Fekadu Zeleke

Fekadu Zeleke delivering factual information to people

የ"ገብረ ሰላመ በመስቀሉ" በዓል በጉራጌ ዞን በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በድመቀ...
11/04/2026

የ"ገብረ ሰላመ በመስቀሉ" በዓል በጉራጌ ዞን በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በድመቀት ተከናወነ።

እንኳን ለብርሃነ ተንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን
Info credit GZCD

  ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ በፈጣሪ መልካም ፈቃድ እየተፋጠነ ይገኛል። ሁላችንም በያለንበት የምንችለው አስተዋጽኦ በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን ጥረት እናድርግ!!
06/03/2026

ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ በፈጣሪ መልካም ፈቃድ እየተፋጠነ ይገኛል።
ሁላችንም በያለንበት የምንችለው አስተዋጽኦ በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን ጥረት እናድርግ!!

ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ የሆነው ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ የኢት/ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምንድብር ሀገረ ስብከት የምታደርገው ጥረት እጅግ የሚደነቅ ነው! እጅግ በ...
12/02/2026

ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ የሆነው ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ የኢት/ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምንድብር ሀገረ ስብከት የምታደርገው ጥረት እጅግ የሚደነቅ ነው! እጅግ በጣም እናመሰግናለን!!

  ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ  ወይይት እየተካሄደ ይገኛል።
07/02/2026

ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ ወይይት እየተካሄደ ይገኛል።

የአንትሮሽት (የእናቶች ቀን) በጉራጌ ዞን በአበሽጌ ወረዳ በድምቀት ተከብሯል።ክብር ለትውልድ ቀጣይነት ከፈጣሪ ቀጥሎ ትልቁን ሚና ለሚወጡት እናቶች ይሁን!!
27/01/2026

የአንትሮሽት (የእናቶች ቀን) በጉራጌ ዞን በአበሽጌ ወረዳ በድምቀት ተከብሯል።
ክብር ለትውልድ ቀጣይነት ከፈጣሪ ቀጥሎ ትልቁን ሚና ለሚወጡት እናቶች ይሁን!!

የዘንድሮ ነቖ የልጃገረዶች በዓል በዞኑ በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚከበር የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ።በዞኑ የተቀዛቀዙና እየጠፉ የነበሩ  የጉራጌ በህላዊ  እሴቶችን...
22/01/2026

የዘንድሮ ነቖ የልጃገረዶች በዓል በዞኑ በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚከበር የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ።

በዞኑ የተቀዛቀዙና እየጠፉ የነበሩ የጉራጌ በህላዊ እሴቶችን በመታደግና በማልማት በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቁ በሚደረገው ጥረት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት ተጠቁሟል።

የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመርጋ እንዳሉት የጉራጌ ማህበረሰብ ከጥንት ጀምሮ ለሴቶች የነበረውን አክብሮትና ነጻነት ማሳያ ነቖ/ረቐ ወይም አስትረ የልጃገረዶች በዓል አንዱ ነው።

ፈረንጆች March 8 mother's day እና Girl's day የሚባሉ ቀናት ባልታሰቡበት ዘመን አስቀድሞ ጉራጌ አስቀድሞ ለልጃገረዶችና ለእናቶች ነጻነት የሰጠ ማህበረሰብ መሆኑን የታሪክ ድርሳናት እንደሚያስረዱ አመላክተዋል።

ነቖ/ረቐ ለማህበረሰቡ ካለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው በተጨማሪ ልጃገረዶች ነጻነታቸውን የሚያዉጁበት፣ የሚገናኙበት፣ የሚተያዩበት፣ አብሮነታቸውን የሚጠናከርበትና ለወደፊት ተስፋ የሚሰንቁበት በዓል ነው።

ከዚህም ባለፈ ሴቶች በራስ የመተማመን ብቃታቸው ከፍ የሚልበት፣ ከቤተሰብ ስጦታ የሚያገኙበት፣ የእርስ በእርስ መስተጋብር የሚጎለብትበትና ህብረብሔራዊነት የሚጎለብትበት በዓል በመሆኑ ፋይዳው ከፍተኛ ነው ያሉት።

ልጃገረዶች በየአካባቢያቸው በተለያዩ ስራዎች ሲደክሙ የነበሩትን የሚያርፉበት፣ የሚጨዋወቱበትና የሚዝናኑበት በዓል መሆኑን ያነሱት ኃላፊዋ ይህን እሴት ከጊዜ ወደ ጊዜ በቴክኖሌጂ፣ በአለም አቀፍ የባህል ወረራና በሌሎችም ምክንያቶች እየተቀዛቀዝ መምጣቱን አንስተዋል።

ይህንን ተከትሎ በዞኑ ባለፉት 4 አመታት የልጃገረዶች በዓል ነቆ/ረቐ እንዲያንሰራራ በእዣና ወረዳና በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ሲከበር እንደነበር አንስተው ይህ በዓል ወጥነት ባለው መልኩ በዞኑ በሁሉም መዋቅር እንዲከበር እቅድ በማቀድ ከታችኛው መዋቅር ጋር መግባባት መቻሉን ገልጸዋል።

