ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef "በጎ ሥራ ከፍቅር ይወለዳል።"
↪️ https://t.me/Hailemariamderese

26/09/2025

+++መስቀል +++
ፍጹም ድንቅ የሆነው የጌታ ፍቅር የተገለጸበት፣ ሰላም የተበሠረበት፣ የነጻነታችን መገለጫ፣ የድኅነታችን መረጋገጫ ቅዱሱ መስቀል የተገኘበት ዕለት የከበረ ነውና በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም በበደሉ ምክንያት ዕዳውን ይከፍለለት ዘንድ ሰው ሆኖ በሞቱ ሕይወትን የሰጠን አምላክ በመስቀል ተሰቅሎ ስለሆነም የመስቀሉ ነገር ለክርስቲያኖች ብዙ ትርጒም አለው፡፡

ለሰው ዘር በሙሉ በተገባለት ቃል ኪዳን መሠረት ጌታችን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ፣ ሰው ሆኖ፣ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ፣ በመስቀል ተሰቅሎ፣ ድኅነትን ለሰው ልጆች ሰጥቶ፣ በመስቀሉ ተጣልተው የነበሩ ሰባቱን መስተፃርራን (ሰውና እግዚአብሔርን መላእክትና ሰውን፣ ነፍስና ሥጋን፣ ሕዝብና አሕዛብን) አስታርቋል፡፡

በሐዲስ ኪዳን መስቀል የመዳን ምልክት መሆኑ የተረጋገጠበት በክርስቶስ ደም የተቀደሰ፣ የጠብ ግድግዳን ያፈረሰ፣ ቅድስናና ክብር ያለው የአበው ተስፋ የተፈጸመበት፣ ሰው ከውድቀቱ የተነሣበት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር … እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፤ በምድርም መካከል መድኃኒትን አደረገ›› (መዝ. ፸፫፥፲፪) እንዳለው መድኃኒት የሆነው አምላካችን በመስቀሉ አዳነን፡፡ (ዮሐ. ፲፱፥፲፯፣ኤፌ. ፪፥፲፮፣ ቆላ. ፩፥፳)

ከበዓሉ በረከት ይክፈለን፤ አሜን!!!

© eotcmk.org

መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

✝️ ደመራ   +++++የታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ ከቁስጥንጥንያ ተነሥታ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘች፡፡ ...
26/09/2025

✝️ ደመራ
+++++
የታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ ከቁስጥንጥንያ ተነሥታ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘች፡፡ በደረሰች ጊዜ የጌታችን መስቀል ተአምራትን እንዳያደርግ አይሁድ በምቀኝነት ቀብረውት ነበርና የተቀበረበትን ቦታ የሚያሳያት አጥታ በመፈለግ ብዙ ጊዜ አሳለፈች፡፡

ኪራኮስ የሚባለው አረጋዊ ሰው መስቀሉ የተቀበረበትን በሥቃይና በመከራ አስጨንቃ ስትይዘው እንደነገራት ታሪኩ ያስረዳናል፤ ቁፋሮ ልታደርግበት የምትችለውን አካባቢም ሲጠቁማት ደመራ አስደምራ ዕጣን አጢሳ ወደ ፈጣሪዋ ተማፀነች፡፡ የዕጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ ከወጣ በኋላ መንበረ ጸባዖት ደርሶ ተመልሶ መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ አመለከታት፡፡ ንግሥቷም በምልክቱ መሠረት ማስቆፈር ጀመረች፡፡ ለማስቆፈር የወሰደባት ጊዜም ከመስከረም ፲፯ እስከ መጋቢት ፲ ነበር፡፡ በቁፋሮውም መጨረሻ ሦስት መስቀሎችን አገኘች፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እነዚህ መስቀሎች አንዱ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር መስቀል እንደሆነ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ፈያታዊው ዘየማንና ፈያታዊው ዘጸጋ ሁለቱ በጌታ ቀኝና ግራ የተሰቀሉት ወንበዴዎች እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡

ንግሥት እሌኒ ሦስቱን መስቀሎች ካገኘች የጌታችን መስቀል ለይታ ለማወቅ የሞተ ሰው አስከሬን አምጥታ በላያቸው ላይ አደረገቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ሙቱን አስነሣው፡፡ ይህን ጊዜ ለይታ ያወቀችውን መስቀል በክብር ወስዳ የቤተ ክርስቲያኑም መሠረት ወዲያው እንዲጣል አደረገች፤ የደመራ ሥርዓት ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚከበር ነው፡፡

ደመራ ማለት “መጨመር፣ መሰብሰብ መከመር” ነው፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም የቃሉን ፍቺ “ደመረ” ከሚለው የግእዝ ቃል አውጥተው ደመራ ግእዝና አማርኛን የአስተባበረ መሆኑን ይናገራሉ፤ አያይዘውም የበዓለ መስቀል ዋዜማ እንጨቶች የሚደመሩበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ (ሰዋሰወ ግእዝ ወግስ መዝገበ ቃላት) በየዓመቱ የመስቀልን በዓል ስናከብር ደመራ የምንደምረውና የምናበራው ቅድስት ዕሌኒን አብነት በማድረግ ነው፡፡

የበረከት በዓል ያድርግልን፤ አሜን!!!

