Fitsum Tesfaye - ፍፁም ተስፋዬ

Fitsum Tesfaye - ፍፁም ተስፋዬ Er-beet Tube

ይህ ለእኛ እንደ ሰበር ዜና ይቆጠራል!የእኛም ምኞት፣ ህልማችን ሆነው የነበረው ይህ ነበረ። እሱም ትልቁ የሃዲያ ህዝብ እና አመራር አንድ ሆነው፣ አንድ ተነግረው ለአንድ ዓለማ፣ ለአንድ ልማት...
28/06/2025

ይህ ለእኛ እንደ ሰበር ዜና ይቆጠራል!

የእኛም ምኞት፣ ህልማችን ሆነው የነበረው ይህ ነበረ። እሱም ትልቁ የሃዲያ ህዝብ እና አመራር አንድ ሆነው፣ አንድ ተነግረው ለአንድ ዓለማ፣ ለአንድ ልማት ለአንድ ሀገር መቆም አለበት የሚለው ጉዳይ ነበርን።

ለሀድያ ህዝብ አንድነት፣ ለሀድያ ህዝብ ልማት፣ ለሀዲያ ህዝብ እድገት ስናወራም እንደ ወንጀለኛ የተቆጠረነውም ይህ ነበር። ወንጀል እንደሰራን መጥሪያ በማውጣት ልንታሰር የተፈለገነውም ለእዚህ ዓለማ ነበረ። ይህ ዓይነት ስብስብ የናፈቅን፣ ያማረንም ነበረ።

በሀገራችን ደረጃ እንኳን በከፍተኛ ሁኔታ የገንዘብ ካፒታል ካሉት አካባቢዎች ውስጥ አንዱ የነበረው የሀዲያ ይህ ነው የማይባል የሚታይ ነገር ማዬት ያቃተን ህዝቡ፣ ወጣቱና አመራሩ አንድ ሆነው በመወያየት ችግሮችን መፍታት፣ መምከር ባለመቻሉ ነው።

አንድ ሀዲያን በሰፈር በጎሳ የመለያየት ስራዎች እየተሰራ በመቆየቱ ነው። አሁንም ጠንካራ ማህበር እንደነበረን መቀጠል ከፈለግን ይህ ዓይነት አንድነት መቀጠል አለበት።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ኢትዮጵያዊያን ይህንን በደንብ ማጤን አለብን!👌ምክንያቱም ስማችን በዓለም ሃያላን ሃገራት በተደጋጋሚ እየተነሳ ይገኛል። በባለፈው ትራምፕ " ግድቡን ያስገነባነው እኛ ነን" ብሏል። ዛሬ ደግም ...
25/06/2025

ኢትዮጵያዊያን ይህንን በደንብ ማጤን አለብን!👌
ምክንያቱም ስማችን በዓለም ሃያላን ሃገራት በተደጋጋሚ እየተነሳ ይገኛል። በባለፈው ትራምፕ " ግድቡን ያስገነባነው እኛ ነን" ብሏል።

ዛሬ ደግም የእስራኤል ፕሬዚዳንት "ኢትዮጵያ ልትጠፋ ነበር እኛ ታደግናት" እያለ ይገኛል።
ምን ልተኮስብን ታስበው ነበረ? ከየትኛው ሀገር ይሁን? የሚለው ግን ግልጽ አላደረገም።
ለማንኛውም ስማችን በተደጋጋሚ እየተነሳ ያለው እየተሻልን እና ተጽዕኖ እየፈጠርን ነው ያለነው ይመስለኛል። የዓለሙ ሃያላን ሃገራት የደከሙ ሀገራትን ስም በተደጋጋሚ የመጥራት አባዜ ብዙ አይታወቅም።

ለማንኛውም ገና ስለ ኢትዮጵያ ብዙ ከዓለም አንደበት የምንሰማው ይሆናል።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል...ስለዚች በላ 20 ሚሊዮን ድልድይ ጉዳይ በቅርቡ ቢቢሲ እና DW ሚዲያዎችም ይዘገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ይገኛል!ይህንን ልጅ በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ በቲክቶክ የማታውቁት...
22/03/2025

አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል...
ስለዚች በላ 20 ሚሊዮን ድልድይ ጉዳይ በቅርቡ ቢቢሲ እና DW ሚዲያዎችም ይዘገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ይገኛል!

