Gifaataa Tube

Gifaataa Tube Wolaita, land of 50 kings

‎   !‎         ወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።  ‎      ይህች  ከታች በፎቶ ላይ የሚትመለከቷት ልጅ እህታችን ኤደን ለገሠ ትባላለች። ...
03/07/2025

‎ !
‎ ወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎ ይህች ከታች በፎቶ ላይ የሚትመለከቷት ልጅ እህታችን ኤደን ለገሠ ትባላለች። ሲዳማ ልማት ማህበርን ጨምር በሲዳማ ክልል ውስጥ የትላልቅ ተቋማት አምባሳደር ናት። የሲዳማ ታሪክ ፤ ባህልና ቋንቋ በዓለም ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ ስሟ ገኗል። ከሲዳማም አልፎ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደተለያዩ ብሔሮች ከተማ እየተዘዋወረች የተለያዩ ብሔሮች ታሪክና ባህል በዓለም አቀፉ ቋንቋ(በእንግሊዝኛ) እየዘገበች ዕንቁ ባህላችን ወደ ዓለም ህዝብ የሚታደርስ ድንቅ ልጅ ናት።
‎ እህታችን ኤዱለገሠ አምላክን የሚትፈራ፤ ሰውንም የሚትወድ፤ የመላውን የኢትዮጵያ ብሔሮችን ታሪክ፤ ቋንቋና ባህል የሚታከብርና ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም የመኖር ባህሪ ያላት የዘመናችን ዕንቁ ሰው ናት።
‎ ነገር ግን ይህችን ትሁት እህታችን በዚህ ሳምንት ከሚትወደው ህዝብ ብርቱ ተቃውሞ ገጥሟታል። ማህበራዊ ሚዲያ ሁሉ እርሷን የሚያሳድድ መረጃ እያሰራጨ ይገኛል። ታዲያ ኤደን ምን አድርጋ ነው የሚትሳደደው የሚል ሰው አይጠፋምና ነገሩ እንዲህ ነው፦
‎ በሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው ውሳኔ በቅጣት የታገዱ ተጫዋቾችን በማሳተፉ ምክንያት የ2017 ኢትዮጵያ ካፕ ሻምፒዮን ተብሎ ዋንጫ የወሰደው የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ በፎርፌ ዋንጫው ለዕለቱ ተጋጣሚው ለወላይታ ዲቻ ይመልስ በሚለው መግለጫ በጣም እንደደነገጠችና በጣም ለሚትወደው ለወላይታ ህዝብ ደግም "የእንኳን ደስ አላችሁ" መልእክት በራሷ ፌስቡክ ፔጇ ለጠፈች። እንስቷ ይህን መልእክት በለጠፈችው በሁለተኛ ደቂቃ ላይ ብሔር ከብሔር ጋር በማጣላት ሥራ የተሰማሩ ወገኖች መልእክቷን በሌላ ተርጎመው screenshot አድርገው ሚዲያ ላይ መሯሯጥ ጀመሩ።
‎ በዩትዩብ፤ በትክቶክና በፌስቡክ የሚከተሏት ወዳጆች unfollow እና unsubscribe እንዲያደርጓት በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወጡ ሰዎች ቁጥራቸው አሸዋ ነው። ከዚያም አልፎ ኤደን ለገሠ አምባሳደር ከሆነችባቸው ተቋማት ሁሉ አምባሳደርነቷ እንዲነሣም ለማድረግ ብዙዎች እንቅስቃሴ ጀምሯል። በሁኔታው እጅጉን የደነገጠችው ኤደን የለጠፈችውን መልክት በፍጥነት ከፔጇ ላይ በማጥፋትና መላውን የሲዳማ ህዝብና የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎችን ይቅርታ በመጠየቅ ነገሩን ለማረጋጋት ብትሞክርም በሰይጣን የሚመሩ ክፉ ሰዎች ይቅርታዋን ለመቀበል ፍቃደኛ አልሆኑም።
‎ ቃል በቃል፦ " የጀግናው የካዎ ጦና ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ። ትናንት ከፌዴሬሽኑ ዘግይቶ በመጣው ውሳኔ ስሜታዊ ሆኜ እናንተን ረሳሁና አፉ በሉኝ። ወንድም የሲዳማ ህዝብ ይወዳችኋል፤ እኔ አንዷ ነኝ።" ከሚለው መልእክቷ ውስጥ እንዴት ጠማማ ትርጉም ይውጣል? እንዴትስ ትኮነናለች? ይህች ልጅ እኮ በመጀመሪያ በፌዴሬሽኑ ውሳኔ ስሜታዊ መሆኗን በመግለፅ የታላቁ የሲዳማ ህዝብ ሃዘን እርሷም አዘነች። ደግሞ ከፈጣሪ የተሰጣት የህዝብ ፍቅር አስገድዷት ለወላይታ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ፍቅሯን ገለፀች። በአጭሩ ከሚያዝነው ህዝብ ጋር የሀዘኑ ተካፋይ እንደሆነችና ከሚደሰተው ህዝብ ጋር ደስታቸውን መጋራቷን ገለፀች። ምክንያቱም ልጅቱ ትክክለኛ ኢትዮጵያዊት ናትና ሁለቱም ህዝቦች ህዝቦቿ ነው። ግን ያለጥፋት ይቅርታ እየጠየቀችና እየወተወተች ላለችው ለዚህች እንስት ሁለቱም ህዝቦች ከጎኗ አልቆሙም። በሲዳማ ህዝብ ስም የሚያባርሩት ጠንክሮ ቀጥሏል። በወላይታ ህዝብ በኩል ደግሞ አንድ ሰው እንኳ ሚዲያ ላይ ወጥቶ አለሁልሽ አላላትም።
‎ በመሆኑም Gifaataa Tube ለመላው የወላይታ ተወላጆች አንድ መልእክት ማስተላለፍ እንፈልጋለን፦ እባካችሁ ሁላችንም ይችን ቀና አመለካከት ያላትን ድንቅ ልጅ በየማህበራዊ ሚዲያዎቿ follow እና subscribe በማድረግ እኛም የወላይታ ህዝብ ከልብ እንደሚንወዳት ፍቅራችን በተግባር ፤ በሥራ እናሳያት።

‎በወላይታ ሁለንተናዊ ሚዲያ አገልግሎት ተዘጋጅቶ በGifaataa Tube የቀረበ፤ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎email - [email protected]
‎website- http://gifaataatube.blogspot.com
‎Youtube- https://youtube.com/
‎Tiktok- https://tiktok.com/.naatu.keettaa
‎ Facebook:- https://www.facebook.com/share/1EZRVzrQtr/
https://www.facebook.com/share/16t5CTL6jo/
https://www.facebook.com/share/16kTnUc3pQ/
https://www.facebook.com/wolayta.dicha.982731
‎telegram- https://t.me/gifaataatube