© eotcmk.org

መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

ዘመነ መስቀልመስቀል በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ለዕርቅ የተተከለ ትእምርተ ፍቅር ነው፡፡ በመስቀል የነፍስና የሥጋ መርገም የተሻረበት በመሆኑ ሰው ሁሉ ለችግሩ መጽናኛ ማግኘትና ነ...

"መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እምጸር - ከሁሉ ነገር በላይ የሆነ ቅዱስ መስቀል ከጠላት ያድነናል።" ቅዱስ ያሬድ  እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ !!!          ...
26/09/2025

"መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እምጸር - ከሁሉ ነገር በላይ የሆነ ቅዱስ መስቀል ከጠላት ያድነናል።" ቅዱስ ያሬድ

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ !!!

መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

24/09/2025

✝️ መዝሙረ ዳዊት ፹፩፥፩-፯
+++++++++++++++
፩ ፤ እግዚአብሔር በአማልክት ማኅበር ቆመ፥ በአማልክትም መካከል ይፈርዳል።

፪ ፤ እስከ መቼ ሐሰትን ትፈርዳላችሁ? እስከ መቼ ለኃጢአተኞች ፊት ታደላላችሁ?

፫ ፤ ለድሆችና ለድሀ አደጎች ፍረዱ፤ ለችግረኛውና ለምስኪኑ ጽድቅ አድርጉ፤

፬ ፤ ብቸኛውንና ችግረኛውን አድኑ፤ ከኃጢአተኞችም እጅ አስጥሉአቸው።

፭ ፤ አያውቁም፥ አያስተውሉም፤ በጨለማ ውስጥ ይመላለሳሉ፤ የምድር መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

፮ ፤ እኔ ግን። አማልክት ናችሁ፥ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ፤

፯ ፤ ነገር ግን እንደ ሰው ትሞታላችሁ፥ ከአለቆችም እንደ አንዱ ትወድቃላችሁ አልሁ። አቤቱ፥ ተነሥ፥ በምድር ላይ ፍርድ፥ አንተ አሕዛብን ሁሉ ትወርሳለህና።

+++
https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

23/09/2025

✝️ መዝሙረ ዳዊት ፴፩፥፩-፲፩
++++++++++++++++
፩ ፤ መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው።

፪ ፤ እግዚአብሔር በደልን የማይቈጥርበት በመንፈሱም ሽንገላ የሌለበት ሰው ምስጉን ነው።

፫|፤ ሁልጊዜ ከመጮኼ የተነሣ ዝም ባልሁ ጊዜ አጥንቶቼ ተበላሹ፤

፬ ፤ በቀንና በሌሊት እጅህ ከብዳብኛለችና፥ እርጥበቴም ለበጋ ትኵሳት ተለወጠ።

፭ ፤ ኃጢአቴን ለአንተ አስታወቅሁ፥ በደሌንም አልሸፈንሁም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እነግራለሁ አልሁ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውህልኝ።

፮ ፤ ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል፤ ብዙ የጥፋት ውኃም ወደ እርሱ አይቀርብም።

፯ ፤ አንተ ለእኔ መሸሸጊያዬ ነህ፥ ከጣርም ትጠብቀኛለህ፤ ከከበቡኝ ታድነኝ ዘንድ ደስታዬ ነህ።

፰ ፤ አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።

፱ ፤ ወደ አንተ እንዳይቀርቡ በልባብና በልጓም ጉንጫቸውን እንደሚለጕሙአቸው፥ ልብ እንደሌላቸው እንደ ፈረስና እንደ በቅሎ አትሁኑ።

፲ ፤ በኃጢአተኛ ብዙ መቅሠፍት አለበት፤ በእግዚአብሔር የሚታመነውን ግን ምሕረት ይከብበዋል።

፲፩ ፤ ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ሐሤትም አድርጉ፤ ልባችሁም የቀና ሁላችሁ፥ እልል በሉ።

