራሽና ተስፋ አስቆራጭ ሂደት ሙያዋን የጀመረችው አይበገሬዋ ድምፃዊት የመጀመሪያ የሙዚቃ ሸክላዋን በተመለከተ አሳታሚው የታንጎ ሙዚቃ ቤት ባለቤት ባንድ ወቅት እንዲህ በሚል ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

"አስቴርን በሸክላ ለማስቀረፅ ስመርጣት ድምጿ አይሰማም ከሚል ስጋት "ይቅርብህ" ያሉኝ ሰዎች ብዙ ነበሩ። እኔ ግን ቁጥር 1 ስራዋን በድፍረት አሳትሜ አወጣሁት። ያው እንደተፈራውም ተቀባይነቱ ቀዝቃዛ ነበረ። ሰዎችን ስጠይቃቸው "ድምጿ ጥሩ ነው ምን እንደምትል ግን አይሰማም "ይሉኝ ነበር።

እናም አስቴርም በወቅቱ "በቃ እኔ ሙዚቃ አይሆንልኝም" ብላ ተስፋ ቆረጠች። እኔ ግን እሷ ትልቅ ቦታ የምትደርስ ድምፃዊ እንደምትሆን እርግጠኛ ስለሆንኩኝ እልህ ውስጥ ገብቼ አስቴርንም አበረታትቼ ፣ የድርሰት ማጥኛ ቤት አዘጋጅቼ ፤ ውብሸት ፍሰሀን ጨምሬ ረጅም ጊዜ በፈጀ ጥናት በባህል መሳሪያዎች የታጀበ ስራቸውን አሳትሜ አወጣው።

ተቀባይነቱ ዳር ከዳር ከመሆኑም በላይ ያኔ ያልተደመጠው የመጀመሪያ ስራዋ ሁሉ እንደገና እንደ አዲስ ይፈለግና ይሰማ ጀመር። ሀገሩ ሁሉ አስቴር ይል ጀመር።" በማለት ያስታውሰዋል ኘሮዲውሰር አሊ አብደላ፤ የታንጎ ሙዚቃ ቤት ባለቤት።

በዚህ መልኩ የአይበገሬነት ጉዞዋን የጀመረችው አስቴር አወቀ ግማሽ ክፍለን ዘመን በሚጠጋው የሙዚቃ ዘመኗ ...

አንድ የሸክላ ሙዚቃና 25 የሙዚቃ ካሴቶችን በግሏ፣ አንድ የሙዚቃ ካሴት ከድምፃዊ ውብሸት ፍስሀ ጋር በጋራ፣ ከድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ ጋር" መች እንዲህ "የተሰኘ አንድ ዜማ በቅብብል፣ "እንኖራለን ገና" በሚል በኤች አይ ቪ ዙሪያ የተሰራ የጋራ አልበም፣ ለሚሊንየም የተጫወተችው ነጠላ ዜማ፣ የኛ ከተባሉ የሙዚቃ ቡድኖች ጋር በጋራ አንድ ዜማ ተጫውታለች።

አስቴር በስራዋ የሀገሯን ሰዎች ብቻ ሳይሆን የውጭ ሀገር ሰዎችን ጆሮዎችም የሳበች ሲሆን ከሲቢኤስ (CBS) ኮርፖሬሽን ጋር የሰባት አመት ኮንትራት እንደነበራት ተገልፇል። በተመሳሳይም ከሌላ ከእንግሊዝ ሀገር ካምፓኒ ጋር ሌላ ኮንትራት ተዋውላ ስራዎቿን አበርክታለች።

በታዋቂው ታይም (TIME) መፅሄት ላይ አዲስ አይነት የሙዚቃ ስልት ዘርፍ ትልቅ አድናቆት እና ክብር ተሰጥቷታል። ከዚህም ባሻገር "ካቡ" የተሰኘው አልበሟ በፈረንጆች አቆጣጠር በ1990 በ "CMJ New Music Charts" ላይ ለአራት ሳምንታት ከፍተኛ ቦታ (Top Position) ላይ እንዲሁም በ "Billboard's World Music Charts" ላይ ለአስር ሳምንታት (Top Ten of Billboard's World Music Charts) ላይ ቆይቷል።

