Adane Yisma Baruda Page/ አዳነ ይስማ ባሩዳ ፔጅ

  • Home
  • Adane Yisma Baruda Page/ አዳነ ይስማ ባሩዳ ፔጅ

Adane Yisma Baruda Page/ አዳነ ይስማ ባሩዳ ፔጅ " ሀይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን ማድረግ እችላለሁ::" ፊል 4:13

☞ ዳግመኛ የተወለደ አማኝ!!
☞ የወንጌል አገልጋይ!!
☞ የአንዲት ሚስት ባል!!
☞ የልጅ አባት!!
☞ የመንፈሳዊ መጽሐፍቶች ጸሐፊ!!
☞ ቴዎሎጂ ዲግሪ(EVANGLICAL CHRISTIAN UNIVERSTY)!!
ፔጁን ፎሎው፡ ላይክና ሼር በማድረግ መንፈስንና አዕምሮን የሚገነቡ አስደናቂ መልዕክቶችን ያገኙ ዘንድ እጋብዛችኃለሁ!!

24/07/2025

#እግዚአብሔር!!

☞እግዚአብሔር ነገሮችህን ሳይሆን እምነትህን ያያል
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
♦️እግዚአብሔር ከእኛ ነገር ይልቅ በእርሱ ዘንድ ያለን የእኛን እምነት ይፈልጋል።ያለ እምነት ጌታን ደስ ማሰኘት የማይቻል እንደሆነ ነው ከቅዱስ ቃል የምንረዳው።
👉“መጽሐፍም፦ አብርሃምም ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።”
— ያዕቆብ 2፥23

👉ሮሜ 4
20-21፤ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ እንጂ በአለማመን ምክንያት ።
22፤ ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
23፤ ነገር ግን፡— ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ እንጂ፤

♦️አዎ አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ የተባለው በእግዚአብሔር ላይ ያለው የተስፋ ቃሉን በማመኑ ነው።እግዚአብሔር በእኛ እምነት ይደሰታል፣በእርሱ የሚያምኑ አያፍሩም ተተብሏልና።
➣ችግር ልኖረን ይችላል
➣በሽታ ልሞከረን ይችላል
➣በእጦት ልንሰቃይ እንችላለን
➣ከሌሎች ተለይተን ተሰድደን ይሆናል
ይህ ሁሉ ባይኖረን እንኳ እግዚአብሔር ከዚህ ስቃይ በላይ ኃያል እንደሆነ በመረዳት በደስታ ልንውጥ ያስፈልገናል።
ለምሳሌ ዕንባቆምን ስንመለከት በወቅቱ የከበቡት ተግዳሮቶች በእግዚአብሔር ላይ ያለውን ትልቅ የእምነት ደስታውን ሊያሸረሸረው አልቻለምና።👇👇
👉ዕንባቆም 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ እኔ ሰምቻለሁ፥ ልቤም ደነገጠብኝ፤ ከድምፁ የተነሣ ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ፤ መንቀጥቀጥ ወደ አጥንቶቼ ውስጥ ገባ፤ በስፍራዬ ሆኜ ተናወጥሁ፤ በሚያስጨንቁን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ እጠብቃለሁ።
¹⁷ ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥
¹⁸ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።

👉ማርቆስ 2
3፤ አራት ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት።
4፤ ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡ፥ ነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ አወረዱ።
5፤ ኢየሱስም ሽባውን፡— አንተ ልጅ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ፡ አለው።

♦️እግዚአብሔር እናንተ ደካሞች ሸክም የከበደባችሁ ወደ እኔ ኑ ይላል።ይህ ማለት እኛ በራሳችን አቅም መፍታት ያቃተንን ነገር ሁሉ በእርሱ ላይ እንድንጥል ነው።ስለዚህ
➣ችግራችንን አንይ ➛አምላካችንን እንየው
➣ፈተና፣መከራ አያስጨንቀን➛በኢየሱስ እናምን
➣በያለቁብን ነገር ተስፋ አናቆርጥ➛በኢየሱስ እናምን
➣ዓላማው ላይ ቆመን ወደ ኢየሱስ ከቀረብን በእምነታችን ልክ እንድሁ መዳናችን ይሆናልና🙏
👉ማቴዎስ 9
2፤ እነሆም፥ በአልጋ የተኛ ሽባ ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፡— አንተ ልጅ፥ አይዞህ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ፡ አለው።
20፤ እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤
21፤ በልብዋ፡— ልብሱን ብቻ ሆነ፥ እድናለሁ፡ ትል ነበረችና።
22፤ ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና፡— ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ ፡ አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች።

♦️እግዚአብሔር የእኛን ነገር ጊዜ ሳይወስድ ልሰራና ልያስተካክለን ይፈልጋል::

23/07/2025

"ሀሰተኛ ነቢያት ጠንቋዮች ናቸው። ሐሰተኛ ነቢያትን በስም ጠርተን ማጋለጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነዉ!!"

