Wolaita Television Office /ወላይታ ቴሌቪዥን ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Wolaita Television Office /ወላይታ ቴሌቪዥን ጽ/ቤት

Wolaita Television Office /ወላይታ ቴሌቪዥን ጽ/ቤት This is the official Wolaita Television page where you can get all the latest news.

This is the official Wolaita Television page - where you can get all the latest news in different language. You can follow us on:
https://t.me/wolaitatelevision

የወላይታ ዞን አስተዳደር አማካሪዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በሶዶ ከተማ የሚሠሩ የአስፋልት መንገድ ሥራዎችን በሚመለከት ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አደረጉ።ወላይታ ሶዶ፣ ጥር ...
28/01/2025

የወላይታ ዞን አስተዳደር አማካሪዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በሶዶ ከተማ የሚሠሩ የአስፋልት መንገድ ሥራዎችን በሚመለከት ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አደረጉ።

ወላይታ ሶዶ፣ ጥር 19/2017 (ወቴቪ)

የወላይታ ዞን አስተዳደር አማካሪዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በሶዶ ከተማ የሚሠሩ የአስፋልት መንገድ ሥራዎችን በሚመለከት ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አደረጉ።

አቶ ተመስገን ታደሰ በሶዶ ከተማ ከኮካቴ እስከ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከከንቲባ አደባባይ እስከ አረካ ማዞሪያ የሚሠሩ የአስፋልት ሥራ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብና የጥራት ደረጃ በሚሠሩበት ሁኔታ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አድርገዋል።

በምክክሩ በአዎንታ ከተነሱ ጉዳዮች የተለያዩ ተቋማት እና የከተማው ነዋሪዎች ድጋፍ ማግኘቱ የሚጠቀስ መሆኑ ተነስቷል።

የግንባታ ሥራው በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ለሥራው እንቅፋት የሚሆኑ በመንገድ ዳር ያሉ መሠረተ ልማቶችን በፍጥነት ማንሳት እንደሚገባ የተነሳ ሲሆን የመንገድ፣ የቴሌ የመብራት እና የውሃ ተቋማት መናበብ ያስፈልጋል ተብሏል።

በኮንትራክተሩ በኩል በሙሉ አቅሙ እንዳይንቀሳቀስ እንቅፋት የሚሆኑ ማናቸውም ጉዳዮች እንዳይኖሩ መሠራት እንዳለበትም ተነስቷል።

በማጠቃለያም የዞኑ ዋና አስተዳደር አማካሪዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን እያንዳንዱ ባለድርሻ አካል የሚጠበቅበትን በመወጣት ለሥራው ስኬታማነት ርብርብ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በምክክሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ፣ የሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ፣የየተቋማቱ የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች፣ የፕሮጀክቶቹ ተቋራጮች ተወካዮች
እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ተከፈተ***********ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰብዓዊ...
27/01/2025

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ተከፈተ
***********
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ከፈተ።

ማህበሩ በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል ባካሄደው መርሐ-ግብር የሰብዓዊነት ትምህርት ቤቱን መከፈት አብስሯል።

በመርሐ-ግብሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶን ጨምሮ የመንግሥት የስራ ሀላፊዎች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮችና አምባሳደሮች ተገኝተዋል።

ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የሰብዓዊነት ትምህርት ቤቱ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሀብት በማፍራት ጉልህ ሚና ይጫወታል።

ትምህርት ቤቱ ሰብዓዊነትን የተላበሰ ትውልድ ለማፍራትና በተለያዩ ምክንያቶች ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

ማህበሩ የሰብዓዊነት ተግባሩን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚረዳውም ምክትል አፈ ጉባኤዋ ጠቅሰዋል።

በመሆኑም መንግስት ማህበሩ ያቀደውን ተግባር እንዲያሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ጸሐፊ አበራ ሉለሳ በበኩላቸው፥ የትምህርት ቤቱ ዋና ዓላማ በሰብዓዊነት የታነጸ ትውልድ ማፍራት ነው ብለዋል።

የትምህርት ካሪኩለሙ ተዘጋጅቶ ማለቁንና ከነገ ጀምሮ ምዝገባ የሚካሄድ መሆኑንም አመላክተዋል።

ትምህርቱ ሰብዓዊነትን የተመለከቱ ዘጠኝ ዓይነት ኮርሶች እንዳሉት ጠቅሰው፤ ትምህርቱን በአካል እና በበይነ መረብ መከታተል እንደሚቻል ገልጸዋል።

ትምህርቱ ለአንድ ዓመት የሚሰጥ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል።

ትምህርቱን የሚሰጡት መምህራን ሰብዓዊነት የሚገዳቸው እና በህብረተሰቡ ዘንድ ጥሩ ተቀባይነት ያላቸው እንደሆኑም ተናግረዋል።
# ኤፍ ኤም ሲ

አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2ኛ ዙር የእጣ ማውጣት መርሐ-ግብር ተከናወነ*******የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች 19 የነበሩ ቢሆንም፤ ውድድሩ ከተጀመረ በኋላ 1...
27/01/2025

