
17/04/2024
ሰላማችን የህልውናችን ቁልፍ፤ የብልፅግናችን መሰረት !!
የሀገርን ሉዓላዊነትና የህዝባችንን አንድነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ወደ ኋላ የማንል ኢትዮጵያውያን ሙሉ አቅማችንን አቀናጅተን ድህነት ላይ ለመዝመት ለዘላቂ ሰላማችን የማንከፍለው ዋጋ አይኖርም።
ከጦርነት አዙሪት በመውጣት ሰላማዊት ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማውረስ ያለፈው ትውልድ የባከነ ቁጭት የዚህ ትውልድ ደግሞ ምርጫውና ተስፋው ነው።
ሰላማችን የህልውናችን ቁልፍ የብልፅግናችን መሰረት በመሆኑ ከግጭት ጠማቂዎች ድግስ ባለመታደምና ሁሉም የሰላም ዘብነቱን በማጠናከር ስለ ሰላም መዘመር እንዲሁም ከፀጥታ ሀይላችን ጎን በመሰለፍ አስፈላጊውን ዋጋ መክፈልን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
ለሰላም የሚደረግ እንቅስቃሴ ሁሉ የህይወት መስዋዕትነትን፣ የንብረት ውድመትን፣ መጎሳቆልን፣ መሰደድን፣ ተስፋ መቁረጥን የመሳሰሉ የጦርነትና ተያያዥ ችግሮችን ስለሚያስቀር ስለሰላም የቱንም ያህል ብንፈጥን የቱንም ያህል መስዋዕትነት ብንከፍል ያንስ ይሆናል እንጂ ስለማይበዛ ሁሉም የፓርቲያችን አባላት፣ ደጋፊዎች እና መላው ህዝባችን ሰላምን በኑሯችን ሁሉ ልንተረጉመው ይገባል።