Sodo comprehensive school

Sodo comprehensive school Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sodo comprehensive school, Digital creator, Sodo.

04/11/2023

"በትምህርት ሴክተሩ የገጠመንን ስብራት አንዱ ለሌላው ከመወራወር ይልቅ እያንዳንዳችን የሚጠበቅብንን በማበርከት ለችግሩ መፍትሔ መሆን ይገባናል" ሲሉ የወላይታ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ወይንሸት ሞላ ገለጹ

ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 24/2016 የወላይታ ዞን ምክር ቤት በ2015 የትምህርት ዘመን የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል የተማሪዎች ውጤት እና የትምህርት ጥራት ቀጣይ መፍትሔ አቅጣጫዎች ዙሪያ የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ አካሄደ።

የወላይታ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ወይንሸት ሞላ የትምህርት ተቋማት ትውልድ የሚገነባባቸው ተቋማት ናቸው በማለት ከገጠመን የትምህርት ውድቀት አንጻር ነገ አገርን የሚረከብ ዜጋን የማፍራት ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን በመገንዘብ የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ ተዘጋጅቷል ብለዋል።

በትምህርት ሴክተሩ የገጠመንን ስብራት አንዱ ለሌላው ከመወራወር ይልቅ እያንዳንዳችን የሚጠበቅብንን ማበርከት መፍትሔ ልናመጣ ይገባናል ሲሉ ለተሳታፊዎች ገልጸዋል ወ/ሮ ወይንሸት።

በ8ኛና 12ኛ ክፍል የተማሪ ውጤት ለማስተካከል እያንዳንዱ ባለድርሻ የሚጠበቅበትን በመውሰድ ለመፈጸም መግባባት የሚፈጠርበት መድረክ እንደሆነም በመግለጽ ሁላችንም ከተኛንበት መንቃት ያስፈልጋል ሲሉም አብራርተዋል።

የወላይታ ዞን ብልጽግና ረዳት የመንግስት ተጠሪና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ተመስገን አለማየሁ በበኩላቸው የትምህርት ውድቀትን ለማስተካከል ሁሉም ከራስ ጀምሮ እርምጃ እየወሰደ መምራት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።

የትምህርት ሥራ የተመራበት አግባብ ለውድቀታችን መነሻ ነው ሲሉም ገልጸው ተቆራርጦ የመምራትና ከሴክተሩም ከባለድርሻ አካላትም ቁርጠኝነት ይጠበቃል ብለዋል።

የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ኩማ የትምህርት ውድቀት መነሻው ዓመታትን ያስቆጠረ እና በትምህርት ጥራት ላይ ሥራዎች ባለመሠራታቸው የመጣ ውድቀት ነው ሲሉ ገልጸው ሁሉም የትምህርት አመራር፣ መምህራን፣ ተማሪ እንዲሁም የተማሪ ወላጆች እጅ ለእጅ በመያያዝ ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

የዘርፉንም ችግር ለመፍታት የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ መደረጉን እንዲሁም በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተዘጋጁ መጻሕፍት የማዳረስና የትምህርት መሠረተ ልማቶችን ባለድርሻ አካላት በማስተባበር የማሟላት ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውን በማስረዳት ከረጅም ጊዜ መፍትሔ አኳያ ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ ሠፊ ሥራ ይጠይቃል ብለዋል።

የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በክረምቱ ወቅት ከ150 ሚሊዮን በላይ ግምት ያላቸው የህዝብ ተሳትፎ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል።

የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ፀጋዬ ቀልታ የትምህርት ስብራት እጅግ የከፋ መሆኑ የትምህርት ሥርዓታችን ችግር ያለበት መሆኑን ያመላከተ ነው በማለት ሁላችንም የጋራ ችግርና ውድቀት አድርገን በመውሰድ በፍጥነት ሠርተን መውጣት ይኖርብናል ሲሉ አስረድተዋል።

በሌላ በኩል ሌሎች የትምህርት አመራ፣ የተማሪ ወላጅ፣ እንዲሁም ተማሪ በውድቀቱ ድርሻ ያለው በመሆኑ በጋራ ውይይት ከችግሩ ለመውጣት እየተሠራ እንደሆነም የገለጹት አቶ ፀጋዬ የግብዓት ማሟላት ሥራም ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመሥራት ለመፍታት እየተሠራ ነው ብለዋል።