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2ኛ ዙር የእጣ ማውጣት መርሐ-ግብር ተከናወነ
*******

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች 19 የነበሩ ቢሆንም፤ ውድድሩ ከተጀመረ በኋላ 18 መሆናቸው ይታወቃል።

የተሳታፊ ክለቦች ቁጥር 18 መሆኑን ተከትሎ እንዲሁም ተስተካካይ ጨዋታችን ለማስቀረት የ2ኛውን ዙር (ከ20ኛ እስከ 36ኛ ሳምንት) አዲስ እጣ ማውጣት ዛሬ ጥር 19/2017 በአዳማ መከናወኑን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር መረጃ ያመለክታል።

ሙሉ መርሐ-ግብሩ ተያይዟል፦
# EBC SPORT
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

"የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማምጣት ራዕይን ለማሳካት የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፉበታል ተብሎ ይጠበቃል" ክቡር አቶ  አደም ፋራህ የብልፅግና ...
27/01/2025

"የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማምጣት ራዕይን ለማሳካት የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፉበታል ተብሎ ይጠበቃል" ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት

ከጥር 23 አስከ 25 በሚካሄደው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማምጣት ራዕይን ለማሳካት የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፉበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ።

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤን በማስመልከት መግለጫ የሰጡት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጉባኤውን የተሳካ ለማድረግ አብይ እና ንዑሳን ኮሚቴዎች ተደራጅተው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን እና በአሁኑ ወቅትም ዝግጅቱ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

“ከቃል እስከ ባህል” የሚለው የጉባኤው መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ ተልዕኮን በአግባቡ የሚገልጽና ፓርቲው በጉባኤው፣ በፕሮግራሞቹ እና በምርጫ ወቅት የገባቸውን ቃሎች እና ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች በስኬት ተግባራዊ ማድረጉን እና የፓርቲውን ቀጣይ አቅጣጫ አመላካች መሆኑንም ነው የተናገሩት።

ጉባኤው በሶስት ምክንያቶች ከፍተኛ ትኩረትን እንደሚስብ የገለጹት አቶ አደም ታላቅ ህዝብና ሀገርን የሚመራ ፓርቲ የሚያደርገው ጉባኤ መሆኑ አንዱ ትኩረት የሚስብበት ምክንያት ነው ብለዋል።

15 ነጥብ 7 ሚሊየን አባላት ያሉት ከአለማችን ግዙፍ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው እና በሁሉም መስኮች ስኬቶችን እያስመዘገበ የመጣው ብልጽግና ፓርቲ የሚያካሂደው ጉባኤ መሆኑ በራሱ ትኩረት እንዲሰጠው ያደርገዋል ብለዋል አቶ አደም።

በጉባኤው ፓርቲውን እና መንግስትን የሚያጠናክሩ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀመጠውን የፓርቲውን ራዕይ እውን ማድረግ የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይወሰናሉ ያሉት አቶ አደም ቀጣይ አቅጣጫዎችም ይቀመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቀዋል፡፡

በጉባኤው 1ሺ 700 በድምጽ የሚሳተፉ እንዲሁም ያለ ድምጽ የሚሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች እና የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች እንደሚሳተፉም ተገልጿል።

15 የሚደርሱ ከተለያዩ የአለም ሀገራት የእህት ፓርቲ ተወካዮችም በጉባኤው በመሳተፍ አጋርነታቸውን ያሳያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተጠቁሟል።


አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲካሄድ የቆየዉ የመጀመሪያው የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ልማት ፕሮግራም የምዘና ዉድድር በወላይታ ዞን አሸናፊነት ተጠናቀቀወላይታ ሶዶ፣ ጥር 19/2017 ዓ.ም ላለፉት ቀና...
27/01/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲካሄድ የቆየዉ የመጀመሪያው የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ልማት ፕሮግራም የምዘና ዉድድር በወላይታ ዞን አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ወላይታ ሶዶ፣ ጥር 19/2017 ዓ.ም ላለፉት ቀናት በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመጀመሪያው የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ልማት ፕሮግራም የምዘና ዉድድር በዛሬው ዕለት በወላይታ ዞን አሸናፊነት ተጠናቋል።

በዉድድሩ ማጠናቀቂያ ለፍፃሜ በተደረገው የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ጨዋታ የወላይታ ዞን የኣሪ ዞን አቻዉን 1 ለ 0 በሆነ ዉጤት የረታው ሲሆን ለደረጃ በተደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ ጋሞ ዞን ጎፋ ዞንን 5 ለ 0 በመርታት ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቋል።

የጎፋ ዞን በውድድሩ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

በዉድድሩ ማጠቃለያ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ም/ቢሮ ኃላፊና የኃላፊው ተወካይ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ ዉድድሩ በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