አስቴር ወደ ኢትዮጵያ መጥታ ትልልቅ የሙዚቃ ዝግጅቶችን በጃንሜዳ፣ አዲስ አበባ ስታድየም፣ ሸራተን አዲስ እና ሚሊኒየም አዳራሽ አድርጋለች። ከዚህ ባሻገር በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለውን የረሃብ አደጋ ሰለባዎች ለመርዳት በተደረገው ጥረት ወደ ሃገሯ በመምጣት በሙያዋ አስተዋፅኦ አበርክታለች።

የራስሽን ዘፈን ስትሰሚ ምን ይሠማሻል ተብላ ተጠይቃ "ተለዋዋጭ ነው፣ በወጣትነት ጊዜዬ በጣም አፍር ነበር፤ የኔን ዘፈን ካዘፈንሽ ያንቺ መኪና ውስጥ አልገባም ነበር፣ የኔን ዘፈን ካዘፈንሽ እቤትሽ አልመጣም ነበር። ምክንያቱን ሁሌም በሰማሁ ቁጥር ይህን እንዲህ ማድረግ ነበረብኝ የምላቸው ስሜቶች ይሰሙኝ ነበር።" ብላለች።

አስቴር ራሷን "አስቴር አወቀ በጣም ደግ፣ ስስ ቆዳ ያላት እና ትልቅ ለመሆን የምትፈልግ ሴት ናት። መፈቀርም ማፍቀርም የምትፈልግ ናት። ሌላ ትርጉም ሊሰጣት አይገባም ከተፈቀረች ይበቃታል። ሌላ ነገር አትፈልግም" ብላ ትገልፃታለች።

አስቴር አወቀ አንድ ሴት ልጅ ያላት ሲሆን የግል ህይወቷን ከሰው ሸሸግ አድርጋ የምትኖር እና ከአደባባይ ይልቅ የግል ሰው እንደሆነች፣ ትልቅ የመድረክ ፍርሃት እንዳለባትም ትናገራለች።

ባለድንቅ ተሰጥኦዋ እና እንደ ህፃን ልጅ የቅን ልብ ባለቤቷ አስቴር አወቀ

* የዜማ ደራሲ
* የግጥም ደራሲ
* በቅንብር የምትሳተፍ
* የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች

በተጨማሪም ኑሮዋን በአሜሪካን ሀገር ካደረገች ጀምሮ ደግሞ የተዋጣላት ዲዛይነር በመሆን ለረጅም አመት የሀገሯን ባህል አስተዋውቃለች። መድረክ ላይ የምታደርጋቸው ውብ የባህል ልብሶች በራሷ ዲዛይን የተደረጉ ናቸው።

አሁን የደረሰን መረጃ‼️የጌታቸው እንቅስቃሴ  ለመግታት ጦርነት መለኮስ።▱▱▱▱▱▱▱▱▱የህወሓት አመራሮች በዚህ ሰዓት ስብሰባ ላይ መሆናቸው የደረሰን መረጃ ያሳያል። አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ሑመ...
25/06/2025

አሁን የደረሰን መረጃ‼️
የጌታቸው እንቅስቃሴ ለመግታት ጦርነት መለኮስ።
▱▱▱▱▱▱▱▱▱

የህወሓት አመራሮች በዚህ ሰዓት ስብሰባ ላይ መሆናቸው የደረሰን መረጃ ያሳያል። አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ሑመራ መጓዛቸውን ተከትሎ በህወሓት ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥ የተፈጠረ ሲሆን አሁን በዚህ ሰዓት ሰብሰባ እያካሄዱ መሆኑን እና አቶ ጌታቸው ረዳ የተፈናቃዮች ለመመለስ እያደረጉት ያሉትን እንቅስቃሴ ለማክሸፍ ጦርነት መጀመር አለብን በማለት መወሰናቸው ምንጫችን ገልፀዋል። እንደምንጫችን ገለፃ ከሆነ ጦርነቱን መቼ ይጀመር የሚለው እየተወያዩ ነው።