‎ !‎        ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ አንድ የሆነችውን ኢትዮጵያ ለመፍጠርና ሁሉንም ጠቅልሎ ራሱ ለመግዛት አቅደው በተነሳው ከፍተኛ ውጊያ በየብሔሩ ንጉሥ አንግሠው የሚተዳደር ህዝብ መንግሥታ...
21/06/2025

‎ !
‎ ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ አንድ የሆነችውን ኢትዮጵያ ለመፍጠርና ሁሉንም ጠቅልሎ ራሱ ለመግዛት አቅደው በተነሳው ከፍተኛ ውጊያ በየብሔሩ ንጉሥ አንግሠው የሚተዳደር ህዝብ መንግሥታዊ ሥርዓቱን፣ ባህሉን፣ቋንቋውን፣ ሀብትና ንብረቱን፣በሕይወት የመቆየት ዕድሉንም ጭምር በዐፄው እጅ እያስረከበ ወደ አገዛዙ ይቀላቀል ነበር። የምኒልክ ጦር በኃልና በቁጣ ተሞልቶ በጉልበት እየገባ ግዛትን ሁሉ የምኒልክ እያደረገ ከሰሜናዊ ኢትዮጵያ አቅጣጫ ወደ ደቡብ እየገሰገሰ ሲመጣ አንድ ያልታሰበ አደጋ ገጠመው። ቀይ መሥመር ! እሳተ-ገሞራ! የማይወጣ ግዙፍ ተራራ! ነጎድጓዱ ንጉሥ አስፈሪውና አስደንጋጩ ካዎ ጦና! ባልሽያ ማታ! ጋንጌ ፈረስ! ማጫምያ እና ጎንዳልያ! በቀይ፣ ቢጫና ጥቁር ቀለም ያጌጠ እንደአሸዋ የማይቆጠር ቁጡ ህዝብ! ታላቁ ንጉሥ ካዎ ጦና ጋጋ የሚያስተዳድረው የወላይታ መንግስት!!! በዓፄው ተልዕኮ የመጣው የመጀመሪያው ዙር ጦር በደቡቡ እሳት ባህር ውስጥ ሰጥመው ቀረ። ሁለተኛ ዙርም የተላከው ጦር የማጫምያ ቶራ እራት ሆነ።
‎ የዐፄውን ጦር አላሻገር ያለውን የእሳቱን ባህር ለመጎብኘት ራሱ ዓፄ ምኒልክ ጦር እየመራ መጣ። ከሰው እስከ ንብ በዓፄ ምኒልክ ጦር ላይ ተረባረቡበት። ሸና። ፈራ። ግን ወደኃላ ከተመለሰ በሽንፈት መንፈስ አንገቱን ደፍተው ሌሎችን መግዛት ስለማይችል መሞትን መረጠ። ደጋግመው ሞከረ። የሰው ሕይወት በሁለቱም በኩል ረገፈ። የሰው ደም እንደ ዓባይ ወንዝ ጎረፈ። ካዎ ጦና ብሎም ዓፄ ምኒልክ በግምባር የተሣተፉበት ጦርነት በአልሸነፍ ባይነት ቀጠለ።
‎ በመጨረሻም አፄ ምኒልክ አንድ ነገር አሰበ። ጉልበት ሄጄማ ይህን ንጉሥ ማሸነፍ አልችልም አለ። ሌላም ዘዴ መዘየድ እንዳለበት ገባው። ባንዳ መፈለግ ጀመረ። አገኘም። "የወላይታ ህዝብ ቤቱንና ልጆቹን እጅጉን ስለሚወድ ሕዝቡ ከፊት እየተዋጋ ከኃላ ቤታቸውን በእሳት ብታቃጥል የካዎው ጦር ቤቱንና ልጆቹን ለማትረፍ ወደቤቱ ይሮጣል" የሚትል ምክር በገንዘብ ከተገዛ ባንዳ ተለገሰችለት። የባንዳው ምክር እውን ሆነ። ለዓፄውም ተሳካለት። አሸነፈ። ካዎውንም ያዘ። ሁለቱ ጀግኖች እጅ ለእጅ ተያይዞ እንጦጦ ገቡ።
‎ ዓፄ ምኒልክ ዳግማዊ ጦርነቱን በብዙ ትግል ከረታ በኃላ በጀግናው በወላይታ ህዝብ ዘላለማዊ ቂም ያዘ። ኢትዮጵያ እስካለችበት ዘመን ሁሉ የትኛውም መንግሥት ሲመጣ በተመሳሳይ አቋም የሚተገብረውን በደል ለወላይታ ህዝብ ቀርፆ በአደራ መልክ አስቀመጠ። ከዚህ የተነሳ መንግሥት በሌላ መንግሥት ሲተካም በወላይታ ህዝብ በደል ጉዳይ አይደራደርም። ከዓፄ ምኒልክ ዳግማዊ መንግሥት አገዛዝ ጀምሮ እስከ ብልፅግና መንግሥት በወጥ አቋም ወላይታን የማድቀቅ ሥራ በብቃትና በንቃት እየሠሩ መጥተዋል።
‎ አዎ፣ ከጥንት ጀምሮ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በወላይታ ህዝብ ላይ በተለያዩ መልኩ ጫናዎችን ሲያሳድር መቆየቱ የታሪክ እውነታ ነው። ይህ ጫና የወላይታን ነባር የራስ ገዝ አስተዳደር፣ ባህልና ማኅበራዊ ገጽታዎች ላይ ተጽዕኖ ሲያደርግ ቆይቷል። እስኪ የኢትዮጵያ መንግሥት ምን አይነት በደሎችን በወላይታ ህዝብ ላይ እየሰነዘረ ነው የሚለውን ከብዙ ጥቅቱን እንመልከት፦

‎ 1.

‎ :- የወላይታ ህዝብ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ድረስ በ"ካዎ" በሚባሉ ነገሥታት የሚመራ ጠንካራና የራሱ የሆነ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መዋቅር ያለው መንግሥት ነበረው። ይህ የራሳቸው የራስ ገዝ አስተዳደር የወላይታ ህዝብ የራሱን ዕድል በራሱ እንዲወስን አስችሎ ነበር።
‎ :- በ1894 ዓ.ም. (1900 እ.ኤ.አ.) ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ የደቡብ ግዛቶችን ወደ ኢትዮጵያ ግዛት የማካተት ዘመቻ አካል ሆኖ የወላይታ መንግሥት ከባድ ጦርነት ከተካሄደ በኋላ ተጠቃለለ። ይህ ወረራ የወላይታን የፖለቲካ ነፃነት በማስቆም የበርካታ ዓመታት የፖለቲካ ጫና መጀመሪያ ሆነ። ንጉሥ ካዎ ቶና የመጨረሻው ገለልተኛ ንጉሥ በመሆን ከፍተኛ ተቃውሞ አድርገው ነበር።

‎ 2.