ሐሰተኛ ነቢያትን በስም ጠርተን ማጋለጥ እንዳለብን መጽሐፍ ቅዱስ "አንድ ሐሰተኛ ነብይ ነበር" አላለም። ስሙን ጠርቶ #በርያሱስ ነው ያለው።
"ደሴቲቱንም ሁሉ እስከ ጳፉ በዞሩ ጊዜ፥ በርያሱስ የሚሉትን ጠንቋይና ሐሰተኛ ነቢይ የሆነውን አንድ አይሁዳዊ ሰው አገኙ፤" ሐዋርያት - 13፥6
ስለዚህ የሐሰተኞችን ስም መጥራትና ማጋለጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው።
ይህ በስም የተገለጸው ሐሰተኛ ነብይ ነው። ያ ማለት ሐሰተኛ ትንቢቶችን ተናግሮ ነበር ማለት ነው። በአጭሩ በስሙ የተጠቀሰው ግለሰብ ሐሰተኛ ነብይ ነው። ስለዚህ ሐሰተኛ ነቢያትን በስም ጠቅሶ ሐሰተኛ ማለት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው።

ሐሰተኛ ነቢያትን በስም ከመጥራትና ከማጋለጥ አልፎ የሐሰተኛ ነብይነታቸው እውነተኛው መገለጫ አላቸው። ይህም #ጠንቋዮች ናቸው። አዎ መጽሐፍ ቅዱስ ያውም በአዲስ ኪዳን ሐሰትን የተናገሩ ነቢያትን በጥሩ መገለጫ ይጠራቸዋል። ሐሰተኛ ነቢያት ጠንቋዮች ናቸው ይላል መጽሐፍ ቅዱስ!!

ስለዚህ ውሸት የተናገሩ ነቢያት (በብዙ እውነት መካከል ቢሆንም) ቀላቅለዋልና ጠንቋዮች ለማለት እንደ እግዚአብሔር ቃል ድፍረቱ አለን። በህይወቱ አንዴ እንኳን የሳተ ጠንቋይ ነው።

በዚህ ዘመን በእግዚአብሔር ስም አያለሁ እሰማለሁ ብሎ ስቶ፣ አስቶ የማያዉቅ ነብይ ታውቃላችሁ? ካለ ጠቁሙን፣ ከሌለ ግን ከነጨዋነቱ ጠንቋይ መሆኑን እንመን።

ማጠቃለያ፦ ሐሰተኛ ነብይ ስሙን ጠርተን ማጋለጥ፤ ሐሰተኛ መሆኑን ማሳየት፤ በዚህም በእግዚአብሔር ስም (በመንፈስ ቅዱስ ስም) ውሸትን ቀላቅሎ በመናገሩ ጠንቋይ እንለዋለን። ከሐሰተኛ ነቢያት ተጠበቁ፣ ከጠንቋዮች ተጠበቁ!!

22/07/2025


✅ የወንዝዳር ነው፦ ያለመልማልና (መዝ. 1፥2-3)፤
✅ የማር ወለላ ነው፦ ያጣፍጣልና (መዝ.118(119) 1031.3:2-3)
✅ጥሩ ውኃ ነው፦ ያረካልና (መዝ.22(23)፥2)
✅ መዶሻ ነው፦ ያደቃልና (ኤር.23፥29)
✅ እሳት ነው፦ ያጠራልና (ኤር.23፥29) →
✅ ብርሃን ነው፦ ያሳውቃልና (መዝ.118(119፥105)፤
✔እንጀራ ነው፦ ያኖራልና (ማቴ. 4፥4፤ ዘዳ. 8፥3)፤
✅ ራጅ ነው፦ ውስጥን ያሳያልና (ዕብ. 4፥12)
✅ዘር ነው፦ ያፈራልና (ሉቃ. 8፥4-15)፤
✅ወተት ነው፦ ያሳድጋልና (1ኛ ጴጥ. 2፥1)
✅፤ ሰይፍ ነው፦ ትጥቅ ነውና (ኤፌ. 6፥17)...።

 !!
22/07/2025

!!

21/07/2025

My Country!!

 !!☞ለወጣቶች የማስተላልፈው 10 ልብን የሚነኩ እና መራር ምክሮች እነሆ፡1. ጤናችሁን እንደ ውድ ንብረት ጠብቁት።በወጣትነት ጉልበት ተማምናችሁ ሰውነታችሁን ቸል አትበሉ።የምትመገቡት ምግብ፣...
19/07/2025

!!

