የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Shone
  • የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ይህ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የማህበራዊ ሚዲያ ድህረ ገጽ ነው።

ቀን 14/12/2017 ዓ/ምበሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስ/ር የማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ እንደሚካሄድ ተገለጸ              ***የሾኔ ከተማ አስ/ር...
21/08/2025

ቀን 14/12/2017 ዓ/ም
በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስ/ር የማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ እንደሚካሄድ ተገለጸ
***
የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በከተማ አስ/ር ስር በሚገኙ በ6ቱም ቀበሌዎች ከነሐሴ 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የትራኮማ በሽታን መከላከል የሚያስችል የአዚትሮማይሲን መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ አስመልክቶ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል ።

የእንኳን ደህና መጣችሁና የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት ስለትራኮማ በሽታ አስከፊነትና የበሽታውን ጫና በማውሳት በከተማ አስተዳደራችን ብዙ ዓመታትን በትራኮማና ሌሎች ትኩረት በሚሹ በሽታዎች መከላከል ዙሪያ በተለይም በአይነስውርነት ሳቢያ የሚከሰተውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ስነልቦናዊ ጫና ትርጉም ባለው መልኩ ለመከላከል ማህበረሰብ ዐቀፍ የትራኮማ መከላከያ መድኃኒት እደላውን ከብክነት በፀዳ መልኩ መድኃኒቱን መስጠት እንደሚገባ ያሳሰቡ ሲሆን

አቶ ኤልያስ አያይዘውም በምንም ሊተካ በማይችለዉ አይን ላይ ጉዳት የሚያደርሰውን ትራኮማን ለመከላከል አልፎም ለማጥፋት የሚሰጠውን መድኃኒት ለህብረተሰቡ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ እንዲሆን በዘመቻዉ የሚሰራጩ መድሃኒቶች በአጋር ድርጅቶች አማካይነት በዉድ ዋጋ ተገዝተዉ የሚቀርቡ መሆናቸዉን በመገንዘብ ዘመቻዉን በተቀመጠለት የግዜ ገደብ ተግባራት በጥብቅ ዲስፒሊን ሊመሩ እንደሚገባ ጠቁመው ለዚህ ስኬትም የጤና ኤክስቴንሽኖች የጤናው ሴክተር ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ በማሳሰብ የእለቱን የክብር እንግዳ የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቴዎስ የመክፈቻ ንግግር እንዲያደርጉ ጋብዘዋል ።

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቴዎስ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራችን ለበርካታ ዜጎች የአይን ብርሃን ማጣት መንስኤ የሆነዉን የትራኮማ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ያስችል ዘንድ ታልሞ ከነሐሴ 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የማህበረሰብ አቀፍ የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሃኒት ዕደላ ዘመቻ በከተማ ለሚገኙ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ተደራሽ መደረግ አለበት ለዚህም በተለመደው ቅንጅታዊ አሰራር መሰረት ዘመቻው በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን እንዲወጣ በማሳሰብ የዕለቱን የስልጠና መድረክ ከፍተዋል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ስራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ አዱኛ ለጋሳ ሲሆኑ ከስልጠናውም መልስ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግና ለሁሉም ቀበሌ ለዘነቻው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በማከፋፈል የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።

በመድረኩ ላይ የከተማ አስተባባሪ ፣የዞን ጤና መምሪያ ደጋፊ ባለሙያ ፣የከተማ የጤና ጽ/ቤት ማኔጅመንት አባለት፣ የጤና ኤክስቴንሽኖች፣ ጤና ባለሙያዎችና ዘርፋ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የሾኔ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት
ሾኔ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አዘጋጅነት"በተደረጀ የአመራርና የህዝብ ባለቤትነት እና ተሰትፎ ህዝባችንን ከመዘናጋት እናውጣ" በሚል መሪ ቃል የተ...
16/06/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አዘጋጅነት"በተደረጀ የአመራርና የህዝብ ባለቤትነት እና ተሰትፎ ህዝባችንን ከመዘናጋት እናውጣ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የኤች,አይ,ቪ ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