የሙያ ማህበሩ ከትምህርት አመራሩ ጋር ተባብሮ ይሠራል ያሉት የወላይታ ዞን መምህራን ማህበር ሰብሳቢ ወ/ሮ ባዩሽ ዘውዴ የትምህርት ጥራት ማስጠበቅና የመምህራን መብት ማስከበር የሙያ ማህበሩ ዋናው ተግባሩ እንደሆነ በማብራራት ችግሩ የጋራ ቢሆንም የመምህራን ድርሻ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ሁሉም መምህራን ችግር ፈጣሪዎች ናቸው ባይባልም ችግር ፈጣሪዎች ላይ ተለይቶ እስከማገድ እርምጃ እየተወሰደ እየተመራ እንደሆነ ያብራሩት ሰብሳቢዋ በመሠረታዊ ችግሮቻችን ላይ ተግባራዊ ጥናት እየሠሩ ግብረ መልስ እየሰጡ እንደሚሠሩ ጠቁመዋል።

ሐጂ ናስር የሱፍ እና አቶ ሚልክያስ ኦሎሎ ከባለድርሻ አካላት የተገኙ ተሳታፊዎች ሲሆኑ እንደሀገርም እንደወላይታም ወድቀናል ሲሉ ገልጸው የኃይማኖት ተቋማት፣ የተማሪዎች ወላጆችም ሆነ መምህራንና ተማሪዎች ድርሻቸውን መውሰድ አለባቸው ብለዋል።

መንግስት መምህራንን የማብቃት ሥራ መሥራት አለበት ያሉት የኃይማኖት አባቶች ትምህርት ቤት የማይሄዱ መምህራን መታረም እንዳለባቸው እና የተማሪ ሥነ ምግባር የማስተካከል ሥራ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል።

እንደዞን ከተፈተኑ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች 1.66% ብቻ ማለፋቸው ፤ የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 36ቱ(45%) አንድም ተማሪ 50% እና በላይ ያላስመዘገቡ መሆናቸው እንዲሁም እንደወረዳ ካስፈተኑት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ምንም ተማሪ ያላሳለፉ አባላ አባያ፣ ሆብቻ እና ሁምቦ ወረዳዎች መሆናቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ መረጃ አመላክቷል።

የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አፈ ጉባኤ ጽ/ቤት ማኔጅመንት፣ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ማኔጅመንት፣የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ የወረዳና ከተማ አፈ ጉባኤዎች የኃይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች የመምህራን ሙያ ማህበራት ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረኩ ተሳታፊዎች ናቸው።

 #የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆኗልበ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒ...
03/11/2023

#የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆኗል

በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለምትከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገልጻለን።

Website: https://result.ethernet.edu.et/
Telegram bot:

Instantly access your exam results on our user-friendly website.

01/11/2023

አዲስ የተማሪዎች ዝውውር መመሪያ ረቂቅ 2016ዓም

ዋና ዋና ነጥቦች

ከዚህ በፊት በተለያዩ ክልሎች ወጥነት ያልነበረው የተከታታይ ምዘና አያያዝ ማለትም 60% ተከታታይ ምዘና 40% ማጠቃለያ ፈተና አሁን ወደ 40% ተከታታይ ምዘና 60% ማጠቃለያ ፈተና ተሰጥቶ ከ100% ይያዛል

ከ9-11ኛ ክፍል Maths and English ከ50% በታች ያመጣ ተማሪ እንዲሁም 1-7ኛ ክፍል 6ኛን ሳይጨምር Maths እና የማስተማሪያ ቋንቋውን ከ50% በታች ካመጣ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር አይችልም

አንድ ክፍል ደረጃ ከአንዴ በላይ ከደገመ ከትምህርት ይሰናበታል
ሙሉ መረጃውን s**o comprehensive high school telegram channel ላይ ያንብቡ

Send a message to learn more

26/10/2023
09/10/2023

ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ፡- የትምህርት ሚኒስቴር
**************

በ2015 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ በድረ-ገፅ ወይም በአጭር የፅሁፍ መልእክት አማካኝነት መመልከት እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡

የ2015 የትምህርት ዘመን የ12ተኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ውጤትን በተመለከተ ሚኒስትሩ ለመገነኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።

ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፤ የ2015 የትምህርት ዘመን የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ 188 ተማሪዎች ውስጥ 27 ሺህ ተማሪዎች ከ50 በመቶ በላይ በማምጣት የማለፍያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልፀዋል።

ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 3.2 ከመቶ ተማሪዎች ብቻ ማለፋቸውን የገለፁት ሚኒሰትሩ፤ ያለፉት ተማሪዎች ቁጥር ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር በ0.01 መቀነሱን ተናግረዋል።

ዘንድሮ 3 ሺህ 106 ትምህርት ቤቶች ፈተና ያስፈተኑ ሲሆን፣ ከነዚህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 328 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በዚህም 42.8 ከመቶ ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸው ነው የተገለፀው።

የዘንድሮው ፈተና ከተፈጥሮ 649 ከ700 ሆኖ ተመዝግቧል። ውጤቱን ያስመዘገበችው ተማሪ ሴት መሆኗም ተነስቷል።

በማህበራዊ ሳይንስ 533 ከ600 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡም ተገልጿል።