በዉድድሩ በሀገር አቀፉ ዉድድር ክልሉን የሚወክሉ ስፖርተኞች መገኘታቸውን፣ የእርስ በእርስ ግንኙነትና አብሮነት መጠናከሩን፣ ተተኪ ወጣቶች መገኘታቸውን እንዲሁም ፕሮጀክቶችን ለመገምገም ዕድል መፈጠሩን አስረድተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የስፖርት ምክር ቤት ፀሐፊ አቶ ጎበዜ ጎዳና በበኩላቸው ሀገራችን ወደ ለዉጥ ሂደት ከገባች በኋላ በስፖርቱ ዘርፍ ያጋጠመውን ስብራት ለመጠገን በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።

ከጥር 27 ጀምሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የስልጠና ልማት ፕሮግራም የምዘና ዉድድር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በ 9 የስፖርት አይነቶች እንደሚሳተፍ ተገልጿል።

ለዉድድሩ ስኬት ልዩ ልዩ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ዕዉቅናና ሰርተፊኬት ተሰጥቷል።

ዉድድሩ ክልላዊ አንድነት እና የእርስ በእርስ ትስስር እንዲፈጠር ከማድረጉም በላይ ታዳጊዎች ወንድማማችነትና ህብረ-ብሄራዊ አንድነታቸዉን እንዲያጠናክሩ ዕድል መፍጠሩ ተገልጿል።

አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

ትራምፕ ሰነድ አልባዎችን እጅ እግራቸውን በሰንሰለት አስጠፍሮ ወደ ሀገራቸው ማባረር ጀምሯልወላይታ ሶዶ፣ ጥር 19/2017(ወቴቪ) USAID ለቀጣይ 90 ቀናት ማንኛውም ዓይነት ድጋፍ ለውጭ ሀ...
27/01/2025

ትራምፕ ሰነድ አልባዎችን እጅ እግራቸውን በሰንሰለት አስጠፍሮ ወደ ሀገራቸው ማባረር ጀምሯል

ወላይታ ሶዶ፣ ጥር 19/2017(ወቴቪ) USAID ለቀጣይ 90 ቀናት ማንኛውም ዓይነት ድጋፍ ለውጭ ሀገራት እንዳያደርግም ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ትላንት የኮሎምቢያ ፕሬዚዳንት Gustavo Petro አንድ ታሪክ ሰርተዋል:: ዶናልድ Trump በገባው ቃል መሠረት ስደተኛችን ወደየመጡበት ማበረር ጀምሯል::

ብራዚላዊያንን እጅ እግራቸውን በሰንሰለት አስሮ ወደ ቤታቸው ሸኝቷል:: ብራዚላዊያንን ስሸኝ በመንገደኞች አውሮፕላን ነበር:: የሚያሳፍረው ግን ስደተኞቹ ሀገራቸው ስደርሱ እንደወንጀለኛ እጅ እግራቸው እንደተሰረ ነበር:: ቢያንስ ሀገራቸው ደርሰው አውሮፕላኑ እንዳረፈ ለሰው ልጅ ክብር ስባል ሰንሰለቱን ፈተው ከህዝባቸው ጋር እንድቀላቀሉ ማድረግ ይችሉ ነበር:: አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ ግን እጅ እግራቸው ታስሮ ከሕዝባቸው ጋር እንድቀላቀሉ ተደርጓል::

ልክ እንደ ብራዚላዊያን ሁሉ ከታች በፎቶ እንደሚትመለከቱት ኮሎምቢያያዊያንም እጅ እግራቸው በሰንሰለት ታስረው ወደ ሀገራቸው ልሸኙ አውሮፕላን እየተሳፈሩ ነው:: የነዚህ ከብራዚል የሚለየው በጦር አውሮፕላን መጫናቸው ነበር::

አውሮፕላኑ መነሳቱ የተነገረው የኮሎምቢያ መንግስት "በዚህ ሰውን ልጅ ክብር በሚነካ መልኩ ዜጎቼን አልቀበልም" በማለት የአየር ክልሉ ዘግቶ ዜጎቹን በክብር ለመቀበል ፕሬዝዳንሻል ፕሌን ወደ አሜሪካ የላከ ቢሆንም "እንደት የሃያሏን አሜሪካ ፕረዚዳንት ትዕዛዝ አታከብሩም" ያለው Trump በፍጥነት ከኮሎምቢያ ወደ አሜሪካ ሚገቡ ምርቶች ላይ የ25% ታሪፍ ጭማሪ፣ የኮሎምቢያ ባለስልጣናት ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ክልከላ እና የኢኮኖሚ ማዕቀብ ስጥል፣ የኮሎምቢያ ፕረዚዳንት Gustavo Petro በበኩሉ ከአሜሪካ ወደ ኮሎምቢያ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ50% ታሪፍ ጭማሪ ጥሏል::