የሾኔ ከተማ አስተ/ር ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 09/2017 ዓ.ም ሾኔ

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ በንግግራቸው ኤችአይቪ/ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በመንግሥት፤ በሕዝብና በአጋር አካላት በተደረጉ ጥረቶች እንደ ሀገር አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ማህበረሰቡም ይሁን አስፈፃሚው አካል ለበሽታው ያላቸው ትኩረት በመቀነሱ ምክንያት የቫይረሱ ስርጭት በ2030 ለመግታት ከታቀደው አንፃር በሚፈለገው መጠን እንዳልቀነሰ አስታውሰው በቀጣይ ሁሉም ባለድርሻ አካል ከገባበት መቀዛቀዝና መዘናጋት እንዲወጣ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ መሆኑን በመግለጽ የዕለቱን መድረክ ከፍተዋል።

የንቅናቄ ሰነዱን ያቀረቡት የከተማ አስተዳደሩ የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ምላሽ ሂደት ተወካይ አቶ አማረ ማርቆስ ሲሆኑ በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግና በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶቾና ቀበሌያት ላይ ተመሳሳይ ውይይት እንዲደረግ የተቋረጠው 0.5 % HIV ፈንድ ለማስቀጠል ሁሉንም የመንግስት ሰራተኛ ማሳመንና ማስቆረጥ እንደሚገባ አቅጣጫ በመያዝ የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።

የሾኔ ከተማ አስተ/ርጤና ጽ/ቤት ሰኔ 09/2017 ዓ.ም
ሾኔ

30/05/2025
የሁለተኛ ዙር የተቀናጀ የልጅነት ልምሻ /ፖሊዮ (nOPV2)ክትባት ዘመቻ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት  በይፋ አስጀመረ።ግንቦት 22/2017 ዓ/ም ሾኔ በሾኔ ከተማ አስተዳ...
30/05/2025

የሁለተኛ ዙር የተቀናጀ የልጅነት ልምሻ /ፖሊዮ (nOPV2)ክትባት ዘመቻ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት በይፋ አስጀመረ።

ግንቦት 22/2017 ዓ/ም ሾኔ
በሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የሁለተኛ ዙር የተቀናጀ ልጅነት ልምሻ /ፖሊዮ (nOPV2)በሽታን መከላከል የሚያስችል ክትባት ዘመቻ ተጀምሯል።

የፖሊዮ በሽታ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በሊቻ ቀበሌ TVT ኮሌጅ አካባቢ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተደርጓል።

የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት በመግቢያ ንግግራቸው ፥ የፖሊዮ በሽታን እንደ ሀገር ለማጥፋት ባለፉት በርካታ ዓመታት በርካታ ስራዎች ቢሰሩም አሁንም በሽታው አለመጥፋቱን በመግለጽ ከመደበኛ ክትባት በተጨማሪ የሚሰጠውን የዘመቻ ክትባት በአግባቡ በመውሰድ ይህን አስከፊ በሽታ መከላከል እንደሚገባ ገልፀዋል።

አቶ ኤልያስ ዳዊት አክለው የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የሁለተኛ ዙር ከግንቦት 22-25/2017 ዓ/ም በከተማ አስተዳደሩ በ6ቱም ቀበሌያት ከ11800 በላይ ለሚሆኑ ህፃናት ክትባቱ ቤት ለቤት የሚሰጥ ሲሆን በክትባት ዘመቻው ከ5ዓመት በታች የሆኑ ሌሎች ክትባቶችንም በመደበኛው መርሃ-ግብር ተደራሽ ያልሆኑ ወይም ጀምረው ያቋረጡ ህፃናትን በመለየት ፤ በጤና ተቋማት ወይንም በጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያ ወይም ሆስፒታል ተደራሽ እንደሚደረግም በመግለጽ የዕለቱን የክብር ዕንግዳ የከተማ አስተዳደሩ የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቲዎስን ዘመቻውን በይፋ እንዲያስጀምሩ ጋብዘዋል ።