‎ :- ወላይታ የኢትዮጵያ አካል ከሆነች በኋላ፣ በአዲስ አበባ ከተሾሙ ገዥዎች (ሹሞች) ሥር እንድትተዳደር ተደረገች። የወላይታ ባህላዊ የአስተዳደር መዋቅር ተዳክሞ በማዕከላዊው መንግሥት ቁጥጥር ስር ወደቀ። ይህ ደግሞ ህዝቡ የራሱን ጉዳዮች በራሱ የመወሰን ሥልጣን እንዲያጣ አደረገ።
‎ :- ወላይታ በወቅቱ በሲዳሞ ክፍለ-ሀገር ሥር እንደ አውራጃ ሆና እንድትተዳደር ተደረገች። ይህ ውሳኔ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ውክልናውንና ተሰሚነቱን እንዲያጣ አደረገ፣ ምክንያቱም የሌላ ትልቅ ክፍለ-ሀገር አካል በመሆኑ በሀገራዊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የራሱን ድምጽ በበቂ ሁኔታ ማሰማት አልቻለም።
‎ :- ለረጅም ጊዜ የወላይታ ህዝብ በአገር አቀፍ የፖለቲካ ውሳኔዎች ላይ ተገቢውን ተሳትፎና ተፅዕኖ ማድረግ አልቻለም። ይህ ደግሞ በህዝቡ ላይ የፖለቲካዊ ጫና እና የእኩልነት ስሜት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ አድርጓል።

‎ 3.

‎ :- "ወላይታ" የሚለው የህዝቡ እውነተኛ ስም ቢሆንም፣ ከውህደቱ በኋላ "ወላሞ" በሚለው ስያሜ በውጪ አካላት በሰፊው መጠራት ጀመረ። ይህ የስም ለውጥ የአንዳንድ የማንነት ጫናዎች ምንጭ ሆኖ ቆይቷል።
‎ :- በማዕከላዊው መንግሥት ለአማርኛ ቋንቋና ለዋናው የኢትዮጵያ ባህል ቅድሚያ የመስጠት ዝንባሌ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ እንደ ወላይታቶ ዶና ያሉ የአካባቢ ቋንቋዎችና ባህሎች ተገቢውን ዕውቅና እንዳያገኙና እንዲዳከሙ ጫና ፈጥሯል።

‎4. (ከ1995 ዓ.ም. በኋላ)

‎ :- በ1995 ዓ.ም. የተቋቋመው የፌዴራል ሥርዓት ብሔር-ብሔረሰቦች የራሳቸውን ክልል እንዲመሰርቱ መብት ቢሰጥም፣ የወላይታ ህዝብ የራሱን ክልል ለማደራጀት እያደረገ ያለው ጥያቄ ለረጅም ጊዜ ምላሽ ሳያገኝ ቀርቷል። ይህ የፖለቲካዊ ውሳኔ መጓተት በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ጫናና ቅሬታ ፈጥሯል። ህዝቡ የራሱን ባህል፣ ቋንቋና ልማት በራሱ ክልል ውስጥ በተሻለ መንገድ ማስተዳደር እንደሚፈልግ ያምናል።
‎ :- በአሁኑ ወቅት የወላይታ ዞን የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አካል ነው። ይህ ክልል በርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን በአንድ አስተዳደር ስር የሚያካትት በመሆኑ፣ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ክብደቱንና ተሰሚነቱን አጥቷል የሚል ስሜት ሰፊ ነው።
‎ :- በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ፣ የብሔር ጥያቄዎች እና የማንነት ውክልና ጉዳዮች ውስብስብ በመሆናቸው፣ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ጥያቄዎቹን በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ አስቸጋሪ ሆኖበታል።
‎ :- የወላይታ ሕዝብ ቁጥር በኢትዮጵያ ኦሮሞን ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃ የያዘ ነው። ወላይታ ከ26 ሚልዮን ሕዝብ በላይ ነዋሪዎች የሚኖርባት ምድር ናት። ነገር ግን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችና የልማት ቅድሚያዎች ላይ ተፅዕኖ እንዳለ ይታመናል። ከዚህም የተነሳ ወጣቶቿ በስደት ወደዓለም ክፍል ሁሉ ተበትኗል። ለትውልዱ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚችል አንድ ፋብሪካ የላትም። ሌላው ቀርተው የገዛ መሬቷ በሌላ አካባቢ ተወላጅ ኢንቨስተሮች ተቆጣጥረው ነዋሪው በዘመናዊ ባርነት በገዛ ቀዬው ለባዳ ተሸክመው ውሎ የዕለት ጉርስ ይዞ ይገባል።

‎ #ማጠቃለያ

‎ከዐፄ ምኒልክ ወረራ ጀምሮ እስከ አሁኑ የፌዴራል ሥርዓት ድረስ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በወላይታ ህዝብ ላይ የራሱ የሆነ ጫና ሲያሳድር መቆየቱ ግልጽ ነው። ይህ ጫና በዋነኛነት ከራስ ገዝ አስተዳደር ማጣት፣ ደካማ የፖለቲካ ውክልና፣ የማንነት ጥያቄዎችና የልማት ፍላጎቶች ጋር የተያያዘ ነው። የወላይታ ህዝብ የራሱን ማንነትና መብት ለማስጠበቅ የሚያደርገው ትግል ደግሞ የዚህ ጫና ውጤት ነው።

‎በወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ተዘጋጅቶ የቀረበ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎ለበለጠ መረጃ:-
‎email - [email protected]
‎Wwebsite- http://gifaataatubeblogspot.com
‎Youtube- https://youtube.com/
‎Tiktok- https://tiktok.com/.naatu.keettaa
‎ Facebook:- https://www.facebook.com/share/1EZRVzrQtr/
https://www.facebook.com/share/16t5CTL6jo/
https://www.facebook.com/share/16kTnUc3pQ/
https://www.facebook.com/wolayta.dicha.982731
‎telegram- https://t.me/gifaataatube

‎     አንድ እውነት በንግግር ሳይሆን በተግባር ማየት ከቻልክ አንተ ትክክለኛ ተመራማሪ ነህ። እውቀትም እውነትም በትክክለኛው መንገድ ታገኝበታለህ። በንግግርማ ማንኛውም የትናቱ ወጠጤ ራሱን...
18/06/2025