+++
https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

22/09/2025

✝️ መዝሙረ ዳዊት ፫፥፩-፰
+++++++++++++++
፩ ፤ አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ! በኔ ላይ የሚቆሙት ብዙ ናቸው።

፪ ፤ ብዙ ሰዎች ነፍሴን። አምላክሽ አያድንሽም አልዋት።

፫ ፤ አንተ ግን አቤቱ፥ መጠጊያዬ ነህ፥ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ።

፬ ፤ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር እጮሃለሁ ከተቀደሰ ተራራውም ይሰማኛል።

፭ ፤ እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤ እግዚአብሔርም ደግፎኛልና ነቃሁ።

፮ ፤ ከሚከብቡኝ ከአእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

፯ ፤ ተነሥ፥ አቤቱ፤ አምላኬ ሆይ፥ አድነኝ፤ አንተ የጠላቶቼን መንጋጋ መትተሃልና፥ የክፉዎችንም ጥርስ ሰብረሃልና።

፰ ፤ ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።

+++
https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

✝️ መስከረም ፲ ጼዴንያ ማርያም      + + + + + + + + + + ጼዴንያ ማርያም፡- ጼዴንያ በምትባል ሀገር ማርታ የምትባል ደግ ሴት ነበረች፡፡ ይህች ደግ ሴት በቤቷ ትልቅ አዳራሽ ሠ...
20/09/2025

✝️ መስከረም ፲ ጼዴንያ ማርያም
+ + + + + + + + + +
ጼዴንያ ማርያም፡- ጼዴንያ በምትባል ሀገር ማርታ የምትባል ደግ ሴት ነበረች፡፡ ይህች ደግ ሴት በቤቷ ትልቅ አዳራሽ ሠርታ እንግዶችን እንደ አባታችን አብርሃም ተቀብላ አብለታ አጠጥታ ማደሪያ ቦታም ሰጥታ ታስተናግድ ነበር፡፡ አባ ቴዎድሮስ የሚባል ኢትዮጵያዊ መነኩሴ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ መሽቶበት ከማርታ ቤት በእንግድነት አደረና ጠዋት ሊሄድ ሲነሣ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድ ሲነግራት ‹‹የእመቤታችንን ሥዕል ገዝተህ አምጣልኝ ዋጋውን ልስጥህ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ገንዘቡን ሥዕሉን ሳመጣልሽ ትሰጪኛለሽ›› ብሏት ሄደ፡፡

ኢየሩሳሌምም ደርሶ ቅዱሳት መካናትን ተሳልሞ ሥዕሉን ረስቶ ሳይገዛ ሲመለስ «አደራ ጥብቅ አይደለምን? ያቺ ሴት አደራ ያለችህን ለምን ረሳህ» የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ በጣም ደንግጦ ተመልሶ ሄዶ ገዝቶ በረሃ በረሃውን መጓዝ ጀመረ፡፡ በመንገድም እየተጓዘ አንበሳ ሊበላው እየሮጠ ወደ እርሱ ሲመጣበት አየ፡፡ መነኩሴው አንበሳውን ከመፍራት የተነሣ ደነገጠ፣ ተንቀጠቀጠ ደንግጦ ቁሞ ሳለ ያች ሥዕል ከአንበሳው ጩኸት ሰባት እጅ በሚበልጥ አስፈሪ ድምፅ ጩሃ ተናገረች፡፡ ያን ጊዜ አንበሳው ደንግጦ ፈጥኖ ሸሸ፡፡ መነኩሴውም መንገዱን ቀጠለ፡፡ በመንገዱም ከሚያስፈራ ዱር ውስጥ ወጥተው ወንበዴዎች ሊቀሙትና ሊገድሉት ከበቡት፡፡ ከሥዕለ ማርያሟም እንደ መብረቅ ያለ ታላቅ ቃል ወጣ፡፡