መርሃ-ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የሾኔ ከተማ አስተዳደር የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ማቲዎስ ባደረጉት ንግግራቸው እንደገለጹት ሕጻናትን የሚያጠቃው የልጅነት ልምሻ በሽታን ለመከላከል ክትባቱን ከዚህ በፊት የተከተቡም ያልተከተቡም አሁን በዘመቻ የሚሰጠውን ክትባት በመውሰድ ይህን አደገኛ በሽታ መከላከል እንደሚገባ ገልፀው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ በማቅረብ ዘመቻውን አስጀምረዋል።

ለተቀናጀ ክትባት ዘመቻው ውጤታማነት ወላጆች አሳዳጊዎችና ባለ ድርሻ አካላት ፣ ትምህርት ቤቶች ፣የሃይማኖት አባቶች ፣የሚዲያ አካላት እና መላው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጽ/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

ፖሊዮ ወይም በተለምዶ የልጅነት ልምሻ የሚባለው በሽታ በልጆች ላይ ሽባነትን ወይም ሞትን ሊያስከትል የሚችል በሽታ ሲሆን በክትባት መከላከል እንደሚቻል ተገልፃል።

ዘገበው የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ነው።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ከ9730  በላይ ህፃናት የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ተከተቡሾኔ፣ ግንቦት 15፣ 2017 ዓ.ምበሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ከግ...
23/05/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ከ9730 በላይ ህፃናት የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ተከተቡ

ሾኔ፣ ግንቦት 15፣ 2017 ዓ.ም

በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ከግንቦት 6 ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ እስካሁን 9730 በላይ ህፃናት መከተባቸውን የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽ/ቤት አስታወቀ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት እንደገለጹት ፤ ክትባቱ ከ9 ወር እስከ 59 ወር ዕድሜ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ህፃናት እንደተሰጠም ገልፀዋል።

በዘመቻው ክትባቱ ከዕቅድ በላይ 9200 ታቅዶ 9730 በማከናወን 105% ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው፤ ከኩፍኝ መከላከያ ክትባት በተጨማሪ ሌሎች የክትባት ሥራዎችም በዘመቻው ወቅት እየተከናወነ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በዚህም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ስድስት ቀበሌዎች በተለያየ ጊዜ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል የሚያስችል የተቀናጀ የክትባት ዘመቻ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

ከተወለዱ ጀምሮ ምንም ክትባት ያልወሰዱ 14 ህፃናትን እንዲሁም ክትባት ጀምረው ያቋረጡ 19 ሕፃናትን በመለየት ክትባት የማስጀመር ሥራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።

- በዘመቻው ወቅት በከተማ አስተዳደሩ 1979 አጥቢ እና ነፍሰጡር እናቶችን እንዲሁም 8225 ህጻናት የሥርዓተ ምግብ ልየታ መደረጉን ገልፀው 8225 ዕድሜያቸው ከ6 ወር በላይ ለሆናቸው ህጻናት የቫይታሚን ኤ እደላ እንዲሁም 6164 የአንጀት ጥገኛ ትላትል መከላከያ መድሃኒት ዕድሜያቸው ከ24 ወር እስከ 59 ወር ድረስ ላሉት መድሃኒት መሰጠቱን ገልፀዋል።