ይህንን ልጅ በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ በቲክቶክ የማታውቁት ትኖራላችሁ ብዬ አላስብም። እጅግ በጣም ተገርመው " ምን ዓይነት ጉድ ነው? " በማለት መልክቱን አስተላልፏል።

"የዞኖችና፣ የወረዳዎች አመራሮች በመንገድ ላይ ዜብራ ቀለም ቀብታችሁ በሚሊዮኖች የተቀባ ነው በማለት በጋጋተ ታስመርቃላችሁ! " በማለትም አክሏል።

አሁንም ስለዚህ ድልድይ ጉዳይ እኛም በኢትዮጵያ ትላልቅ ሚዲያዎች ሰፋ ያለ ዘገባ የምንጠብቀው ይሆናል። ብቻም ሳይሆን ይህ ጉዳይ ፍትህ የሚያስጠይቅ በመሆኑ " ፍትህ ለህዝባችን " እንላለን።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ጀግጊቷ.. እንደዚህ የዓይነት ሴት የዓለማ ሴቶች በዚህ ዘመን እንደ ብርቅ ነገር ይቆጠራሉ..ተማሪ ኤርሳሜ ብርሃኑ በቴቦ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ፕሮግራም ...
22/03/2025

ጀግጊቷ..
እንደዚህ የዓይነት ሴት የዓለማ ሴቶች በዚህ ዘመን እንደ ብርቅ ነገር ይቆጠራሉ..

ተማሪ ኤርሳሜ ብርሃኑ በቴቦ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች አጠቃላይ የትምህርት መስክ መረጣ ከሁሉም ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች። ለቀጣይ ትምህርት ዘመን የMedicine የመማር እድሉንም አግኝታለች።

/ERSAME/ የስሟ ትርጉም በአማርኛ መልካም ዕጣ ወይም መልካም እድል በማለት ይተረጎማል..

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ኢትዮጵያ 15 ሚሊየን ዶላር ለሱዳን🇪🇹🤝🇸🇩የቢዝነስ ሳይኮሎጂ ምን ይላል" ሀብት በፍጥነት ወደ አንተ እንዲመጣ አመስጋኝ እና ለጋሽ መሆን ይጠበቅባሃል" ይላል። አንዳንድ ሰዎች "ኢትዮጵያ የተ...
15/02/2025

ኢትዮጵያ 15 ሚሊየን ዶላር ለሱዳን🇪🇹🤝🇸🇩
የቢዝነስ ሳይኮሎጂ ምን ይላል" ሀብት በፍጥነት ወደ አንተ እንዲመጣ አመስጋኝ እና ለጋሽ መሆን ይጠበቅባሃል" ይላል።

አንዳንድ ሰዎች "ኢትዮጵያ የተቸገረ ዜጎቿ እያሏት እንዴት እርዳታ ትሰጣለች? " የሚሉ ትችቶች አይጠፉም። ግን ኢትዮጵያ ዜጎቿ በቶሎ ከችግር እንዲላቀቁ ጠንክሮ መስራት እና የተቸገሩትን ጎረቤት ሀገራትን መደገፍ ይጠበቅባታል።

ኢትዮጵያ ለሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ 15 ሚሊየን ዶላር የለገሰች ስሆን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችም 200 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ለሱዳን ሰጥታለች።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ባልታወቀ መንስኤ የተቀሰቀሰው የእሳት ቃጠሎ አደጋ በሀዲያ ዞን ሻሾጎ ወረዳ በቻጎለ ቀበሌ 9 ቤቶችን  ሙሉ ለሙሉ አውድሟል።በሻሾጎ ወረዳ በቻጎለ ቀበሌ መንስኤ ባልታወቀ ሁኔታ የተቀሰቀሰው የ...
17/01/2025

ባልታወቀ መንስኤ የተቀሰቀሰው የእሳት ቃጠሎ አደጋ በሀዲያ ዞን ሻሾጎ ወረዳ በቻጎለ ቀበሌ 9 ቤቶችን ሙሉ ለሙሉ አውድሟል።

በሻሾጎ ወረዳ በቻጎለ ቀበሌ መንስኤ ባልታወቀ ሁኔታ የተቀሰቀሰው የእሳት አደጋ የስድስት አባወራዎች እና የአንድ እማወራ ዘጠኝ ቤቶችን ከነሙሉ የቤት ውስጥ እህልና ቁሳቁስ አውድሟል።

እንድሁም መነሻ ምክንያት ባልታወቀ የእሳት ቃጠሎ አደጋ በደደ ቀበሌ ሁለት ቤቶች በአደጋው ከጥቅም ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

የእሳት ቃጠሎው ባስከተለው አደጋ የጓሮ ፍራፍሬና አትክልት እንድሁም በቤቶች የተንጠለጠሉ የንብ ቀፎዎች ሙሉ ለሙሉ ወድሟል።

በመሆኑም ወቅቱ ደረቅ የአየር ሁኔታ የሚስተዋል እንደመሆኑ መጠን ህብረተሰቡ አስፈለጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል የሚል ጥሪ በሻሾጎ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አደጋ ስጋት መከላከል ዘርፍ ተላልፏል ስል የዘገበው
የሻ/ወ/መ/ኮ/ጽ/ቤት ነው።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ነፍስ ይማር!😥የድሬዳዋው የሀዲያ ድምቀትአቶ አርጋው በሆሳዕና ከተማ በአደባባይ ሰፈር ትላንት ማታ አሻም ሆቴል ጀርባ በወንበዴዎች ተገሎ አስክሬኑ ተጥሎ ተገኝተዋል!አቶ አርጋዉ የድሬዳዋ ነዋሪ...
17/01/2025

ነፍስ ይማር!😥
የድሬዳዋው የሀዲያ ድምቀትአቶ አርጋው በሆሳዕና ከተማ በአደባባይ ሰፈር ትላንት ማታ አሻም ሆቴል ጀርባ በወንበዴዎች ተገሎ አስክሬኑ ተጥሎ ተገኝተዋል!