☞ለወጣቶች የማስተላልፈው 10 ልብን የሚነኩ እና መራር ምክሮች እነሆ፡

1. ጤናችሁን እንደ ውድ ንብረት ጠብቁት።
በወጣትነት ጉልበት ተማምናችሁ ሰውነታችሁን ቸል አትበሉ።የምትመገቡት ምግብ፣ የምታደርጉት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና አጠቃላይ የአኗኗር ዘይቤ ለወደፊት ህይወታችሁ መሰረት ነው።ዛሬ የምትዘሩት የጤና ዘር፣ በዕድሜ ስትገፉ ፍሬውን ትቀምሳላችሁ።

2. ገንዘብን በጥበብ መያዝን ተማሩ።
ገንዘብ ነክ ትምህርት ለወደፊት የፋይናንስ ነጻነታችሁ ወሳኝ ነው። ገቢዎቻችሁን በአግባቡ መምራት፣ ቁጠባን ማዳበር እና ዕዳን ማስወገድ የፋይናንስ ደህንነታችሁን ያረጋግጣል።ብልህ የፋይናንስ ውሳኔዎች የተረጋጋ የወደፊት ህይወት መሰረት ናቸው።

3. በሙያችሁ ላይ በርትታችሁ ስሩ እና አዳዲስ ክህሎቶችን ለመማር አትስነፉ።
የ20ዎቹ ዕድሜ ለሙያ እድገት ወሳኝ ወቅት ነው።ጠንክሮ መስራት፣ አዳዲስ ክህሎቶችን መማር እና በስራ ቦታችሁ እድሎችን መጠቀም ለስኬታማ የሙያ ህይወት በር ይከፍታል። ስራችሁን አክብሩ እና ሁልጊዜም ራሳችሁን ለማሻሻል ጥረት አድርጉ።

4. ትርጉም ያለው ግንኙነቶችን ፍጠሩ እና ጠብቁ።
ከቤተሰብ፣ ከጓደኞች እና ከፍቅር አጋሮች ጋር የምትፈጥሯቸው ግንኙነቶች በህይወታችሁ ውስጥ ትልቅ ዋጋ አላቸው። እነዚህ ግንኙነቶች በችግር ጊዜ ደጋፊ እና በደስታ ጊዜ አጋዥ ናቸው።

5. ውድቀትን አትፍሩ፤ ከስህተቶቻችሁ ተማሩ።
በህይወት ጉዞ ላይ ውድቀት እና ስህተት የማይቀሩ ናቸው።ዋናው ነገር ከእነዚህ ልምዶች መማር እና እንደገና መሞከር ነው። ውድቀት የጥንካሬ እና የጥበብ ምንጭ ሊሆን ይችላል።

6. ለአዳዲስ ነገሮች ክፍት ሁኑ እና ከምቾት ቀጠናችሁ ውጡ።
አዳዲስ ነገሮችን መሞከር፣ ወደ ተለያዩ ቦታዎች መጓዝ እና ከተለያዩ ሰዎች ጋር መተዋወቅ የአስተሳሰብ አድማሳችሁን ያሰፋል። ይህ ጊዜ አዳዲስ ፍላጎቶችን እና ችሎታዎችን የምታገኙበት ነው።

7. የሌሎችን አስተያየት ከራሳችሁ በላይ አታስቀምጡ።
የሌሎችን ምክር መስማት ጠቃሚ ቢሆንም፣ የመጨረሻው ውሳኔ ግን የራሳችሁ ሊሆን ይገባል።[1] የራሳችሁን ውስጣዊ ድምጽ ማዳመጥ እና በራሳችሁ መተማመን ለህይወታችሁ ትክክለኛውን መንገድ ለመምረጥ ይረዳል።

8. ጊዜያችሁን በአግባቡ ተጠቀሙበት።
ጊዜ ውድ ሀብት ነው፤ አንዴ ካለፈ አይመለስም።ጊዜያችሁን ለዓላማችሁ በሚጠቅሙ ነገሮች ላይ አውሉት። ነገሮችን ማዘግየት እና ጊዜን ማባከን ለጸጸት ይዳርጋል።

9. ራሳችሁን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አቁሙ።
እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ የህይወት ጉዞ እና የጊዜ ሰሌዳ አለው።ራሳችሁን ከሌሎች ጋር ማወዳደር ደስታን ከመንጠቅ እና እርካታን ከማሳጣት ውጪ ምንም አይፈይድም። በራስችሁ እድገት ላይ አተኩሩ።

10. ለህይወት ያላችሁን ፍቅር እና ጉጉት ጠብቁ።
ህይወት ውጣ ውረድ አላት፤ ነገር ግን ለእያንዳንዱ ቀን በአመስጋኝነት እና በአዎንታዊ አመለካከት መኖር አስፈላጊ ነው።ትናንሽ ደስታዎችን ማድነቅ እና ለወደፊቱ በተስፋ መመልከት ህይወትን ትርጉም ያለው ያደርገዋል።

Address

Hossana

Telephone

+251932655168

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adane Yisma Baruda Page/ አዳነ ይስማ ባሩዳ ፔጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Adane Yisma Baruda Page/ አዳነ ይስማ ባሩዳ ፔጅ:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share