‎ አንድ እውነት በንግግር ሳይሆን በተግባር ማየት ከቻልክ አንተ ትክክለኛ ተመራማሪ ነህ። እውቀትም እውነትም በትክክለኛው መንገድ ታገኝበታለህ። በንግግርማ ማንኛውም የትናቱ ወጠጤ ራሱን በሰማይ አስቀምጦ አያስነካህም። ከአፉ የሚወጣውን ቃል አልፈህ ወደ ታሪኩ ሲትመጣ ግን ነገሩ ጉም መጨበጥ ይሆንብሃል። በአፈ-ታሪክ የመሸወድ ጊዜ ይብቃህ።
‎ ና! ወደ 50+ ነገሥታት ሀገር ወደ ወላይታ ና! በላይና በታች የሚንጫጫ የጫጩቶች ድምፅ አልፈህ ና! የትናንትናዎቹ አዲስ ጎጆቹን አልፈህ ከጥንት ጀምሮ መሠረቱን በዓለት ላይ ወዳደረገው ቤት ወደ ወላይታ ና!
‎በአቅራቢያው ካሉት ወገኖች ቀንጨብ ቀንጨብ አድርጋ በመውሰድ ብሔሯንና ባህሏን ገና እየቀረፀች ካለችው ከግልገሏ አልፈህ ብዙኃኑን አቅፈው ቋንቋውንና ባህሉና በልግስና ተሰጥቷቸው በሥልጣኔ ጎዳና ላይ እንዲራመዱ ወዳደረገው ወደ ወላይታ ና!
‎ መጥቼ ምን የተለየ ነገር አያለሁ ትላለህ? ጥሩ ጥያቄ ነው ያነሳኸው። መጥተህ የሚታየው:-
‎ #1. ከሃምሣ በላይ የወላይታ ነገሥታት ታሪክን ፤ የመንግሥታቸውን ሥርዓት ፤ ዲፕሎማሲያቸውን፤ ድንበር ጠባቂ ብቻ ሳይሆኑ የተለያዩ አናሳ ጎሳዎችን በራሳቸው እያጠቃለሉ ድንበራቸውን ያስፋፉ መሆናቸውን፤ ጀግንነታቸውንና ሥልጣኔያቸውን ትመለከታለህ።
‎ #2. ማርጩዋ ታያለህ። ማርጩዋ ምንድ ነው ልትል ትችላለህ። በዱሮ ገበያ ሥርዓት ሰው የተለያየ ዕቃ ይዘው ወደ አንድ ሜዳ በመሰብሰብ ዕቃን-በዕቃ እየቃያየሩ የሚገበያዩበት ሥርዓት ነበር። ይህንን ሥርዓት በማዘመን በአህጉር ቀዳሚ የሆነውን ማርጩዋ የተባለውን የሀገሩ ገንዘብ በማምረት ዕቃን በገንዘብ የመግዛት ዘመናዊ የገበያ ሥርዓት ያመጣ በአፍሪካ ተቀዳሚ ሀገር ወላይታ ነው። በዚያን ዘመን በማርጩዋ ዓለም አቀፋዊ ንግድ እንደሚደረግና አንድ ማርጩዋ በስድስት ዶላር እንደሚመነዘር ታሪኩ ያረጋግጣል። ና ላሳህ!
‎ #3. ታሪካዊና መዝናኛ ቦታዎችን ትጎበኛለህ። ካዎ ጋሮታ(ቤተ-መንግሥታት)፤ ታሪካዊና ከ70,000 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ ዋሻዎችን፤ በአፍሪካ ደረጃ ረዥም የተባሉ ፏፏቴዎችን፤ ጦሳ ዛርጵያ(የእግዜር ድልድይ)፤ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ሐይቆችን፤ እስከ አጎራባች አፍሪካ ሀገራት ድረስ ተዘርግተው ለሃገራችን ከፍተኛ የገቢ ምንጭ የሆነውን ጊቤ-3 ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ፤ ተክል ድንጋዮችን፤ ጥንታዊና ታሪካዊ ከተሞችን፤ ሙሉ የወላይታ ህዝብ ጥንታዊ የቤት ቁሳቁሶችንና የጦር መሣሪያዎችን የያዙ ሙዚየሞችን፤ በራሱ ዘመን አቆጣጠር መሠረት አዲስ ዓመትን የሚቀበልበት የጊፋታ በዓልን፤ ወዘተ ትመለከታለህ።
‎ #4. ጥንታዊ የወላይታ ህዝብ ሙዚቃ መሣሪያዎችንና ህዝባዊ ዘፈኖችን ታያለህ፤ትሰማለህም። በአፍሪካ አህጉር ከወፎች ዝማሬ በስተቀር በዜማ የሚከፈት የሰው አፍ ባልነበረበት ዘመን የወላይታ ህዝብ ለሠርግ፤ ለደቦ ሥራ፤ ለልደት፤ ለሙሾ፤ ለበዓላትና ለተለያዩ ጉዳዮች እንደየሁኔታቸው የቃል ግጥም በማዘጋጀት ኩነቶችን በዜማ ይገልፁ ነበር። በዚያ ብቻ ለምን ትደነቃለህ? የኩኔቶችን ዜማ የሚደግፍ ላሁኖች ሙዚቃ መሣሪያዎች መሠረት የሆኑ የሙዚቃ መሣሪያዎችን ሙሉ ባንድ አድርገው መፍጠራቸውን መቼ ሰማህ? ድንክያ፤ጫቻ ዛእያ፤ኡልዱዱዋ፤ካምባ፤ካራቢያ፤ዲታ፤ እና የመሳሰሉትን በመፍጠር ከዘመን ቀድሞ በመሠልጠን ዜማቸውን በባህላዊ ባንድ ታጅበው ያቀርቡ ነበር።
‎ #5. ጥንታዊ የወላይታ ህዝብ ባህላዊ ልብሶችን ትመለከታለህ። ሃድያ ተብለው የሚጠራው የወላይታ ብሔር ባህላዊ ልብሶች አጠቃላይ ስያሜ በውስጡ አምስት ዓይነት ባህላዊ ልብሶችን የያዘ ነው። አዎ! የወላይታ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ የሠለጠነና ምሁር ህዝብ ነው። ለለቅሶ የሚለብሰውን ለሠርግ አይለብስም። ለሠርግ የሚለብሰውን ለጦር ሜዳ አይጠቀምም። ንጉሥ የሚለብሰውን ህዝብ አይለብስም። ለሁሉ የየራሱ ባህላዊ ልብስ በአምስት ዓይነት በማዘጋጀት ሥርዓት ባለው መልኩ የተጠቀመ ህዝብ ነው። በዚያን ዘመን የወላይታ ብሔር ቀያይረው ስለለበስ የአፍሪካ ምድር ላይ የልብስ ፋብሪካና ሌላ ልብስ የሚጠቀም ብሔር ያለ እንዳይመስልህ! አአልነበረም። ግን ጠቢቡ የወላይታ ህዝብ ልብሶቹን በእጆቹ ሸምኖ በማዘጋጀት ይጠቀም ነበር። ልብሶቹም:-ጉቱማ ሃድያ፣ ሴሬ ሃድያ፣ ጉማራ ሃድያ፣ ፓታላ ሃድያ እና ዱንጉዛ ሃድያ በመባል ይታወቃሉ። ዕድለኛ ከሆንክ ስትመጣ አይተህ ትመሠክራለህ።