ትራምፕ አሁን የጀመረው የሰውን ሰብዓዊ ክብር በማያከብር መልኩ ስደተኞችን ወደ መጡበት የመሸኘት ዘመቻ ሁሉን ሀገራት መነካካቱ የማይቀር በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ምን ቢሆኑ ምን ቢያደርጉ ከመሰል ችግር ልያመልጡ ይችላሉ?
ከተለያዩ ምንጮች
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ

https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/

የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw

ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/wolaitatelevision

ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ

https://twitter.com/WolaitaTV?s=09

ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ይበልጥ ተቀራርበው መሥራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።*********   ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)"የላቀ ...
27/01/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ይበልጥ ተቀራርበው መሥራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
*********
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)
"የላቀ አገልግሎት ፤ ደስተኛ ደንበኛ" በሚል መሪ ቃል የደንበኞች አገልግሎት ወርን በተለያዩ ኹነቶች እያከበረ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በወለይታ ሶዶ ከተማ ተገኝቶ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይቷል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ፤የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቅርንጫፍ እና ሪቴይል የባንክ አገልግሎት ኤክስኪውቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ደረጀ ፉፋ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደቡብ ምእራብ ሪጅን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉነህ ለማ እና የወላይታ ሶዶ ዲስትሪክት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የክልሉን የልማት ሥራዎችን ይበልጥ መደገፍ በሚችልባቸዉ ጉዳዮች ዙሪያ፤ በርዕሰ መስተዳድሩ ጽህፈት ቤት ምክክር አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ጥላሁን ከበደ በቱሪዝም፣በግብርና፣በብድር አቅርቦት እንዲሁም በባንክ አገልግሎት ተደራሽነት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን የባንክ አገልግሎት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቅርንጫፍ እና ሪቴይል የባንክ አገልግሎት ኤክስኪውቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ደረጀ ፉፋ በበኩላቸው በተለያዩ ዘርፎች አብሮ ለመሥራት የቀረበው ፍላጎት ትክክል መሆኑንና በተለይም በተደራሽነት በኩል ባንኩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፤ የዲጅታል ባንክ አገልግሎት አማራጮችን በስፋት ለማቅረብ እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡

የወላይታ ሶዳ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ፍጹም አላሎ በበኩላቸው ዲስተሪክቱ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጋር በቅርበት በመሥራት የተነሱትን ጉዳይች ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሁሉም ዲስትሪክት ድ/ቤቶችና በተለያዩ ከተሞች "የላቀ አገልግሎት ፣ ደስተኛ ደንበኛ" በሚል መሪ ቃል የደንበኞች አገልግሎት ወርን እያከበረ ይገኛል ሲል ባንኩ በኦፊሴላዊ ፌስቡክ ገጹ ላይ አስነብቧል፡፡
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የአየር አምቡላንስ አገልግሎት የመጀመር ፍላጎት እንዳለ ተገለጸ ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19፣ 2017 (ወቴቪ) በኢትዮጵያ የአየር አምቡላንስ አገልግሎት ለመጀመር ፍላጎት መኖሩን እና ለዚህም ዝግጅ...
27/01/2025

የአየር አምቡላንስ አገልግሎት የመጀመር ፍላጎት እንዳለ ተገለጸ

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19፣ 2017 (ወቴቪ) በኢትዮጵያ የአየር አምቡላንስ አገልግሎት ለመጀመር ፍላጎት መኖሩን እና ለዚህም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በሚኒስቴሩ የህክምና አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኢሉባቦር ቡኖ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደተናገሩት÷ የአየር አምቡላንስ አገልግሎትን ለማስጀመር የዶክመንት ዝግጅት ተደርጓል፡፡

ለትግበራው የገንዘብ ሚኒስቴር፣ አየር ሀይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን እና ሂደቱም ጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በመጀመሪያው ለሀገር ውስጥ ህክምና አንድ ሄሊኮፕተር እና ለውጭ ሀገር የህክምና አገልግሎት ደግሞ አንድ ፊክስድ ዊንግ የአየር አምቡላስ ለመግዛት መታቀዱን ገልጸዋል።

አገልግሎቱ በግጭት፣ በእሳት አደጋ፣ የተሟላ አገልግሎት ከሚሰጡ ጤና ተቋማት በርቀት ላይ ያሉ አልያም በሌሎች ምክንያቶች ከፍተኛ የድንገተኛ ህክምና ቢያስፈልግ ታካሚዎችን በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ለማድረስ እንደሚያስችል ዶ/ር ኢሉባቦር ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም አስፈላጊ የህክምና ግብዓቶችን እና ባለሙያዎችን በአጭር ደቂቃ ከተፈለገበት ቦታ ለማድረስ ያግዛልም ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል ፊክስድ ዊንግ የአየር አምቡላንስ ዜጎች ድንገተኛ ከባድ ህክምና ቢያጋጥማቸው እና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ለመታከም አጭር ደቂቃ ቢኖራቸው እነሱን በፍጥነት ለማድረስ ያለመ ነው ብለዋል ፡፡

እንዲሁም በመደበኛ አውሮፕላን መንቀሳቀስ የማይችል ሰው በዚሁ የአየር አምቡላንስ ማሽን ላይ የጤና ባለሙያዎች የህክምና እርዳታ እየሰጡት ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ መታከም ይችላልም ብለዋል፡፡
# ኤፍ ኤም ሲ