አስፈላጊ ክትባቶችን መስጠትን ጨምሮ የእናቶችና ህፃናትን ጤና ለመጠበቅ ቀጣይነት ያለው ሥራ እስከ ቀበሌ ድረስ ባሉ አደረጃጀቶች እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በመልክታቸውም ህብረተሰቡና ሌሎችም መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በቀጣይ ሁለት ቀን በሚጠናቀቀው ዘመቻ አንድም ሕፃን ሳይከተብ እንዳያልፍ ትብብር በማድረግ ሕፃናትን ክትባት ባለመከተብ ከሚመጡ በሽታዎች እንታደግ ብለዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ሾኔ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር "የጤና ዘርፍ አርበኝነት ለሀገር እድገት"  በሚል መሪ ቃል የጤና ባለሙያዎች ውይይት ተካሄደ፤ባለሙያዎች በከተማ አስተዳደሩ እየተ...
15/05/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር "የጤና ዘርፍ አርበኝነት ለሀገር እድገት" በሚል መሪ ቃል የጤና ባለሙያዎች ውይይት ተካሄደ፤

ባለሙያዎች በከተማ አስተዳደሩ እየተገነባ ያለውን የውሃ ፕሮጀክትን ጨምሮ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችንም ጎብኝተዋል። በዕለቱም በጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት አማካኝነት ሀገር አቀፍ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ሾኔ፦ግንቦት -7-2017ዓ.ም
የውይይቱ ዋና ዓላማ በጤና ልማት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችና እየተስተዋሉ ያሉ ጉድለቶችን እንዲሁም ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ከዘርፋ ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት መሆኑ ተገልፆል።

ባለፋት ዓመታት መንግስት በማህበራዊ ልማት ዘርፍ በተለይም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ የቆየ ሲሆን ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡ በወይይቱ ተነስቷል።

በጤና ልማት ዘርፍ የሚስተዋሉ የተለያዩ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ጉድለቶችን ደረጃ በደረጃ ለሟሟላት ሰፊ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና አሁንም ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ መንግስት ቁርጠኛ መሆኑ ተገልጿል፣

በውይይቱም ከባለሙያዎች የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች ፣ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት እና የክልሉ ጤና ቢሮ ተወካይ አቶ ተስፋዬ ሌጂሶ ፣የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ፣ የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል አየለ እና የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት እንዲሁም የሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ሎምቤ፣

ግንዛቤ በሚሹ እና የመረጃ ክፍተት ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ተወካይ አቶ ተስፋዬ በባለሙያዎች የተነሱትን ጥያቄዎች በድጋሚ ለክልሉ እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ መድረኩን ባጠቃለሉበት ወቅት እንደገለጹት ፣የጤና ባለሙያዎች ስላላቸው አገልግሎት ከፍ ያለ አክብሮት እንዳለቸው በመግለጽ፣ በተለይ የመስክ ምልከታው እንደ ከተማ ምን እየተሰራ እንዳለ ለማወቅ ትልቅ እድል የፈጠረ ነው በማለት:-

እንደ ከተማ ወስደን መስራት የሚጠበቅብንን ከዚህ ቀደም እየሰራን እንደመጣን ሁሉ ፣አሁንም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራን እንሄዳለን ብለዋል።

መደረኩ ነፃ፣ አሳታፊ ፣ ዴሞክራሲያዊና ባለሙያዎች በነፃነት አስተያየት የሰጡበት መድረክ እንደሆነ ተመላክቷል።

በቀጣይም የጤና ባለሙያዉ በሀገር ደረጃ የተቀረጸዉን አዲሱን የጤና ልማት ፖሊሲ ለመተግበር በሚደረገዉ ጥረት የራሱን አስተዋጾ ለማበርከት ቃል በመግባት ዉይይቱ ተጠናቋል።

የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት ሾኔ

ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 59 ወራት ለሆኑ ሕፃናት የተቀናጀ  የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ከግንቦት 6 እስከ 15/2017 ዓ.ም  ድረስ እንደሚሰጥ የሾኔ ከተማ አስተዳደር  ጤና ጽ/ቤት ገለፀ...
11/05/2025

ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 59 ወራት ለሆኑ ሕፃናት የተቀናጀ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ከግንቦት 6 እስከ 15/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