‎ #6. ጥንታዊ ቤተ-እምነቶችን ታያለህ። በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢ ከየትኛውም ብሔር ቀድሞ የክርስቲና እምነት የተቀበለው የወላይታ ህዝብ ነው። ከ700ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማንያን ቤተክርስቲያንን ታያለህ። ከወላይታ ህዝብ የተገኙ አባታችን ሶስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ያረፉበትን መቃብር ታያለህ። በኢትዮጵያ ደረጃ ከሁሉም ቀድሞ የወንጌላውያን አቢያተክርስቲያናት እምነት የተቀበለው የወላይታ ህዝብ ነው። ለአብዘኞቹ የወንጌላዊት ቤተ-እምነቶች እናት የሆነችው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የተጀመረችው ብሎም ስያሜዋን ያገኘችው በወላይታ እምነት አባቶች ነው። በርካታ ነቢያት ፈጣሪ በሰጣቸው ራዕይ መሠረት የሚንትሪ ቤተ አምልኮ መሥርተው ባሁኑ ጊዜ በየቀኑ በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ነፍሳት ወደ ፈጣሪያቸው መንግሥት እንዲቀላቀሉ በማድረግ ላይ ያሉ ታላቅ አገልጋዮች የተወለዱበት ሀገር ወላይታ። በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ኃላፊነት የሚሠሩ ታላላቅ የእስልምና እምነት ተከታዮችና ዕድሜ ጠገብ መስገዶች ያሉበት ሀገር ነው ወላይታ። የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎችን ሙሉ የሚያስተዳድረው ፣ ሰፊ በመንፈሳዊና ማህበራዊ ድጋፎችን በመስጠት የሚታወቀው የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያው የደቡብ አካባቢዎች ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ታገኛለህ። በሐዋሪያት ቤተ እምነት፣ በአድቫንቲስት ቤተ- እምነት፣ በይሆዋ ምስክሮች ቤተ እምነት ፣ ወዘተ የወላይታ ምድር ተቀዳሚ ናት። መጥተህ ካየህ ከሰማኸው ይበልጣል።
‎ #7. በእንግዳ ተቀባይነቱ፣ በአቃፍነቱ፣በለጋስነቱ፣በጀግንነቱ፣በሥራ ወዳድነቱ፣በጥበቡ፣በታታሪነቱ፣በፈጠራ ሥራዎች፣ በምርምር፣ ወዘተ የሚታወቀውን ታላቁን የወላይታ ህዝብን ታያለህ። በእርግጥ የወላይታ ህዝብና ወላይትኛ ቋንቋ የሌለበት የዓለም ክፍል የለም። ቢሆንም መነሻውጋ በመምጣት የሚታየው ህዝብና የሚትሰማው ወላይትኛ የተለየ ደስታ እንደሚሰጥህ ሙሉ እምነት አለኝና ግድ የለም ና!
‎ #8. መጥተህ የሚትመገበው በዓለም ደረጃ ተወዳጅነትን ያተረፈው የወላይታ ባህላዊ ምግብ። አንተ ብቻ መምጣትህን እርግጠኛ ሁን። የወላይታ ህዝብ ሎጎሙዋ፣ ሱልሱዋ፣ቆጭቆጫዋ፣ ባጭራ፤ሼንደራ፣ፕጫታ፣ ሙቹዋ፣ ፖሻሙዋ፣ ብላንዱዋ፣ Cadhdhiyaa፣ፕላ፣ጉርዱዋ፣ እና ከሁሉም በላይ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የጥሬ ስጋ አምሮቱን ለማርካት ወደ እኛ እንዲመጡ ምክንያት የሆነውንና በብዙ ዓይነት ዳጣ በተለየ አቀራረብ የሚቀርበውን፤ የወላይታ አምባሳደርም የሆነውን ቁርጥ ሥጋ በቃኝ እስኪትል ድረስ ልመግብህ ተዘጋጅተው እየጠበቀ ነዉ።
‎ ስትመጣ የመንገድ ችግር የሌለበት፤ ስትደረስ የመብራት፣ የንፅህና ውኃ፣ ንፁህ ማረፊያ ሥፍራ፣ የኔትወርክና የነፃ ዋይፋይ ችግር በፍጹም አይገጥምህም። ዛሬ ያገኘህ ወላይታዊ ወንድምህ ሆኖ በሴኮንድ ይግባባሃል። ወደ ቱሪዝም መዳረሻዎች የሚያጓጉዙ ምቹና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም ደግሞ እንግሊዘኛን ጨምሮ ከሀያ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራትን ቋንቋዎችን አቀላጥፈው የሚናገሩ አስጎብኚዎች ተዘጋጅተው ይጠብቁሃል። ና!
‎ ግን ትመጣለህ ወይስ ዝም ብለህ አስለፈለፍከኸኝ?
‎youtube.com/


