Meki Post-መቂ ፖስት

Meki Post-መቂ ፖስት Meki Post

“አእምሮህን ተጠቅመህ ነገህን ፍጠር!” - ዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ  |  የኒዩሮ ሳይንስ አመራር መጽሐፍ ***ለአንድ ተቋም ስኬታማነትም ሆነ ውድቀት በቅድሚያ ጣት የሚቀሰረው ወደ መሪው እንደመሆ...
23/07/2025

“አእምሮህን ተጠቅመህ ነገህን ፍጠር!”
- ዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ

| የኒዩሮ ሳይንስ አመራር መጽሐፍ

***
ለአንድ ተቋም ስኬታማነትም ሆነ ውድቀት በቅድሚያ ጣት የሚቀሰረው ወደ መሪው እንደመሆኑ “በሁሉም ነገር ምሉእ የሆነ መሪ” ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው? መሪውስ ምን ዓይነት ባሕርያት ሊኖሩት ይገባል? ሥራዎቹስ ምን መምሰል አለባቸው? መሪውን ከሌላው ማኅበረሰብ የተለየ ምን ዓይነት ክህሎት ቢኖሩት ነው፥ የሚመራው ተቋም የሚገጥሙትን ፈተናዎች እና ተግዳሮች ተቋቁሞ በስኬታማነት ሊወጣ የሚችለው? ለሌሎች አርዓያ በመሆን የተቋሙን ስምና ዝና ጠብቆ ማቆየት እንዴት ይችላል?

የንግድ ተቋማት ተወዳዳሪ ሆነው እንዲዘልቁ ምን ዓይነት ስትራቴጂዎችን መንደፍ እና መተግበር ይኖርባቸዋል? የሚሉና ሌሎች በርካታ ጥያቄዎችን እያነሣ ምላሹን እጅግ ማራኪ በሆነ መንገድ የሚያቀርበው፣ በእውቀት የደረጀ፣ ከዚህ ቀደም በተግባር ተሞክሮ ውጤታማነቱንን ያስመሰከረ፣ “የኒዩሮ ሳይንስ አመራር” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ እንደበቃ ሰምተዋል?

ይህ የዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ፣ “ኒዩሮ ሳይንስ ለሥራ ፈጠራ” ቅጽ አንድ መጽሐፋቸውን ተከትሎ ለንባብ ያበቁት ቅጽ ሁለት መጽሐፋቸው ሲሆን፣ ዶ/ር ያሬድ፣ በአገረ አሜሪካን ፍሎሪዳ ውስጥ በሚገኘው ኬይ ዌስት ዩንቨርሲቲ፣ የስትራቴጂክ ውሳኔ አሰጣጥና ችግር አፈታት እንዲሁም የአስተዳደር ኮርስ አስተማሪ ሲሆኑ፣ ሥራ ፈጣሪ፣ የካፒታል ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና የስኬታማ ኩባንያዎች ባለቤትም ናቸው።

ዶ/ር ያሬድ፣ ለዓመታት ካካበቱት የትምህርት ዝግጅታቸው እና የስኬታማ ኢንቨስትመንት አመራራቸውን መነሻ አድርገው፣ ለሀገሬው ልጆች፣ “የኒዩሮ ሳይንስ አመራር” የተሰኘውን፣ ስኬታማ ሥራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረገ፣ በዓይነቱ ለየት ያለ መጽሐፋቸውን “የአመራር ልህቀትን በኒዩሮ ሳይንስ የማጎልበት ሂደት” በማለት ለንባብ አብቅተዋል።

መጽሐፉ በ237 ገጾች የተቀነበበ፣ 3 ክፍሎች፣19 ምዕራፎችን ያካተተ፣ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የታተመ ሲሆን፣ ከሐምሌ 2-2017 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሁሉም የመጻሕፍት መደብሮች እየተሸጠ ይገኛል።

***
ዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ፤ በአገረ አሜሪካን ፍሎሪዳ ውስጥ በሚገኘው ኬይ ዌስት ዩንቨርስቲ፣ የስትራቴጂክ ውሳኔ አሰጣጥና ችግር አፈታት እንዲሁም የአስተዳደር ኮርስ አስተማሪ ሲሆኑ፣ ሥራ ፈጣሪ፣ የካፒታል ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና የስኬታማ ኩባንያዎች ባለቤትም ናቸው።

ዶ/ር ያሬድ፣ ለዓመታት ካካበቱት የትምህርት ዝግጅታቸው እና ስኬታማ ሥራዎቻቸውን መነሻ አድርገው፣ ለሀገሬው ልጆች፣ “ኒዩሮ ሳይንስ ለሥራ ፈጠራ” የተሰኘውን፣ ውጤታማ የሥራ ፈጠራ ላይ ትኩረት ያደረገ፣ በዓይነቱ ለየት ያለ መጽሐፋቸውን ለንባብ አብቅተዋል።