ትህነግ ትግራይን ዳግም ወደ ማያባራ ጦርነት እየወሰዳት ነው።

24/06/2025

ኢትዮጵያ በመጪው አዲስ ዓመት በ 3 ቢሊየን ዶላር (420 ቢሊየን ብር) ግዙፍ የማዳበሪያ (Fertilizer ) ማምረቻ ኢንደስትሪ ግንባታ ታስጀምራለች ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ (ሌላኛው ህዳሴ) በመባል የተሰየመው ትልቅ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ለማዳበሪያ ከነ ማጓጓዣው በየአመቱ የምታወጣውን ወደ 2ቢሊየን ዶላር የተጠጋ ወጪ ያስቀራል የተባለው ፋብሪካ በኢትዮጵያ መንግስትና በአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሃብቱ አሊኮ ዳንጎቴ ትብብር (Joint Venture) እንደሚሰራ ተነግሯል።

በ 3 ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ኢትዮጵያ ለማዳበሪያ የምታወጣውን እጅግ በርካታ ወጪና አሰልቺ የመርከብ ሎጀስቲክ መጉላላቶችን አስቀርቶ በዛውም ገበሬው እንደልብ በቅናሽ ዋጋ ማዳበሪ እንዲያገኝ በማድረግ የኢትዮጵያን የግብርና ምርት ወደ ልዩ ከፍታ ይወስዳል ተብሏል።

ኢራን ዙሩን አክርራዋለች ኢራን ምሽቱን  ወደ ተለያዩ የአረቢያን ገልፍ ሃገራት ማለትም  ኳታር፣ባህሬይን፣ኢራቅ   የባላስቲክ ሚሳኤሎችን አስወንጭፋለች የገልፍ ሃገራት  አብዛኞቹ  የአየር ክል...
23/06/2025

ኢራን ዙሩን አክርራዋለች
ኢራን ምሽቱን ወደ ተለያዩ የአረቢያን ገልፍ ሃገራት ማለትም ኳታር፣ባህሬይን፣ኢራቅ የባላስቲክ ሚሳኤሎችን አስወንጭፋለች የገልፍ ሃገራት አብዛኞቹ የአየር ክልል በረራ ተቋርጦ ተዘግቷል ።
ኢራን ሚሳኤሎቹን የአሜሪካ ቤዝ ይገኙባቸዋል ወደ ተባሉ የወታደራዊ ጣቢያዎች ነው የተኮሰችው ።
ይህ የነዳጅና የበርካታ ንግድ ማዕከላት አከባቢዎች ወደ ሆኑት ሀገራት የተተኮሰው ሚሳኤል ቀጠናውን ወደ ለየለት ጦርነት እንዳያስገባ ስጋት ፈጥሯል።

🈲ሜጀር_ጀኔራል_ረጋሳ_ጂማ➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺  #ጀግናው ከፍተኛ መኮንን በኢሉባቦር ክ/ሀገር የተወለዱ ሲሆን የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተወልደው ባደጉበት ከተማና  በአዲስ አ...
20/06/2025

🈲ሜጀር_ጀኔራል_ረጋሳ_ጂማ
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
#ጀግናው ከፍተኛ መኮንን በኢሉባቦር ክ/ሀገር የተወለዱ ሲሆን የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተወልደው ባደጉበት ከተማና በአዲስ አበባ ተከታትለው አጠናቀዋል።በ1944 ዓ.ም ክቡር ዘበኛ ጦር ት/ቤት በመግባት ከ3ኛው ዙር እጩ መኮንን ተመራቂዎች አንዱ ነበሩ።

#ከፍተኛ መኮንኑ የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በኦጋዴን ግንባር የሻለቃ አዛዥ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ሀገራችንን ወክሎ በኮንጎና በኮርያ ዘምቶ ግዳጁን ከተወጣው የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት አንዱም ናቸው።

#ጄኔራል ረጋሳ በ1970 ዓም ግብረ ኃይሎች በተቋቋሙበት ጊዜ የ501ኛ ግብረ ኃይል አዛዥ በመሆን ከጎንደር ተነስቶ በሁመራ ተሰነይ ባሬንቱ የገባው 3ኛ ክፍለን ጨምሮ 7ኛ ክፍለ ጦርም የዚሁ ግብረ ኃይል አካል ነበር።በአፍአበት ግንባር 508 ግብረ ኃይልን በአዛዥነት ከመምረታቸውም በላይ የሁአሠ ምክትል አዛዥና አዛዥነትም ሠርተዋል።