ትውልዱም በሀገሩ ሲኮራ፤  ሀገርም በትውልዱ ከፍ ብሎ ስከብር ማየት እጅግ በጣም የሚያስደስት ነው። ያኔ ንጉሣችን ሞቶሎሚ ማንም ጥቃቅንና አነስተኛ በቆሸሸ እጁ እንዳይነካት ከፍ አድርጎ ማንም...
18/06/2025

ትውልዱም በሀገሩ ሲኮራ፤ ሀገርም በትውልዱ ከፍ ብሎ ስከብር ማየት እጅግ በጣም የሚያስደስት ነው። ያኔ ንጉሣችን ሞቶሎሚ ማንም ጥቃቅንና አነስተኛ በቆሸሸ እጁ እንዳይነካት ከፍ አድርጎ ማንም በማይደርስበት ቦታ ያስቀመጣትን ሀገር እርሱን ቀጥሎ የመጡ ነገሥታትም ክብሯን ፤ ታሪኳን፤ ጀግንነቷን፤ ድንበሯን፤ ቋንቋዋንና ባህሏን ከነበረበት ከፍታም ወደላይ ጨምሮ ከፍ በማድረግ ዕንቁ የሆነችውን ሀገሩ ለእኛ አስረክቦልን አለፉ።
እኛ ደግሞ አሁን ተረኞች ነን። ታዲያ ታሪክ መናገር ብቻ ሳይሆን ታሪክ በመሥራት ወላይታችን የዘመናችንም ታላቅና አሰሰፈሪ ሀገርነቷን እንዲታስቀጥል የሚንሠራው የየራሳችን አስተዋጽኦ ማዋጣት ይኖርብናል። ትናንት በአፍሪካ አንደኛ ፀጥታ ኃይል አለኝ ብላ የሚትፎክረው አንዲት ሉዓላዊ ሀገር ጀግናው የጦና ትውልድ በከፊል የአፍሪካ መቀመጫ የሆነችውን ቱንጋ ሲገቡ እንዴት እንደፈሩ በቅርብ ቀናት ያየነው እውነት ነው።
ስለዚህ እኛ ኩሩ ህዝብ፤ የማንነት ጠባሳና የታሪክ ጥላሸት የሌለን ወላይታውያን በዚህ ማንነታችን ሲንኮራ፤ ቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችንና ባህላዊ ሙዚየሞቻችን በየጊዜው መጎበኘትና በዓለም ህዝብ ዓይን ሌንስ እንዲገቡ ማድረጋችን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል። ምክንያቱም የታላቁ የወላይታ ህዝብ ባህል የሆኑ እጅግ ውብና ድንቅ የሆኑ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶችን በላይና በታች የሚኖር ተለጣፊ አካል የራሱ ለማድረግ ብዙ ጥረት እያደረገ ነው። እኛ ደግሞ የደቡብ ባህሎችና የኦሞቲክ ቋንቋዎች መነሻ መሆናችንን ለዓለም ህዝብ ማሳየታችንን መቀጠል ይኖርብናል።
እናመሰግናለን!
youtube.com/

‎  :-‎        የ2017 ዓ. ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ እና ሲዳማ ቡና በአበበ ብቅላ ስታዲየም በሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚፋለሙ መርሐግብር ...
08/06/2025

‎ :-
‎ የ2017 ዓ. ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ እና ሲዳማ ቡና በአበበ ብቅላ ስታዲየም በሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚፋለሙ መርሐግብር ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ሁለቱም ክለቦች እየተዘጋጁና ደጋፊዎቻቸውም ወደተባለው ስታዲየም ለድጋፍ ለመጓዝ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ቆይተው ልክ የተባለው ቀን ስደርስ ደጋፊዎች ጉዞ ጀምሮ መንገዱን ካጋመሱ በኃላ እንደሌባ በሌሊት አንድ አስደንጋጭና ኢፍትሐዊ የሆነ ውሳኔ በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፌስቡክ ይፋዊ ፔጁ ላይ ተለጥፎ ታየ። " ከአቅም በላይ በሆነ" ምክንያት ጨዋታው በዝግ ስታዲየም ይደረጋል ተብሎ ተወሰነ።
‎ የGifaataa Tube ይህን መረጃ ሰምቶ ሁኔታውን ለማጣራት ብዙ የሞከረ ብሆንም ውሳኔውን ያስተላለፈው አካል ሌሊት 5:00 ሰአት ላይ መረጃው በፌስቡክ እንደለጠፈ የውሃ ሽታ ሆነ። ከነጋ በኃላ ይህ መግለጫ የተሰጠበት ጊዜ ድረስ ተቋሙ ሐሳብ ቀይረው ስታዲየሙን ለተመልካች ክፍት እንደሚያደርግ የሚገልፅ ከሆነ የጠበቅን ብሆንም ምንም የተለየ መረጃ ባለማግኘታችን ምክንያት በቀሩት ጥቅት ሰአታት ውሳኔውን እንዲያስተካክልና ረዥም ርቀት በሌሊት ተጉዞ ለድጋፍ አ.አ የገቡ የሁለቱም ክለቦች ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም ገብተው በስፖርታዊ ጨዋነት ክለቦቻቸውን እንዲደግፉ ዕድል እንዲሰጥ፤ ይህ ካልሆነ ደግሞ ተቋሞ ለፈፀመው ጥፋት ተጠያቂ እንደሚሆን ልናሳስብ እንወዳለን።
‎ አንድ ሀገር አቀፋዊ ተቋም እንዴት እንደዚህ ዓይነት የወረደ ውሳኔ ያስተላልፋል? የጨዋታ ጊዜ ሳሌዳ ያዘጋችሁ እናንተ አይደላችሁም? ደግሞ "ከአቅም በላይ በሆነ ጉዳይ .." ተብሎ በድፍኑ በምክንያትነት የቀረበው ለምን ለሕዝቡ በግልፅ አልተገለፀም? ከአቅም በላይ ምን ገጠማችሁ? ያ ብሆንም ጨዋታው ያለተመልካች በዝግ ስታዲየም ይደረጋል የሚባል ከሆነስ ደጋፊዎች ከክልል ከተማዎች ያላነሰ ኪ.ሜ ተጉዞ መንገዱ ካጋመሱ በኃላ ነው የሚታወጀው? ደግሞም በሌሊት 5:00 እንዴትና የት ተሰብስባችሁ ነው ይህን ውሳኔ በቃለጉባኤ ወስናችሁ ያስተላለፋችሁት ወይስ የአንድ ግለሰብ ውሳኔ ነው?
‎ ያም ሆነ ይህ ውሳኔያችሁ ተቋምን በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ ሐሳባችሁን በመቀየር ቀደሞ ሳላልተነገረው በሌሊት ጉዞ በድካም አ.አ የገባውን የሁለቱም ክለቦች ደጋፊ ቡድን በሥነሥርዓት እንዲታስተናግዱ በጥብቅ እናሳስባለን።
‎ሰኔ 1/2017 ዓ.ም
‎Gifaataa Tube
‎ universal media service center

‎  :-‎          ክለባችን ዲቻ በየዓመቱ ለኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ፍጻሜ ዋንጫ በሚያደርገው ጨዋታ እንዳያሸንፍና ዋንጫም እንዳያነሳ በተቀናጀ ኃይል ግፍ እየተፈፀመ ውጤት በማሳጣትና በ...
05/06/2025