ምክር ቤቱ ሁለት የብድር ስምምነቶችን አፀደቀወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አንደኛ ልዩ ስብሰባ መንግስት ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ጋ...
27/01/2025

ምክር ቤቱ ሁለት የብድር ስምምነቶችን አፀደቀ

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አንደኛ ልዩ ስብሰባ መንግስት ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ጋር ያደረጋቸውን ሁለት የብድር ስምምነቶችን አፅድቋል።

የብድር ስምምነቶቹ የፋይናንስ ዘርፉን ለማጠናከርና የመንግስት አገልግሎትን ለማሻሻል የሚውሉ ናቸው ተብሏል።

የብድር ስምምነቶቹን አስመልክቶ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ጋር ያደረገችው የ700 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነትና ተወዳዳሪነት የበለጠ ለማሻሻል ያስችላል ብለዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካፒታል አቅምን እንደሚያሳድግ ገልፀው፤ ብድሩ የኢትዮጵያ ልማት ባንክን አሰራር ለማዘመን ያስችላልም ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት የዕዳ ጫናዋ እየቀነሰ መምጣቱንም ነው የተናገሩት።

ኢትዮጵያና ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ለዘመናዊ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል የ70 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነትም ለምክር ቤተ ቀርቧል።

ምክር ቤቱ በብድር ስምምነቶቹ ላይ ከተወያየ በኃላ ስምምነቶቹን በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።

#ኢዜአ

ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር  በሚቀጥለው ሳምንት ይጀመራልወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)ስምንተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር በሚቀጥለው ሳምንት ...
27/01/2025

ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር በሚቀጥለው ሳምንት ይጀመራል

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)

ስምንተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር በሚቀጥለው ሳምንት በወላይታ ሶዶ ከተማ እንደሚካሄድ የባህልና ስፓርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር "የታዳጊ ስፖርተኞች ልማት ለአሸናፊ አገር" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ እንደሚካሄድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሀመድ እንደገለፁት፤መንግስት ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ትኩረት ሰጥቷል።

በተለይም ከለውጡ በኋላ እየተሰሩ ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ለስፖርቱ ዘርፍ ትልቅ ትኩረት መሰጠቱን የሚያመላክት ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡

በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚካሄደው ውድድር ላይ እግር ኳስ፤አትሌቲክስ፤ ፤ውሃ ዋና፤ማርሻል አርትን ጨምሮ በ11 የስፖርት አይነቶች ምዘናው ይካሄዳል።

2 ሺ 656 ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የታዳጊ ወጣቶች ውድድርም ከጥር 27 እስከ የካቲት 5 ቀን 2017 እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

ውድድሩ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ስልጠና ፕሮግራምን ጥራት እና ውጤታማነት በመመዘን ክፍተቶችን መለየት አላማ አድርጎ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል፡፡

በውድድሩ የሚለዩ ተተኪ ስፖርተኞች ወደ ክለቦችና የስፖርት አካዳሚዎች የሚገቡበትን ዕድል ለመፍጠር እንደሚያስችልም አብራርተዋል።

በሚኒስቴሩ የስፖርት ልማት ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ ተስፋዬ በቀለ በበኩላቸው፤ተቋርጦ የቆየው የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር በተለይም ስፖርቱን ለማነቃቃት የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡

በተለይም ውድድሩ በወላይታ ሶዶ መካሄዱ ያሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ለማነቃቃት በር እንደሚከፍት ነው የጠቀሱት፡፡

ከዚህ ባለፈ ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ታዳጊዎች የሚሳተፉበት በመሆኑ እርስ በርስ ይበልጥ የሚተዋወቁበትን መድረክ ይፈጥራል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ እዳ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት አንጻር ወደ 13.7 በመቶ ዝቅ ማለቱ ተገለፀ**********************ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)የኢትዮጵያ የውጭ እዳ መጠን ...
27/01/2025

የኢትዮጵያ እዳ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት አንጻር ወደ 13.7 በመቶ ዝቅ ማለቱ ተገለፀ
**********************
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2017(ወቴቪ)
የኢትዮጵያ የውጭ እዳ መጠን ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት አንፃር ወደ 13.7 በመቶ ዝቅ ማለቱን ሲጂቲኤን በዘገባው አመልክቷል፡፡

ባለፉት አምስት አመታት በተሰሩ ትልልቅ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ኢትዮጵያ የነበረባትን እዳ ዝቅ ማድረግ ችላለች::

ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት አመታት የ10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈል መቻሏ ለእዳ ጫናው መቀነስ አንዱ ምክንያት ነው ተብሏል::

ከዚህ በተጨማሪም የገቢ ማስገኛ አቅምን ማሻሻል መቻሉ ኢትዮጵያ የዕዳ መጠኗ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት የነበረው ድርሻ በ13.7 በመቶ ዝቅ እንዲል ማድረጉን ሲጂቲኤንን ዋቢ በማድረግ ኢ ቢ ሲ ዘግቧል::
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