አቶ አርጋዉ የድሬዳዋ ነዋሪ ሲሆን የሀዲያ ሆሳዕና እግርኳስ ወደ ፕሪሚየርልግ ለመግባት ውድድር በሚያደርግበት ወቅት በድሬደዋ የሀዲያ ተወላጆችን በመሰብሰብና በማስተባበር ከእስታዲየም ሞራል ድጋፍ ጀምሮ በመግባት እንዲሁም ዘንድሮ የሀዲያ ዘመን መለወጫ በዓል ያሆዴ ለመጀመሪያ ጊዜ በድሬዳዋ ከተማ እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጸኦም የነበረው።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

መልካም ዜና ✈️✈️በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ለአዉሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚሆን ቦታ ምልከታ ተደረገ በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ለአዉሮፕላን ማረፊያ ታሳቢ ተደርጎ ምልከታ...
19/12/2024

መልካም ዜና ✈️✈️

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ለአዉሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚሆን ቦታ ምልከታ ተደረገ

በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ለአዉሮፕላን ማረፊያ ታሳቢ ተደርጎ ምልከታ የተደረገበት ቦታ ላይ ሙያዊ ጥናት ተደረጎ በአጭር ጊዜ ግንባታ እንደሚጀምር ተገልጿል ።

በምልከታው የሀድያ ዞን አስተዳደሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ይርጋ ሀንድሶና ሌሎች የዞኑ አስፈፃሚ አካላት እንዲሁም የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ደዊት ጡምደዶ፣ የሌሞ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ ጨምሮ የፊት አመራር ተገኝተዋል ስል የዘገበው ሀድያ ቴሌቪዥን ነው።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

ምዝገባ ተጀምሯል👌👌ሰሞኑን በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የኢትዮጵያ ዜጎች በእንግልት በመደረጋቸው የይድረሱልን ጥሪ ስያሰሙ እንደነበረ ይታወሳል።አሁን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሊባኖስ አማ...
30/09/2024

ምዝገባ ተጀምሯል👌👌
ሰሞኑን በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የኢትዮጵያ ዜጎች በእንግልት በመደረጋቸው የይድረሱልን ጥሪ ስያሰሙ እንደነበረ ይታወሳል።

አሁን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሊባኖስ አማካኝነት ዜጎቻችን ለመታደግ ምዝገባ መጀመሩን እና ተመዝገብዎች ለምዝገባ ስመጡ ማሟላት ያለባቸውን መስፈርት በገፅ ላይ አስፍረው አግኝቸዋለሁ።

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

"የውክልና ጦርነት በሃገሬ እንዲሆን አልፈቅድም"  የሱማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ከአልጀዚራ ጋዜጠኛ ጋር ባደረጉት ንግግራቸው "ኢትዮጵያን ጦርነት መግጠም አንችልም አሉ" ብሏል። ኢት...
29/09/2024

"የውክልና ጦርነት በሃገሬ እንዲሆን አልፈቅድም" የሱማሊያ ፕሬዚዳንት
ሀሰን ሼክ መሃሙድ ከአልጀዚራ ጋዜጠኛ ጋር ባደረጉት ንግግራቸው "ኢትዮጵያን ጦርነት መግጠም አንችልም አሉ" ብሏል። ኢትዮጵያ ከሱማሊላንድ ጋር ያደረገችውን የወደብ ስምምነት በዲፕሎማሲ መፍታት ካልቻልን እና ቱርክ እያደራደረች ያለችው ድርድሩ ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን። ያሳይሆን ቀርተው የባህር በር ስምምነቱ ብተገበር እንኳን ከኢትዮጵያ ጋር አንዋጋም። የውክልና ጦርነት በሱማሊያ ምድር አይታሰብም ብሏል።

ኢትዮጵያ ብቻዋን አይደለችም ከኋላ በኢኮኖሚ ጠንካራ እና ሃያላን ሃገራትም አሏት። ግን ሃገራቶችን ለመጥቀስ አልፈለጉም።

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር 🇪🇹

@ፍፁም ተስፋዬ(Erbeeto)

Address

Hosanna
Shewa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fitsum Tesfaye - ፍፁም ተስፋዬ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Fitsum Tesfaye - ፍፁም ተስፋዬ:

Share