ሾኔ :- ግንቦት 02/09/2017 ዓ.ም

በስልጠናው ከጤና ጽቤት፣ ከማዞሪ ጤና ጣቢያ እና ከሆስፒታል ካችመንት የተውጣጡ የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ሱፔርቫይዘሮች እና ኮርድኔቴሮች ተገኝተዋል ።

የስልጠናውን መድረክ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት የከፈቱ ሲሆን በመክፈቻ ንግግራቸውም ከኩፍኝ ዘመቻ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ ዝርዝር ተግባራትን ለተሳታፊዎች ገልፀዋል።

በመቀጠልም ባለፋት ዓመታት የክፋኝ በሽታ ለሕፃናት ህመም ስቃይና ሞት ምክንያት መሆኑ የቅርብ ጊዜ ትውስታ መሆኑን በመግለጽ ይህንን የተገኘውን ዕድል በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ በማሳሰብ ዘመቻው ውጤታማ እንዲሆን የሀይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች ፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሕፃናት ወላጆችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ትብብር እንዲያደርጉ በማሳሰብ ዘመቻው በከተማ አስተዳደሩ ባሉ በሁሉም ቀበሌያት ከግንቦት 6 እስከ 15/2017 ዓ.ም ድረስ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው በዘመቻው አንድም ሕፃን ሳይከተብ እንዳያልፍ የአደራ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ የዕለቱን የስልጠና መድረክ ከፍተዋል።

ሥልጠናውን የእናቶች እና ህጻናት ጤና ክፍል አስተባባሪ አቶ አማራ ማርቆስ እና የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አሸናፊ ዮሴፍ ሰጥተዋል ።

ከኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ ስራዎች ያልተከተቡ ህጻናት/zero dose/ ፣የአንጀት ጥገኛ ትላትል መድኃኒት እደላ ፣የቫይታሚን ኤ እደላ የታመሙ ሕፃናት ካሉ ወደ ጤና ተቋም መላክ , ስነምግብ አገልግሎት ፣ ፊስቱላ ፣የእግር መቆልመም እና ሌሎችም የጤና ችግር ያለባቸውን ሰዎች የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሠራ ተገልፆል በመቀጠልም በቀጣይ በቀበሌ ደረጃ የሚተገበሩ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶች ተነስተዉ ማብራሪያ ከተሰጠ በኃላ የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ሾኔ

በማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት ለስቅለት እና ትንሳኤ  በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፋ፡፡ ሚያዚያ 10/08/...
18/04/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት ለስቅለት እና ትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፋ፡፡

ሚያዚያ 10/08/2017ዓ/ም ሾኔ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና ትንሳኤ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል ፡፡

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከሃጢያት ነፃ ለማውጣት የተሰቀለበትን ፣ የሞተበትን እና በሦስተኛው ቀንም ሞትን ድል አድርጎ ትንሳኤ ያደረገበትን ዕለት በክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው ኃይማኖታዊ በዓል መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

የትንሳኤ በዓል አብይ በዓል መሆኑን ገልጸው ህዝበ ክርስቲያኑ ያለፋትን ሁለት ወራት ፆም ፣ ፀሎት እና መልካም ተግባራት ሲፈጽም መቆየቱ ከመንፈሳዊ ባሻገር የጤና ጥቅም እንዳለው ገልጸዋል ፡፡

ህዝበ ክርስቲያኑ በፆም ወራት ከፍተኛ ቅባት እና ስብ ካላቸው ምግቦች ተቆጥቦ የቆየ በመሆኑ የበዓል አመጋገብ ስርዓት ከጤናችን የተስማማ እና ሰውነታችን ቅባት የበዛባቸው ምግቦችን እያለማመዱ መመገብ እንደሚገባ ምክራቸውን ሰጥተዋል ፡፡