በርካታ ፍልስጤማውያን ወደ ቀያቸው መመለስ ጀመሩወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19፣ 2017 (ወቴቪ) እስራኤል እና ሃማስ የደረሱትን ስምምነት ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ወደ ሰሜን ጋዛ ማ...
27/01/2025

በርካታ ፍልስጤማውያን ወደ ቀያቸው መመለስ ጀመሩ

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19፣ 2017 (ወቴቪ) እስራኤል እና ሃማስ የደረሱትን ስምምነት ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ወደ ሰሜን ጋዛ ማቅናት ጀምረዋል፡፡

እስራኤል እና ሃማስ የደረሱት ታጋቾችን የመለዋወጥ ስምምነት ተከትሎ ነው ፍልስጤማውያኑ ተፈናቃዮች እስራኤል ተቆጣጥራው በነበረው ኔትዛሪም ኮሪደር በኩል ወደ ሰሜን ጋዛ እየሄዱ ያሉት፡፡

ፍልስጤማውያኑ በእግር እና በተሽከርካሪ ወደ ሰሜን ጋዛ እንዲገቡ መፍቀዷን የገለጸችው እስራኤል እስከ አሁን ድረስ ግማሽ ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎች ወደ ከተማቸው እየገቡ መሆናቸውን አስታውቃለች፡፡

ወደ ከተማቸው መመለሳቸው ደስታን ቢፈጥርላቸውም በነበረው የከፋ ጦርነት ምክንያት ቤትና ንብረታቸውን የማግኘት ዕድል እንደማይኖራቸው ፍልስጤማውያኑ ገልጸዋል፡፡

ቢቢሲ ያነጋገረው የ42 ዓመት ዕድሜ ያለው ፍልስጤማዊ ኒርመን ሙሳቤህ “ወዳደኩበት ቀየ መመለስ እፈልጋለሁ፤ ምንም እንኳን ቤቴ ቢኖርም ባይኖርም” ብሏል፡፡

ተፈናቃዮቹ ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ወደ ጋዛ እንዲመለሱ ከስምምነት ተደርሶ የነበር ቢሆንም÷ ሃማስ የ28 ዓመቷን እስራኤላዊ ታጋች ባለመልቀቁ ምክንያት መዘግየታቸው ተነግሯል፡፡

ይሁን እንጂ ታጋቿ የፊታችን ሐሙስ ለቀይ መስቀል ማኅበር ተላልፋ እንድትሰጥ መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎ ፍልስጤማውያኑ ከሁለት ቀናት ቆይታ በኋላ ወደ ጋዛ መግባት መጀመራቸውን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

በወላይታ ዞን በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ፈተና ለተማሪዎች መስጠት ተጀመረወላይታ ሶዶ፤ጥር 19/2017(ወቴቪ)በዞኑ የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ፈተና ከ57...
27/01/2025

በወላይታ ዞን በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ፈተና ለተማሪዎች መስጠት ተጀመረ

ወላይታ ሶዶ፤ጥር 19/2017(ወቴቪ)
በዞኑ የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ፈተና ከ571 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተና እየወሰዱ መሆናቸውንም የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለጸ።

በወላይታ ዞን በሁሉም ትምህርት ቤቶች የ2017 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ፈተና ለተማሪዎች መስጠት መጀመሩን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።

የወላይታ ዞን የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚካኤል ሳዖል በዞኑ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ያወጣውን አመታዊ የትምህርት ካለንደር መሠረት ተማሪዎችን ማስፈተን መጀመሩን አስታውቀዋል።

እንደዞን የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ፈተና ከ571 ሺህ በላይ ተማሪዎች እየወሰዱ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

የ6ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሀገር አቀፋዊና ክልላዊ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ ዞናዊ ፈተና ተዘጋጅቶላቸዉ በመፈተን ላይ ይገኛሉ ያሉት ኃላፊው ፈተናው ከኩረጃ በጸዳ መልኩ እንዲሆን የትምህርት ባለሙያዎች በሁሉም ወረዳ/ከተማ ተመድበው ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

የወላይታ ዞን አስተዳደር ከ250 ሺህ ብር በላይ በጀት በመመደብና የፈተና ዝግጅቱ ከተጀመረበት ቀን አንስቶ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረጉንም ተናግረዋል።

መምሪያው የትምህርት ፖሊሲ መሠረት በመንግሥትና በግል ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን በዕዉቀት፣ በክህሎት በአመለካከትና ልማትን ዉጤታማ ለማድረግ እና የትምህርትን ዉጤታማትን ለማረጋገጥና ዘርፈ ሥራዎችን ሲያከናዉን ቆይቷልም ብለዋል።

በዞኑ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከትምህርት ስብራትን ወደ ብሥራት ዉጤታማ ጉዞ ለማድረግ ዘርፈብዙ ተግባራት እና ልዩ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዘንድሮ በበጀት ዓመቱ በተለየ መልኩ በተማሪዎች ዘንድ የዉድድር መንፈስን ለመፍጠር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