በዞኑ ዘንድሮ በተለየ መልኩ በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የነቆ/ረቐ የልጃገረዶች በዓል ከጥር 15 ጀምሮ እስከ ጥር 30 ድረስ በትምህርት ተቋማት፣ በተመረጡ ቀበሌዎችና በማዕከል ደረጃ እንደሚከበርም ወይዘሮ መሰረት አስረድተዋል።

በዞኑ በዘንድሮ አመት ከ2 ሺህ በላይ ልጃገረዶች በበዓሉ እንደሚሳተፉ ያነሱት ኃላፊዋ ይህን እሴት ጎልቶ እንዲወጣ ባለሀብቶችና ሌሎችም እገዛ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።

በዞኑ መምሪያው የተቀዛቀዙና የጠፉ የጉራጌ ማህበረሰብ እሴቶችን እንዲያንሰራሩ፣ እንዲለሙና እንዲተዋወቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እነዚህ እሴቶችን ጎልተው እንዲወጡ በቀጣይ በጥናትና ምርምር በማስደገፍ በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲተዋወቁ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እንደሚሰራ አመላክተዋል።

ይህ በዓል ከእምነት ጋር የማያያዝ ዝንባሌዎች እየተስተዋለ መሆኑን አንስተው ይህም የተዛቡ አመለካከቶችን ማስተካከል ላይ ወላጆችና ሌሎችም የበኩላቸውን ድርሻ መውጣት እንዳለባቸው አስረድተዋል።

እንደ ዞኑ ኮሚዩኒኬሽን ዘገባ የባህል ቱሪዝም ጽህፈት ቤቶች ከትምህርት መዋቅር ጋር በመቀናጀት ለልጃገረዶች በታሪካዊ አመጣጡ ዙሪያ ግንዛቤ የመፍጠር፣ ልጃገረዶች የመመልመል፣ ግጥሙ እንዲያጠኑና እንዲለማመዱ ማድረግ እንዳለባቸው አውስተው በተጨማሪም በዓሉ በጀፎረ፣ በጎጆ ቤትና በሌሎችም በማክበር የጉራጌ እሴቶችን ማስተዋወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የጥምቀት በዓል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ  ስነ-ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ነው።
19/01/2026

የጥምቀት በዓል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ነው።

የከተራ በዓል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርዓት በድምቀት እየተከበረ ነው። ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ማደሪያቸው ጥምቀተ ባህር  በመሄድ ላይ ናቸው።እንኳን አ...
18/01/2026

የከተራ በዓል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርዓት በድምቀት እየተከበረ ነው።

ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ማደሪያቸው ጥምቀተ ባህር በመሄድ ላይ ናቸው።
እንኳን አደረሳችሁ!!

ርዕሰ መሰተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ ( ዶ/ር ) የወልቂጤ ዩኒቪርስቲ  ያስገነባዉን 'ማዕከላዊ  የአስተዳደር 'ሕንፃ መርቀዉ ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ
18/01/2026

ርዕሰ መሰተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ ( ዶ/ር ) የወልቂጤ ዩኒቪርስቲ ያስገነባዉን 'ማዕከላዊ የአስተዳደር 'ሕንፃ መርቀዉ ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ

 #ህፃናት በጅብ እየተበሉ ነው   #ወላጆች ጥንቃቄ ለልጆቻችን እናድርግ !!በጉራጌ ዞን እምድብር  ከተማ የጭሬት መንደር ልደቱ ታረቀኝ ፀጋዬ የሚባል ልጅ የገና ጨዋታ እየተጫወተ እያለ በጅብ...
09/01/2026

#ህፃናት በጅብ እየተበሉ ነው #ወላጆች ጥንቃቄ ለልጆቻችን እናድርግ !!

በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ የጭሬት መንደር ልደቱ ታረቀኝ ፀጋዬ የሚባል ልጅ የገና ጨዋታ እየተጫወተ እያለ በጅብ መበላቱ ተሰምቷል።

#በተለያዩ አካባቢዎች ባልተለመደ ሁኔታ #ጅብ በተለያየ ጊዜ ሰው እየበላ መሆኑን ይታወቃል።ከዚህ መነሻም ጥቃቱም ለመከላከል እያንዳንዱ ወላጆች ልጆቻቸው በምንም ሁኔታ ከቤት ወደ ውጪ በሚልኩበት ጊዜ ለብቻቸው ወይም አላዋቂ ሰው መላክ የለባችሁም።

☞ #በተለይም ህፃናትና ሴቶችን ለተለያየ ውሃ ለመቅዳት፣ለሸመታ ወደ ገበያ፣ እንጨት ለቀማና ሳር አጨዳ በሚሄዱበት ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል

☞ #ልጆቻችሁ ወደ ትምህርት ቤት ሲሄዱና ሲመለሱ ወላጆች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። መረጃው የደስታ ጊዜያቱ ነው

Address

Wolkite
Shewa

Telephone

+251913084971

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fekadu Zeleke posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Fekadu Zeleke:

Share