በዓሉ አንድነትን ይቅርታን ፣ መተሳሰብን እንዲሁም ወገንን በማገዝ የሚገለጽበት በመሆኑ በተለይ በህመም ላይ ያሉ ፣ ወላጆቻቸውን በተለያየ አጋጣሚ በህይወት ያጡ ፣ አቅመ ደካማ ወገኖቻችንን በመጠየቅ ፣ በመረዳዳት በማካፈል አብሮ በዓሉን ማክበር ይገባል ብለዋል ፡፡

አቶ ኤልያስ በመልዕክታቸው የበዓል እርድ ስርዓታችንም መንግስት ጽዱ ኢትዮዺያን ለመፍጠር እየሰራ ያለውን የአካባቢን ጽዳት የጠበቀ እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል ፡፡

በበአል ዋዜማ እና በበአሉ እለት በሁሉም አካባቢ ህብረተሰብን በጤና ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ ላሉ እንዲሁም ለሁሉም ውድ የጤና ባለሙያዎች እንኳን አደረሳቹሁ ብለዋል ፡፡

በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖች በሙሉ በድጋሚ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ፡፡

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ሾኔ

በሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህዝብ ፎረም አካሄደ ።መጋቢት 23/2017 ዓ.ም።በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር...
01/04/2025

በሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህዝብ ፎረም አካሄደ ።

መጋቢት 23/2017 ዓ.ም።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህዝብ ፎረም አካሄደ ።

በህዝብ ፎረም ላይ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ እንዲሁም የሾኔ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ደንኤል አየለን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ሥራ አስፈፃሚዎች እና ፑል አመራር የጤና ጽ/ቤትና የሆስፒታል የማናጅመንት አካላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተወካዮች የንግዱ ማህበረሠብ ተወካዮች የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል ።

የመክፈቻ ንግግር በከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ የመክፈቻ ንግግር ከተደረገ በኃላ በሆስፒታሉ በ8ወር የተሰሩ ሥራዎች በሆስፒታሉ ልማት ዕቅድ ክፍል አስተባባሪ በአቶ አበበ ሄሎሬ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል ።

የውይይቱን መድረክ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ እንዲሁም የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት እና የሆስፒታሉ ሥራአስኪያጅ አቶ አብርሃም ሎምቤ መርተውታል።

በፎረሙ ተሳታፊዎች ሆስፒታሉ እየሠጠ ባለው የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እንዲሁም ጉድለቶቹ ላይ አስተያየት በስፋት ከተሰጠ በኃላ በጉድለቶቹ ላይ ሁሉም የሚመለከተው ባለድርሻ አካላት የራሱን አስተዋፆ እንደሚያበረክት ቃል በመግባት የዕለቱ ፕሮግራም የተጠናቀቀ ሲሆን በዕለቱ የከተማ ፅዳት ስራ እንዲሁም ማስ ስፖርት ተከናውኗል ።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት
ሾኔ

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አገር አቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ የሦስተኛ  ቀን ውሎ በጽ/ቤት ደረጃ ገመገመ።          *******  17/06/2017 ዓ.ም  *****የጤና ...
24/02/2025

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አገር አቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ የሦስተኛ ቀን ውሎ በጽ/ቤት ደረጃ ገመገመ።
******* 17/06/2017 ዓ.ም *****
የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት ፣ ኮኦርዲነተሮች እና የቀበሌ ሱፐርቫይዘሮች ባሉበት የሦስተኛ ቀን አፈፃፀም ግምገማ ላይ የተገኙ ሲሆን የዕለቱን ውሎ የሚገልጽ ሪፖርት በሱፐርቫይዘሮች በኩል ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል።

እንደ ከተማ አስተዳደር 8862 ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ህጻናት ክትባቱን ለመስጠት ታቅዶ በመጀመሪያ ቀን ውሎ 9012 ህፃናትን ተከትበው አጠቃላይ አፈፃፀም 102 % እንደሆነ በአፈፃፀም ግምገማው ተረጋግጧል።