‎ :-
‎ ክለባችን ዲቻ በየዓመቱ ለኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ፍጻሜ ዋንጫ በሚያደርገው ጨዋታ እንዳያሸንፍና ዋንጫም እንዳያነሳ በተቀናጀ ኃይል ግፍ እየተፈፀመ ውጤት በማሳጣትና በዚያ በደል ምክንያት ተጨዋቾችና ደጋፊዎች በንዴት ተነሳስቶ በሚያደርጉት ተግባር ክለቡን ከፍተኛ የገንብና ሌሎችም የቅጣት ዓይነቶችን እየቀጡ መቆየታቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው።
‎ በመሆኑም በዚህ ዓመት ጨዋታ ጊዜ ከጉዞ ጀምሮ እስከ ስታዲየም ድረስ በሚናደርገው ቆይታችን በኛ ላይ ሰበብ የሚፈልግ አካል ነጥብ እንዳያገኝ ማንም ደጋፊ ዕድል እንዳይሰጥ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ለክረባችን የሚገባውን ሞራል እንደተለመደው በመዝሙርና በዲቻ ዘፈን ከመስጠት ውጪ ከሌላው ክለብ ጋር መበሻሸቅ አያስፈልግም። በሌላ በኩል የሚመጣ ማንኛውም ያልተገባ ተግባርና ንግግር ካለ በተቻላችሁ መጠን በaudio & video ቀርጻችሁ በመያዝ ወደሚመለከተው አካል በመቅረብ በህግ እንዲጠየቅ ከማድረግ ውጪ አፀፋውን ለመመለስ ተብሎ ስህተት ውስጥ በመግባት ክለባችን እንዲቀጣ ማድረግ የለብንም።
‎ አንጋፋው ክለባችን ዲቻ እንደሚያሸንፉና ዋንጫውን እንደሚያነሱ እርግጠኞች ነን። ስለሆነም የተሸነፈው ክለብና ደጋፊዎቹ ከፍተኛ የስሜት ጉዳት ውስጥ ስለሚወድቁ የድል ጭፈራችንና የደስታ አገላለፃችን አናድዷቸው የተለመደውን ግርግር ለመቀስቀስ ሊሞክሩ ይችላሉና መፍትሄው ስማቸውን ሳንጠራ፤ ውድቀታቸውን ሳናውጅ፤ ሞራላቸው ላይ ሳንረማመድ ዓላማውን በድል ያደረገ ንፁህ የደስታ አገላለጽ በዎዜ ዘፈናችን መግለጽ ነው ።
‎ ፈጣሪ አምላክም ይጠብቀን። በሰላም ተጉዘን፤ ጨዋታውንም በስፖርታዊ ጨዋነት በሠላምና በድል አጠናቅቀን የድካማችን ውጤት የሆነውን ዋንጫ በክብር አንስተን በደስታ ወደቀዬአችን እንዲንመለስ ይርዳን።
‎ ይህን መልእክት ሼር አድርጋችሁ ለሁሉም ዲቻ ደጋፊዎች እንዲደርስ አድርጉ።
‎ ድልና ድምቀት ለጦና ንቦች!

Wolaytta Naatu Keettaa

ቀኑ:- የፊታችን እሁድጉዞ:_ ወደ ቱንጋትራንስፖርት :- በነፃዓላማ :- የጦና ንቦችን ለመደገፍመስፈርት :- የዲቻ መለያ ቲሸርት መልበስ                 የወላይታ ባንዲራ መያዝ   ...
03/06/2025

ቀኑ:- የፊታችን እሁድ
ጉዞ:_ ወደ ቱንጋ
ትራንስፖርት :- በነፃ
ዓላማ :- የጦና ንቦችን ለመደገፍ
መስፈርት :- የዲቻ መለያ ቲሸርት መልበስ
የወላይታ ባንዲራ መያዝ
በዱንጉዛ መድመቅ
የወላይትኛ ዉዝዋዜ (ከቻሉ)
የዲቻ ሙዚቃ ማቅለጥ (የግድ)
ማሳሰቢያ :- እኛ የጦና ንቦች ዋንጫ ይዘን በድልና በደስታ ወደ ውብቷ ወ/ሶዶ ከተማ ሲንገባ ደማቅ አቀባበል ማድረግ በተለያዩ ምክንያቶች የቱንጋ ጉዞ ላላደረጉ ወላይታውያን ግዴታ ነው ።
አያውቁንም እኛን አያውቁንም
ላላወቁን የጦና ንቦች ነን!

Wolaytta Naatu Keettaa

 ) .)ወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ በይፋ የተመሰረተው በ2001 ዓ.ም.(በጎርጎሮሳዊው 2008/2009) ነው። ክለቡ የተቋቋመው በወቅቱ በወላይታ ልማት ማህበር (ወ.ል.ማ) አማካኝነት ሲሆን፣ ...
29/05/2025

)

.)
ወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ በይፋ የተመሰረተው በ2001 ዓ.ም.(በጎርጎሮሳዊው 2008/2009) ነው። ክለቡ የተቋቋመው በወቅቱ በወላይታ ልማት ማህበር (ወ.ል.ማ) አማካኝነት ሲሆን፣ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማን መነሻ በማድረግ ነው። ክለቡ ሲመሰረት ቀደም ሲል የነበረውንና የበርካታ ደጋፊዎች ትዝታ የነበረበትን የወላይታ ቱሳ እግር ኳስ ክለብን በመተካት እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። የምስረታው ዋነኛ አላማም የወላይታን ወጣቶች የስፖርት ተሳትፎ ማሳደግና አካባቢውን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስፖርቱ ዘርፍ ተወዳዳሪ ማድረግ ነበር።

(2001 - 2005 ዓ.ም.)
ከተመሰረተ በኋላ ወላይታ ዲቻ ጉዞውን የጀመረው ከታችኛው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሊግ እርከኖች ነበር። ክለቡ በእነዚህ ሊጎች ውስጥ ጠንካራ ተፎካካሪነት በማሳየትና ስኬታማ ውጤቶችን በማስመዝገብ በፍጥነት መሻሻል ችሏል። በደጋፊዎቹም ከፍተኛ ድጋፍ እየተደረገለት በየደረጃው በማሸነፍ በ2005 ዓ.ም. መጨረሻ (በጎርጎሮሳዊው 2013 አጋማሽ) የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ (ያሁኑ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ) ተካፋይ ለመሆን በቅቷል። ይህም ማለት ክለቡ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መሳተፍ የጀመረው በ2006 ዓ.ም.(በጎርጎሮሳዊው 2013/2014) የውድድር ዘመን ነው።

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ (2006 ዓ.ም. - እስካሁን)
ወደ ፕሪምየር ሊጉ ከገባበት ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ ወላይታ ዲቻ "የጦና ንቦች" በሚለው ቅጽል ስሙ እየታወቀ ጠንካራ ተፎካካሪ መሆኑን አስመስክሯል። ክለቡ በሊጉ ለበርካታ አመታት የቆየ ሲሆን በተለያዩ የውድድር ዘመናትም በመካከል እና የላይኛው የደረጃ ሰንጠረዥ ክፍል ውስጥ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ታይቷል። የክለቡ ደጋፊዎች በሀገር ውስጥ ከሚገኙ ቀናተኛ እና ስርአት ካላቸው ደጋፊዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን የሜዳቸውንም ድባብ ለተጋጣሚ ቡድኖች ፈታኝ ያደርጉታል።