ዶ/ር ያሬድ፣ “ኒዩሮ ሳይንስ ለሥራ ፈጠራ” ቅጽ አንድ መጽሐፋቸው፣ የስኬታማ ሥራ ፈጣሪነት ዋነኛው ምሥጢር የሆነውን የአእምሮን ሥነ ሕይወታዊና ግብረ አካላዊ ባሕርያት በማስረዳት፣ ሥራ ፈጣሪው በአግባቡ እና በብቃት እንዲጠቀመው፣ የሚገጥሙትን ፈተናዎች ምንነት በተገቢው ሁኔታ እንዲገነዘብና መፍትሔዎቻቸውን በመፈለግ ረገድ የተዋጣለት፣ ከሌሎች የተሻለ ስኬታማ ሊያደርገው የሚችለውን በመጽሐፋቸው በስፋትና በጥልቀት አቅርበውል።

መጽሐፉ በ310 ገጾች የተቀነበበ፣ 12 ምዕራፎችን ያካተተ፣ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የታተመ ሲሆን፣ ከሐምሌ 2-2017 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሁሉም የመጻሕፍት መደብሮች እየተሸጠ ይገኛል።

“አእምሮህን ተጠቅመህ ነገህን ፍጠር!” (ዶ/ር ያሬድ ኢሳያስ)

23/07/2025

እነዚህ ከታች የምታዩዋቸውና በቅርብ ቀን ለንባብ የበቁ እህትማማች መጻሕፍት---

-- ትውልድ ያንፃሉ፤ ለመልካም ተግባራትና ለተሻለ ኑሮም ያተጋሉ ከሚባሉ የመጻሕፍት ዘርፎች የሚመደቡ ናቸው። አንብበንና አነብንበን ጊዜያዊ መነቃቃት የሚፈጥሩብን ሳይሆኑ፣ በተግባር እንድንሞክራቸው ራሳችንንም እንድንፈትንባቸው የሚያደርጉ ናቸው። በተለይ ሥራ አጥ፣ ሥራ ፈትና ሥራ ጠል ለሚበዛባት አገራችን ከፍቱን መድሃኒቶች መካከል አንዱ፣ "ኒዮሮ ሳይንስ ለሥራ ፈጠራ" እንዴት እንደሚያግዝ መረዳት እና የ"ኒዮሮ አመራር ሳይንስ" ምንነትን በጥልቀት መገንዘብ ነው።

አንብቤ እንደጨረስኳቸው በእነዚህ መጻሕፍት የተነሱ ሃሳቦች ባክነው እንዳይቀሩ ምን መደረግ አለበት ብዬ ራሴን ጠየቅሁ። የመጽሐፉ ባለቤት ያሬድ ኢሳያስ (ዶ/ር)ም ሆነ እሱን መሰል ሙያተኞችና 'አእምሮን ተጠቅሞ ነገን መፍጠር እንደሚቻል' የሚያምኑ አማኞች---በእነዚህ መጻሕፍት መነሻነት በየብዙሃን መገናኛው፣ በየከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱና መሰል ስፍራዎች የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎችን ቢሰጡ፣ ተለውጠው የሚለውጡ ንቁና ብቁ ልጆችን በአጭር ጊዜያት ማፍራት ይቻላል ብዬ አምናለሁ።

ሥራን መፍጠር የሚችሉ ወጣቶች በዙርያችን ባንዣበቡ ቁጥር ተስፋ የሚቆርጡ፣ በቀላሉ ለሱስ እጅ የሚሰጡና ራሳቸውን ለማጥፋት የሚፈጥኑ እግሮች አደብ እየገዙ ይመጣሉ ብዬ አምናለሁ። ይህ እንዳይሆን ደግሞ እንደ ያሬድ ኢሳያስ እንዲህ በትጋትና በንቃት የተጻፉ መጻሕፍትን ማንበብና ማስነበብ አንደኛው መንገድ ነው። ያኔ የደበዘዘው ሲፈካ፣ የዘመመውም ሲቃና ይታወቀናል።

( ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ስለመጽሐፉ አስተያየት የሰጠው )

23/07/2025

መልካምነት ዋጋው ስንት ነው?🤔

21/07/2025

ጅብ ሰው አንበሳ
➪ገጣሚ:-ዘውድአክሊል🙏🙏🙏

14/07/2025

ሁሉም ወንድ የሚጀነጅናቹ ለሚመስላቹ ሴቶች 🤔🤔🤔

06/07/2025

አዝናኝ የAl ስብስቦች 😂😂😂😂😂😂😂🥰

06/07/2025

እንደዚህ ቪዲዮ ቀኔን ያሳመረልኝ የለም! ፈታ በሉበት😂😂😂😂😂

የቡና ቁርስ ተጋበዙልኝ🤲🤲🤲🤲🤲
05/07/2025

የቡና ቁርስ ተጋበዙልኝ🤲🤲🤲🤲🤲

05/07/2025

💙💙💙💙💙💛💛💛💛💛

🤔🤔🤔 መቂ አርብ ሰኔ 27/2017ዓ.ም🥰🥰🥰
04/07/2025

🤔🤔🤔 መቂ አርብ ሰኔ 27/2017ዓ.ም🥰🥰🥰

እንደምን አደርሽ መቂ? አርብ ሰኔ 27/2017ዓ.ም🥰🥰🥰
04/07/2025

እንደምን አደርሽ መቂ? አርብ ሰኔ 27/2017ዓ.ም🥰🥰🥰

Address

Mek'I
Shewa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Meki Post-መቂ ፖስት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share