በወረዳና ከተማ ደረጃ ሞዴል ተማሪዎችን በየትምህርት እርከኑ በልዩ መርሃ ግብር በማስተማር በማስጠናትና የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት እየተሠሩ ያሉ ተግባራት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል።

የሁሉም ተማሪዎች ዉጤት ተከታታይ ምዘናን፣ ወረዳዊ ከተማ አቀፍና ዞናዊ ፈተናን ያካተተ ማጠቃለያ ዉጤት ትንተና ከ100% ለሁሉም ክፍሎች የሚዘጋጅ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

ፈተናው በሠላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የትምህርቱ አመራር፣ ርዕሰ መምህራን፣ መምህር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚጠብቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡም ጠይቀዋል።

አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1ኛ ልዩ ስብሰባውን እያካሄደ ነውወላይታ ሶዶ፤ ጥር 29/2017(ወቴቪ)6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ እየተካሄደ ይገ...
27/01/2025

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1ኛ ልዩ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 29/2017(ወቴቪ)

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ እየተካሄደ ይገኛል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የግብርና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያዳምጥ ሲሆን፤ ሁለት የብድር ስምምነቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ እንዲሁም የከተማ መሬትን በሊዝ ስለመያዝ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

ወደጋዛ የሚወስደው መንገድ በእስራኤል በመዘጋቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውን ወደቤታቸው መመለስ አልቻሉምወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017(ወቴቪ)በሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያን በጋዛ...
27/01/2025

ወደጋዛ የሚወስደው መንገድ በእስራኤል በመዘጋቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውን ወደቤታቸው መመለስ አልቻሉም

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017(ወቴቪ)
በሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያን በጋዛ ሰርጥ ወደሚገኝ ቤታቸው እንዳይመለሱ እስራኤል ዋና መንገዱን መዝጋቷ ተገለጸ።

እስራኤል ዋና መንገዱን የዘጋችው ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን አፍርሷል በሚል ነው።

በእስራኤልና ሐማስ መካከል ውዝግብ የተነሳው ሐማስ አራት እስራኤላዊ ሴት ወታደሮችን ከለቀቀ በኋላ እስራኤል 200 ፍልስጤማው እስረኞችን መልቀቋን ተከትሎ ነው።

እስራኤላዊቷ አርቤል ያሁድ እስከምትለቀቅ ድረስ የጋዛ ነዋሪዎች ወደ ሰሜናዊው ክፍል መጓዝ እንደማይፈቀድላቸው እስራኤል ገልጻለች።

ሐማስ አርቤል በሕይወት እንዳለችና በቀጣይ ሳምንት እንደምትለቀቅ ገልጿል።

ሐማስ ከወታደሮች በፊት ዜጎችን ለመመለስ ተስማምቷል።

ተፈናቃዮች ወደ ጋዛ ሊመለሱበት በነበረው አል-ራሺድ መንገድ ላይ የተኩስ ድምጽ ተሰምቷል።

ሮይተርስ እንደዘገበው አንድ ሰው ተገድሏል። ቢቢሲ ያላረጋገጠው ቪድዮ ላይም ተኩስ ይሰማል።

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር በማዕከላዊ ጋዛ "የተሰባሰቡና ስጋት ናቸው ተብለው የተወሰዱ ሰዎች" ስለታዩ ተኩስ እንደነበር ገልጿል።

ወታደሮች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በሚል መተኮሱን አክሏል።

ወደ ጋዛ ለመመለስ እየጠበቁ ካሉት አንዱ የሆነው ሙሐመድ ኢማድ አል-ዲን "ቤቴ ፈርሶ ሊሆን እንደሚችል አውቃለሁ። ፀጉር አስተካካይ ነበርኩ። ወደ ሥራዬ መመለስ አለብኝ። ልጆቼን ማብላት ስላልቻልኩ ብዙ ገንዘብ ተበድሬያለሁ" ብሏል።

የእስራኤልና ሐማስ የ15 ወራት ጦርነት ተቋጭቶ ወደቀያቸው መመለስ እንደሚሹም ተናግሯል።

ትሪም የሚባለው መተላለፊያ ሰባት ኪሎሜትር ይሸፋናል። በእስራኤል ቁጥጥር ሥር ሲሆን ወደ ሰሜናዊ ጋዛ የሚወስድ ዋነኛ መንገድ ነው።

በአካባቢው የምትገኘው ሉብና ናስር ከሁለት ልጆቿ ጋር ወደ ቤታቸው ለመሄድ እየተጠባበቁ ነው።

ለ11 ወራት ካላገኘችው ከባለቤቷ ሱልጣን ጋር ለመገናኘት ወደቤታቸው የሚወስዳት አህያ ተከራይታ ብትጠብቅም ማለፍ አልቻለችም።

"ልጆቼ ለወራት አባታቸውን ለማየት ጓጉተው ነበር። እዚሁ መተላለፊያ አካባቢ እጠብቃለሁ። ወደ ጋዛ ለመመለስ የመጀመሪያዋ መሆን እፈልጋለሁ" ትላለች።

