
21/08/2025
ቀን 14/12/2017 ዓ/ም
በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስ/ር የማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ እንደሚካሄድ ተገለጸ
***
የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በከተማ አስ/ር ስር በሚገኙ በ6ቱም ቀበሌዎች ከነሐሴ 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የትራኮማ በሽታን መከላከል የሚያስችል የአዚትሮማይሲን መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ አስመልክቶ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል ።
የእንኳን ደህና መጣችሁና የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት ስለትራኮማ በሽታ አስከፊነትና የበሽታውን ጫና በማውሳት በከተማ አስተዳደራችን ብዙ ዓመታትን በትራኮማና ሌሎች ትኩረት በሚሹ በሽታዎች መከላከል ዙሪያ በተለይም በአይነስውርነት ሳቢያ የሚከሰተውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ስነልቦናዊ ጫና ትርጉም ባለው መልኩ ለመከላከል ማህበረሰብ ዐቀፍ የትራኮማ መከላከያ መድኃኒት እደላውን ከብክነት በፀዳ መልኩ መድኃኒቱን መስጠት እንደሚገባ ያሳሰቡ ሲሆን
አቶ ኤልያስ አያይዘውም በምንም ሊተካ በማይችለዉ አይን ላይ ጉዳት የሚያደርሰውን ትራኮማን ለመከላከል አልፎም ለማጥፋት የሚሰጠውን መድኃኒት ለህብረተሰቡ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ እንዲሆን በዘመቻዉ የሚሰራጩ መድሃኒቶች በአጋር ድርጅቶች አማካይነት በዉድ ዋጋ ተገዝተዉ የሚቀርቡ መሆናቸዉን በመገንዘብ ዘመቻዉን በተቀመጠለት የግዜ ገደብ ተግባራት በጥብቅ ዲስፒሊን ሊመሩ እንደሚገባ ጠቁመው ለዚህ ስኬትም የጤና ኤክስቴንሽኖች የጤናው ሴክተር ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ በማሳሰብ የእለቱን የክብር እንግዳ የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቴዎስ የመክፈቻ ንግግር እንዲያደርጉ ጋብዘዋል ።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቴዎስ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራችን ለበርካታ ዜጎች የአይን ብርሃን ማጣት መንስኤ የሆነዉን የትራኮማ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ያስችል ዘንድ ታልሞ ከነሐሴ 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ በከተማ ለሚገኙ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ተደራሽ መደረግ አለበት ለዚህም በተለመደው ቅንጅታዊ አሰራር መሰረት ዘመቻው በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን እንዲወጣ በማሳሰብ የዕለቱን የስልጠና መድረክ ከፍተዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ስራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ አዱኛ ለጋሳ ሲሆኑ ከስልጠናውም መልስ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግና ለሁሉም ቀበሌ ለዘነቻው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በማከፋፈል የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
በመድረኩ ላይ የከተማ አስተባባሪ ፣የዞን ጤና መምሪያ ደጋፊ ባለሙያ ፣የከተማ የጤና ጽ/ቤት ማኔጅመንት አባለት፣ የጤና ኤክስቴንሽኖች፣ ጤና ባለሙያዎችና ዘርፋ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት
ሾኔ