ከፖሊዮ ዘመቻ ጎን ለጎን በቅንጅት እየተከናወኑ ባሉት ተግባራትም ሰፋ ያለ ስራ እንደተሰራ በግምገማ ተረጋግጧል።

በመጨረሻም በማጠቃለያው ለደጋፊ ሱፐርሻይዘሮች ፣ ለኮኦርዲነተሮች :-
- ክትባቱ ተደራሽ ያለሆነባቸውን አካባቢዎች መድረስ እንዲሁም ክትባቱ የተሰራባቸው ቀበሌዎች ላይ በትኩረት የመልሶ ማረጋገጥ ስራ እንዲሰራ አቅጣጫ በመያዝ
የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት!!

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አገር አቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ በጽ/ቤት ደረጃ ገመገመ።          *******  15/6/2017 ዓ.ም  *****የጤና ጽ...
22/02/2025

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አገር አቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ በጽ/ቤት ደረጃ ገመገመ።
******* 15/6/2017 ዓ.ም *****
የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት፣የዞን ደጋፊዎች፣ እና የሁሉም መዋቅር ሱፐርቫይዘሮች የመጀመሪያ ቀን አፈጻጸም ግምገማ ላይ የተገኙ ሲሆን የዕለቱን ውሎ የሚገልጽ ሪፖርት በሱፐርቫይዘሮች በኩል ሰፋ ባለ መልኩ ቀርቧል።

ከፖሊዮ ዘመቻ ጎን ለጎን በቅንጅት የሚሠሩ ተግባራት በሁሉም ቀበሌዎች እየተከናወኑ እንደሆነና በቀጣይም በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠል እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል።

እንደ ከተማ አስተዳደር 8862 ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ህጻናት ክትባቱን ለመስጠት ታቅዶ በመጀመሪያ ቀን ውሎ 2793 ህፃናትን ተከትበው አፈፃፀሙ ከዕለቱ ዕቅድ አንፃር 126 % ሆኖ ከአጠቃላዩ 31.5 % እንደሆነ በአፈፃፀም ግምገማው ተረጋግጧል ይህም አፈፃፀም ሥራው በታለመለት ጊዜ ሊያልቅ እንደሚችል ማሳያ ሥለሆነ ተጠናክሮ መቀጠል እናዳለበት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት አሳስበዋል።

በቅንጅት እየተከናወኑ ባሉት ተግባራትም ሰፊ ሥራ እየተሠራ እንደሆነ ተገምግሞ ከጥራት እና በጊዜ ሪፖርቱን ከመላክ ረገድ በተወሰኑ ቀበሌዎች ጉድለቶች የተገመገሙ ሲሆን በቀጣይ ቀናት መታረም እንዳለባቸው አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም የዛሬውን የውሎ ግምገማ እንደ ጥሩ እድል በመውሰድ ሱፐርሻይዘሮች ግብረ መልሱን ለሚደግፋት ቀበሌ እንዲያደርሱ በማሳሰብ ሥራውን በጥራት በሚሰራበት ሂደት የማጠቃለያ ሀሳብ በመዉሰድ የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት!!

የካቲት 14/2017 ዓ.ም።በሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በይፋ ተጀመረ።በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ዙር...
21/02/2025

የካቲት 14/2017 ዓ.ም።

በሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በይፋ ተጀመረ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የሀድያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በአራንቻ ቀበሌ ላይ በይፋ ተጀምሯል።

የክትባት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የማነጅመንት አካላት ከሀድያ ዞን ጤና መምሪያ ባላሙያዎች ፣ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ እንዲሁም የሾኔ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ደንኤል አየለ ፣ የምስራቅ ባደዋቾ ወረዳ የፊት አመራሮች እና የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ደዊትን ጨምሮ ኮርድነቴሮችና ሡፔርቫይዘሮች ተገኝተዋል ።

Address

On The Way Of Addis Abeba To Arbaminch Main Street
Shone
GIRMAAYELEBUILDING

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251911666511

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት:

Share