(2009 ዓ.ም.)
የወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ በታሪኩ ያስመዘገበው ትልቁ ስኬት በ2009 ዓ.ም. (በጎርጎሮሳዊው 2017) የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫን (የቀድሞው የኢትዮጵያ ዋንጫ) ማንሳቱ ነው። በዚህ የውድድር ዘመን እጅግ አስደናቂ ብቃትን ያሳዩት "የጦና ንቦች" በፍጻሜው ጨዋታ መከላከያ (ዲፌንስ ፎርስ) ክለብን 1ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ታላቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ ከፍ ማድረግ ችለዋል።

(2010 ዓ.ም.)
የ2009 ዓ.ም. የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ድል ወላይታ ዲቻ በቀጣዩ ዓመት ማለትም በ2010 ዓ.ም. (በጎርጎሮሳዊው 2018) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያን እንድትወክል እድል ሰጥቷታል። በዚህ የአህጉራዊ መድረክ ላይ ወላይታ ዲቻ ከብዙዎች ያልተጠበቀ አስደናቂ ጉዞ አድርጓል። በተለይም በመጀመሪያው ዙር የግብጹን ሀያል ክለብ ዛማሌክ ኤስ.ሲ.ን በሜዳው 2ለ1 በማሸነፍና በመለያ ምት በመርታት ወደ ምድብ ድልድሉ ማለፍ ችሏል። ምንም እንኳን የዛማሌክን ድል በሜዳው ቢያስመዘግብም ከሜዳ ውጪ በተደረገው ጨዋታ ተሸንፎ የነበረ ቢሆንም በመለያ ምት ማሸነፉ ትልቅ ታሪክ ነበር። ይህ ውጤት በኢትዮጵያ ክለቦች የአፍሪካ ውድድር ታሪክ ውስጥ ከደማቅ ስኬቶች አንዱ ተደርጎ ይቆጠራል። በምድብ የማጣሪያ ጨዋታዎችም ልምድ ካላቸው የአፍሪካ ክለቦች ጋር ተጫውቶ ልምድ ቀስሟል።

(2011 ዓ.ም. - እስካሁን)
ከአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳትፎ በኋላም ወላይታ ዲቻ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳትፎውን የቀጠለ ሲሆን፣ ሊጉን ተወዳዳሪ እና ጠንካራ ከሚያደርጉ ክለቦች መካከል አንዱ ሆኖ ቀጥሏል። ክለቡ በተለያዩ ጊዜያት በአሰልጣኝ እና በተጫዋቾች ስብስቡ ላይ ለውጦችን እያደረገ የውድድር ብቃቱን ለማሻሻል ጥረት ያደርጋል። እስከ አሁን ባለው የ2017 ዓ.ም. (በጎርጎሮሳዊው 2024/2025) የውድድር ዘመንም በሊጉ በመሳተፍ ላይ ይገኛል።



#ስታዲየም፡_ ክለቡ በዚህ ልክ በአፍሪካ ደረጃ ግምባር ቀደምና ጠንካራ ክለብ ቢሆንም የራሱ የሆነ ምቹ ሜዳ የለውም።።
#ደጋፊዎች፡_ "የጦና ንቦች" በመባል የሚታወቁት ደጋፊዎቹ ለክለቡ ያላቸው ፍቅር እና ድጋፍ ከፍተኛ ነው። የወላይታን ባህል በሚያሳዩ አለባበሶች እና ጭፈራዎች ስታዲየሙን ያደምቃሉ።
፡_ ከእግር ኳሱ ጎን ለጎን የወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ በተለይም በወንዶች ቮሊቦል ስኬታማ ቡድን ያለው ሲሆን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ ዋንጫዎችን አሸንፏል።

በማጠቃለያው ወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ በአንጻራዊነት በአጭር እድሜው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ የራሱን አሻራ ያሳረፈ፣ በተለይም በ2009 ዓ.ም የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ድሉ እና በ2010 ዓ.ም በአፍሪካ መድረክ ባሳየው ድንቅ ብቃት የሚታወስ ክለብ ነው።
Habte Nibrete Dicha
Wolaytta Naatu Keettaa
Gifaataa Tube
Gifaataa Gallery
Wolayta Dicha
የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና
ኢሚግሬሽን- ወላይታ ሶዶ
Kawo Dagato Kumbe
youtube.com/

የተከበራችሁ የወላይታ ዞን ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች የተለያዩ የግል ድርጅቶች መሪዮች እና ባለቤቶች የወላይታ ዲቻ እሁድ ሰኔ 1 ከሲዳማ ቡና ጋር ለሚጫወቱት የዋንጫ ጨዋታ ከወዲሁ አስፈላጊውን...
27/05/2025

የተከበራችሁ የወላይታ ዞን ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች የተለያዩ የግል ድርጅቶች መሪዮች እና ባለቤቶች

የወላይታ ዲቻ እሁድ ሰኔ 1 ከሲዳማ ቡና ጋር ለሚጫወቱት የዋንጫ ጨዋታ ከወዲሁ አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት እና ትብብር በማድረግ ለምሳሌ መኪና፣ ባንዲራ እና የዎላይታን ህዝብ ማንነት የሚያሳውቅ ዱንጉዛ እገዛ ከወዲሁ ቢጀመር መልካም ነው።

ክለባችን ወላይታ ዲቻ ዋንጫውን ይዞ እንዲመለስ ዘንድ ሙሉ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል።

አስፈላጊው ሁሉ ዝግጅት እና ትብብር ከተደረገ እና ተጓዥ ደጋፊዎችም በሜዳው ተገኝተው ለተጨዋቾቹ ድጋፍ ሞራል ቢሰጡ እና አስፈላጊው ሁሉ ትብብር ቢደረግ ዲቻ ዋንጫውን ይዞ እንደሚመለስ ትልቅ እምነት እና ተስፋ አለን

ምክንያቱም ክለባችን ዲቻ ከዚህ በፊት ዛማሊክን እዛው በሀገሩ እና እዚህ በሀገራችንም ጭምር አሸንፎ የማይፋቅ ታላቅ ድልን ማስመመዝገቡ ትልቅ ምስክርነት ነው። ድል ለወላይታ ዲቻ 💪
ኑናራ ዲያጌ ኡባ ጦንያጋ

27/05/2025

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gifaataa Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gifaataa Tube:

Share