#ከሁአሠ አዛዥነት በኋላም በገነት ጦር ትምህርት ቤት አዛዥነትና በሦአሠ አዛዥነት እናት አገራቸውን በጀግንነት ያገለገሉ ሲሆን በሠራዊቱ ዘንድም እጅግ ተወዳጅ የሠራዊቱን አባላት " ልጆቼ !" እያሉ ፍቅር የሚሰጡ በመሆናቸው ሠራዊቱም በአባትነት ሥሜት እያከበራቸው አባታችን ይላቸው ነበር

#በ1975 ዓ.ም በተለይ ከቀይ ኮከብ ዘመቻ በኋላ ለተቋቋመው የመንጥር ዕዝ አዛዥ በመሆን በምዕራብ ከረን ከተማ በምትገኘው መለብሶ ወረዳ ከፍተኛና ጠንካራ ምሽግ በመስራት የጠላትን ተደጋጋሚ ጥቃት በማክሸፍ ወደር የሌለውን የአመራራር ብቃታቸውን አስመስክረዋል። በወቅቱም በዕዛቸው ስር ተዋቅረው የነበሩት 3ኛው አንበሳው ክ/ጦር፣የብረት አጠር የሚሰኘው 18ኛ ተራራ ክ/ጦርና፣2ኛው ዋሊያ ክ/ጦሮች ነበሩ።

#ከፍተኛ መኮንኑ የስርአቱን ለውጥ ተከትሎ ለእስር ተዳርገው ነበር።ጀግናው ከፍተኛ መኮንን በእስር ላይ እነዳሉ በገጠማቸው የጤና መታወክ ሕይወታቸው አልፏል።

#ክብር ለአንዲት እናት ሀገር ሉአላዊነት ለተዋደቁ ጀግኖቻችን!!!

©️ ዳንኤል እንግዳ

Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም

"በከፊል ፖለቲከኛ፤በከፊል አሸባሪ የሚባል ፖለቲካ በአለም ላይ ታይቶ አይታወቅም!!ከመረቁ አድርግልኝ ከስጋው ጾም ነኝ አይነት ፖለቲካ አይሰራም!! ሲመች ሲመች በሰላም ሳይሆን ደግሞ በሃይል ...
20/06/2025

"በከፊል ፖለቲከኛ፤በከፊል አሸባሪ የሚባል ፖለቲካ በአለም ላይ ታይቶ አይታወቅም!!ከመረቁ አድርግልኝ ከስጋው ጾም ነኝ አይነት ፖለቲካ አይሰራም!! ሲመች ሲመች በሰላም ሳይሆን ደግሞ በሃይል የሚባል ነገር የለም!!"

ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ(ዶ/ር)

መደመር and ብልፅግና *************👉 መደመር አዲስ የፖለቲካ paradigm ነው፡፡👉 ብልፅግና ያን paradigm ተሸክሞ የሚያስፈፅም ስብስብ ነው፡፡ ሃይል ነው ፓርቲ ነው፡፡👉 መደ...
17/06/2025

መደመር and ብልፅግና
*************
👉 መደመር አዲስ የፖለቲካ paradigm ነው፡፡
👉 ብልፅግና ያን paradigm ተሸክሞ የሚያስፈፅም ስብስብ ነው፡፡ ሃይል ነው ፓርቲ ነው፡፡
👉 መደመር ማእቀፍ ነው፡፡ ብልፅግና ይዘት ነው፡፡
👉 መደመር container ነው፡፡ ብልፅግና content ነው፡፡
👉 ኮንቴይነር ከኮንቴንቱ ወይም እኩል ወይም የላቀ መሆን አለበት፡፡
👉 መደመር አቅጣጫን ይወስናል፡፡ ብልፅግና ግን መዳረሻን ይወስናል፡፡
👉 መደመር direction ብልፅግና destination ይወስናል፡፡
👉 ለዚህ ነው መደመር መንገዳችን ብልፅግና መዳረሻችን የምንለው፡፡
👉 መደመር ፍልስፍና ነው፡፡ ፓርቲ ግን ክዋኔ ነው፡፡
👉 ይሄኛው theory ይህኛው practice ነው፡፡
👉 መደመር ቴዎሪውን ያወራዋል፡፡ ብልፅግና ይኖረዋል ይሰራዋል፡፡

Address

Adama
Shewa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሌተ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አድናቂ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የሌተ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አድናቂ:

Share