ወንበዴዎችም እጅግ ፈርተው ሸሽተው ከጫካው ውስጥ ገቡ፡፡ ያም መነኩሴ እነኚህን የሚያስደንቁ ተአምራት በተመለከተ ጊዜ በልቡ «ለእኔ ረዳት ትሆነኝ ዘንድ ወደ ሀገሬ ይዣት እሄዳለሁ እንጂ ለላከችኝ ሴት አልሰጥም» ብሎ ወደ ሀገሩ ሊሄድ በመርከብ ተሳፈረ፡፡ በባሕር ላይም ሳለ ጽኑ ነፋስ ተነስቶ መርከቡን እየገፋ ማርታ ወዳለችበት ሀገር ወደ ጽዴንያ ዳርቻ አደረሰው፡፡ ማደሪያም ስለሌለው ወደ ደጓ ሴት ወደ ማርታ ቤት ከእንግዶች ጋር አብሮ ገብቶ አደረ፡፡ ሲነጋ ወጥቶ ሊሄድ ከደጃፍ ሲደርስ ደጃፉ ጠፍቶት ከአጥሩ ሲታገል ዋለ፡፡ ማርታም «አባቴ ያመመህ የደከመህ ትመስላለህ ዛሬ ደግሞ እዚህ እደርና ነገ ትሄዳለህ» አለችውና አደረ፡፡ በሁለኛውም ዕለት እንደ መጀመሪያው ቀን በሩን አልፎ መሄድ አቃተውና እዚያው ማርታ ቤት አደረ፡፡ በሦስተኛው ቀን መውጣት ፈልጐ አሁንም ከአጥሩ ጋር ሲታገል አይታ «አባቴ የሆንከው ምንድነው? እነሆ ዛሬ ሦስተኛ ቀንህ ነው» አለችው፡፡

መነኩሴውም «ይህችን ተአምረኛ ሥዕል አልሰጥም ብዬ ነው፡፡ እኔኮ ሥዕል ከኢየሩሳሌም ግዛልኝ ያልሽኝ መነኩሴ ነኝ» ብሎ ሥዕለ ማርያምን አውጥቶ ሰጣት፡፡ እርሷም እጅግ በጣም ተደስታ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡፡ በሥዕሏም ፊት ሰግዳ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ምስጋናን አቀረበች፡፡ ተቀብላም ሥዕል ቤት አሠርታ በክብር አስቀመጠቻት፡፡ ይህችም ሥዕል ቅዱስ ሉቃስ የሳላት ናት፡፡ ሥጋ የለበሰች ትመስላለች፡፡ ከፊቷም ወዝ ይንጠባጠባል፡፡ በዚህችም ሥዕል ብዙ ተአምራት ተደረገ ሕሙማን ተፈወሱ፣ ዐይነ ስውራን ማየት ቻሉ፡፡ በዚያ ዘመን የነበረው ሊቀ ጳጳስ ተአምሯን ሰምቶ ሥዕሏ ወደ ማርታ ቤት የገባችበት ዕለት መስከረም 10 ቀን እንዲከበር ሥርዓት ሠራ፡፡ ይህም በዓል በቤተ ክርስቲያናችን ሁልጊዜ ይከበራል፡፡

የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ፍቅሯን ጣዕሟን ታሳድርብን፣ ልጇ አምላካችን በጸሎቷ ይማረን፡፡

© በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን

https://t.me/Hailemariamderese
➽ ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

20/09/2025

✝️ መዝሙረ ዳዊት ፻፴፯፥፩፥፰
++++++++++++++++
፩ ፤ አቤቱ፥ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፥ የአፌን ነገር ሰምተኸኛልና፤ በመላእክት ፊት እዘምርልሃለሁ።

፪|፤ ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ ስምህንም አመሰግናለሁ፥ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና።

፫ ፤ በጠራሁህ ቀን በፍጥነት አድምጠኝ፤ ነፍሴን በኃይልህ በብዙ አጸናሃት።

፬ ፤ አቤቱ፥ የምድር ነገሥታት ሁሉ ያመሰግኑሃል፤ የአፍህን ቃል ሁሉ ሰምተዋልና።

፭ ፤ በእግዚአብሔርም መንገድ ይዘምራሉ፤ የእግዚአብሔር ክብር ታላቅ ነውና።

፮ ፤ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ነውና፥ ወደ ችግረኞችም ይመለከታልና፤ ትዕቢተኞችንም ከሩቅ ያውቃል።

፯ ፤ በመከራ መካከል እንኳ ብሄድ፥ አንተ ሕያው ታደርገኛለህ፤ በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጆቼን ትዘረጋለህ፥ ቀኝህም ታድነኛለች።

፰ ፤ እግዚአብሔር ብድራትን ይመልስልኛል፤ አቤቱ፥ ምሕረትህ ለዘላለም ነው፤ አቤቱ፥ የእጅህን ሥራ ቸል አትበል።

+++
https://t.me/Hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

✝️ 3 የዮሴፍ ንጽህና እና የጲጥፋራ ሚስት፡       ++++++++++++++++++++++ ምንም እንኳን ዮሴፍ እንደ ባርያ ለእስማኤለውያን ቢሸጥም ልቡ ግን እንደ ባርያ አልነበረም፡፡ ከምን...
19/09/2025