የካታርና ግብፅ አደራዳሪዎች በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ቤታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ጥረታቸውን ቀጥለዋል።

ሆኖም እስራኤል መተላለፊያ መንገዱን ዘግታዋለች።

ሐማስ የታገተችውን ሴት በሕይወት መኖር እንዲያረጋግጥ እስራኤል ጠይቃለች። ማረጋገጫው ለአደራዳሪዋ ግብፅ እንዲሰጥም አሳስባለች።
# BBC AMHARIC
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 1ኛ ልዩ ስብሰባውን ያካሂዳልወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017(ወቴቪ)፦ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ነገ ይካሂዳ...
27/01/2025

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 1ኛ ልዩ ስብሰባውን ያካሂዳል

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017(ወቴቪ)፦ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ነገ ይካሂዳል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የግብርና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያዳምጥ ሲሆን፤ ሁለት የብድር ስምምነቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ እንዲሁም የከተማ መሬትን በሊዝ ስለመያዝ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ የተገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ ኢዜአ ዘግቧል።
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ፎረም ተመሰረተ ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017 (ወቴቪ) ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀገር...
26/01/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ፎረም ተመሰረተ

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017 (ወቴቪ) ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ፎረም በሆሳዕና ከተማ ተመሰረተ።

የፎረሙ መመስረት ዐቢይ ዓላማ የክልሉን ሕዝቦች የእርስ በርስ መስተጋብር ከማጠናከሩም በላይ፤ ከመንግስት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችል መሆኑን የፎረሙ ሰብሳቢ ዳኛ ሞላ ጫኬቦ ተናግረዋል፡፡

የክልሉን ሕዝቦች አንድነት ለማስጠበቅ፣ ባህሎችና እሴቶች ለማጎልበትና የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፎረሙ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

የፎረሙ አባላት በክልሉ የሚነሱ ጉዳዮችን በውይይትና በምክክር ለማስፈጸም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ማረጋገጣቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

ሁሉንም የክልሉን ሕዝቦች በእኩልነት እና በታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

"ሀይሶት ህርባ" የጋርዱላ ዞን ህዝቦች ያለፈውን አዝመራ ሰብስበው ፈጣሪያቸውን የሚያመሰግኑበት፣ለቀጣይ የዘር ወቅት የሚዘጋጁበት የደስታና የምስጋና በዓል ነው  :- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ...
26/01/2025

"ሀይሶት ህርባ" የጋርዱላ ዞን ህዝቦች ያለፈውን አዝመራ ሰብስበው ፈጣሪያቸውን የሚያመሰግኑበት፣ለቀጣይ የዘር ወቅት የሚዘጋጁበት የደስታና የምስጋና በዓል ነው :- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 18/2017(ወቴቪ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በጋርዱላ ዞን ህዝቦች የዘመን መለወጫ በዓል ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት "ሀይሶት ህርባ" የጋርዱላ ዞን ህዝቦች ያለፈውን አዝመራ ሰብስቦ ፈጣሪያቸውን የሚያመሰግኑበት፣ ለቀጣይ የዘር ወቅት የሚዘጋጁበት የደስታና የምስጋና በዓል ነው ብለዋል።

ባለሰባት ኖታ ፊላ የትንፋሽ መሳሪያን ሰርታችሁ ለአለም እንዳስተዋወቃችሁ በፍቅርና በሰላም ተደምራችሁ ለሀገር ብልፅግና የበኩላችሁን ልታበረክቱ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

ባለፉት ጊዜያት በዞኑ የነበረውን የሰላም እጦት አስወግዳችሁ በዓሉን በድምቀት በአደባባይ በማክበራችሁ ምስጋና ይገባችኋል ሲሉም ተናግረዋል።

"ሀይሶት ህርባ" በርካታ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን የተጣላ የሚታረቅበት፤ቂምና ቁርሾ የሚወገድበት፣ በድንቅ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የሚታወቅ፣ እህልን በጉድጓድ ለሩብ ምዕተ አመታት በማኖር ቁጠባን የሚያስተምር ድንቅ እሴት መሆኑንም አብራርተዋል።

የጀመራችሁትን የሰላም ግንባታ በማፅናት፣ ልማት ባሻገር በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራና በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መረባረብ እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን መልዕክት ማስተላለፋቸውን የዘገበው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ።
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ
https://www.facebook.com/Wolaita-Television-Office-ወላይታ-ቴሌቪዥን-ጽቤት-100509191530481/
የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UC1BT_6xDzGufgELD-TUznmw
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/wolaitatelevision
ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቲውተር አካውንታችንን ይከተሉ
https://twitter.com/WolaitaTV?s=09
ከኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Television Office /ወላይታ ቴሌቪዥን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wolaita Television Office /ወላይታ ቴሌቪዥን ጽ/ቤት:

Videos

Share