✝️ 3 የዮሴፍ ንጽህና እና የጲጥፋራ ሚስት፡
++++++++++++++++++++++
ምንም እንኳን ዮሴፍ እንደ ባርያ ለእስማኤለውያን ቢሸጥም ልቡ ግን እንደ ባርያ አልነበረም፡፡ ከምንም በላይ ረዳቱ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነውና ጭንቀት የሚባል ነገር አይታይበትም ነበር፡፡ ባርያ ቢሆንም ግብጽን ከረሀብ ታድጓታል፡፡ ምንም ወንድሞቹ በቅናት ወደ ባርነት ቢሸጡትም እርሱ ግን በፎርዖን ቤት ነገሠ፡፡ በፎርዖን ዘንድ ባለሟልነትን አገኘ፡፡

እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ስለ ነበረ የውስጡ ውበት በየዕለቱ ይፈካ ነበር፡፡ ይህም ቢሆን ግን ልቡ ወደ ትዕቢት አላዘነበለበትም፡፡ በዚሁ ሰዓት ግን ሌላ ፈተና ተጋረጠበት፡፡ የንጉሡ ሚስት ታስነቅፈው ዘንድ ወደደች፡፡ ይህም ቢሆን ግን ምናልባት ልብሱ ትቀድበት እንደ ሆነ እንጂ ልቡን ታቆሽሽበት ዘንድ አልተቻላትም፡፡ ዮሴፍ እንደ ስሙ ጥንካሬ እና ንጽህናን እየጨመረ ሄደ፡፡

ወንደሞቹን እንደወደዳቸውም የጴጢፋራን ሚሰት ይወዳት ነበር፡፡ ስለዚህም ነበር ልብን በሚያቆስል አነጋገር “አንቺ አመንዝራ ሴት ነሽ፤ ከአመንዝራ ሴትም ጋር እተኛ ዘንድ አይገባም” ሳይላት ስለ ራሱ ብቻ ይናገር የነበረው፡፡ እርሷ ንግሥት እርሱ ግን ባርያ እንደሆነም ይነግራት ነበር፡፡

ምንም ወደ ወኅኒ ብትጥለውም አንዳች እንኳን አልመለሰላትም፡፡ እርሷ ግን በተቃራኒው እንኳንስ እርሱን ራሷንም የማትወድ ምስኪን ነበረች፡፡ ምክንያቱም ወዳውስ ቢሆን ኖሮ ወደ እስር ቤት ባልጣለችው ነበርና፤ ራሷንም የምትወድ ብትሆን ኖሮ ንግሥት ሆና ሳለ ይህን የመሰለ አሳፋሪ ሥራ አታደርግም ነበርና፡፡

ስለዚህ እርሷ በፍቅር ሳይሆን በዝሙት የተቃጠለች ሴት ነበረች፡፡ ምንም እንኳን ዮሴፍ አብርሃም እና ይስሐቅን ከመሰሉ ታላላቅ አባቶች የተወለደ ቢሆንም ራሱን ከፍ ከፍ ሳያደርግ ለፎርዖን ይታዘዝ ነበር፡፡ ንጽህናው ለወጣት ወንዶች ሁሉ አርአያ ነው፡፡ አዎ! ወንዶች ከዮሴፍ፣ ሴቶች ከሶስና ደናግላንም ከድንግል ማርያም ንጽህናን መማር ይገባናል፡፡ ይህን ንጽህና እንይዝ ዘንድ ጌታ ይፈልጋል፡፡ ይኸንን ስናደርግ አምላካችን ይደሰታል፤ በሕይወታችንም እንደ ዮሴፍ ይባርከናል፡፡ ምንም እንኳን ዮሴፍ ልብሱን ትቶላት ቢሮጥም እንደ አዳም ግን አላፈረም፡፡

ንጽህናው በገነት ውስጥ ሆኖ ከበደለው አዳም ትበልጥ ነበርና፡፡ እንግዲያስ እኛም ወጣቶች ክብራችንን ለማጉደፍ እንቅልፍ ላጣች ዓለም ልብሳችንንም እንኳን ቢሆን ጥለንላት ከዝሙት ግብዣዋ እንራቅ (ዮሐንስ አፈወርቅ)፡፡

ይህንን ስናደርግ በእርግጥም መስቀላችንን ተሸክመናልና የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንባላለን፡፡
ኤልያስ የዚህ ዓለም የሆነውን መጐናጸፍያ በዚሁ ዓለም ትቶት እንደ ሄደ እኛም የዓለም የሆነውን ለራሷ እንስጣት (ቅዱስ ጀሮም)፡፡

https://t.me/hailemariamderese
ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef

Address

Shewa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ቤተ ዮሴፍ - Bete Yosef:

Share