ፈተናውን የተፈተኑ ተማሪዎች ከነገ ጠዋት 12 ሰአት ጀምሮ ውጤት ማየት እንደሚችሉም ተገልጿል።

Etv እንደዘገበው

09/10/2023



በአጠቃላይ በ2015 ዓ.ም ከተፈተኑ ተማሪዎች 3.2 በመቶ ብቻ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተዋል፡፡

በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለፈተና ከተቀመጡ በድምሩ 845,677 ተማሪዎች 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 31, 224 ተማሪዎች ብቻ ናቸው፡፡

በዚህም 160 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን በሬሜዲያል ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚቀበሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ትህርት ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አለመቻላቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

08/10/2023

የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል

ወላይታ ሶዶ፣ መስከረም 27፣ 2016 የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ተማሪዎች ትክክለኛውን መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ገጽ ላይ እንዲከታተሉም አሳውቋል፡፡

በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል፡፡

ምንጭ፦(ኤፍ ቢ ሲ)

24/09/2023
2016 calander
18/09/2023

2016 calander

28/08/2023

ሀገር አቀፍ ደረጃ በማይ ሶሮባን ኢትዮጵያ አማካይነት ሰካሄድ የሰነበተው የአገር አቀፍ የሒሳብ እና ቴክኖሎጂ ዉድድር በወላይታ ሶዶ ተማሪዎች አሸናፍነት ተጠናቀቀ።

ባለፉት ቀናት ሲካሄድ በቆየው ውድድር ላይ 10 ከተሞች ማለትም አድስ አበባ፣ አዳማ፣ ብሾፍቱ፣ ጎንደር፣ ባህር ዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ ሀረር፣ ድረዳዋ እና ሀዋሳ የተሳተፉ ስሆን አጠቃላይ ለዉድድር ከተዘጋጀዉ 10 ዋንጫ ዉስጥ 4ቱን በማሸነፍ በአገር አቀፍ ደረጃ 1ኛ በመዉጣት ከወላይታ ሶዶ ከተማ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ተማሪዎች ተሸላሚ ሆኗል።

25/08/2023

በ2016 ዓ.ም አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይተገበራል::

የሁለተኛ ደረጃ የተማሪ መጻህፍትና የመምህራን መምሪያዎችን ለመምህራንና ባለድርሻዎች ለማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠም ይገኛል::
---------------------//---------------------------
ነሐሴ 19/2015 (የትምህርት ሚኒስቴር) በ2016 ዓ.ም አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሁሉም የመንግስትና የግል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚተገበር የትሞህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪ መጻህፍትና የመምህራን መምሪያዎችን ለመምህራንና ባለድርሻዎች ለማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠም ይገኛል።
የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) ስርዓተ ትምህርቱ የሚተገበረው ከዓለም አቀፍና ከውጭ የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች በስተቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በሚያስተምሩ ሁሉም የመግስትና የግል ትምህርት ቤቶች መሆኑን ገልፀዋል።
ስርዓተ ትምህርቱም በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ፣ በትግራይ ክልል ደግሞ በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል እንደሚተገበርም ተናግረዋል።
ሰራ አስፈፃሚው ስርዓተ ትምህርቱ ከሥራና የተግባር የትምህርት አይነቶች በስተቀር በሁሉም የቀለም ትምህርት ዓይነቶች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ እንደሚተገበርም ገልፀው የሥራና የተግባር ትምህርቶችም ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚተገበሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
ስርዓተ ትምህርት እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድ የጠቆሙት ዶ/ር ቴዎድሮስ ለስርዓተ ትምህርቱ ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ2015 ዓ. ም ጀምሮ መተግበር መጀመሩ ይታወቃል።

16/08/2023

ማስታወቂያ
እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ!!
የ2016 የትምህርት ዘመን ከቅድመ-አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያለው የተማሪ ቅበላ/ምዝገባ/ የሚፈፀመው ከነሐሴ 15/ 2015- ጳጉሜ 5/2015 ድረስ ብቻ ይሆናል። ስለሆነ ተማሪም ሆነ የተማሪ ወላጅ ከወዲሁ በቂ ዝግጅት በማድረግ ለተግባራዊነቱ እንዲተጋ ጥሪያችንን እያቀረብን፣ ዘንድሮ ከተቀመጠው የምዝገባ ጊዜ ሠሌዳ ውጪ የሚፈፀም የቅበላ ሥራ በማንኛውም አይነት ምክንያት የማይስተናገድ መሆኑን ለማሳወቅ እንገደዳለን። (የ2016 ምዝገባ ቋትም አይቀበለውም)።
NB...የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀመረው በቀን 02/01/2016 ነው።
የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ!!

Address

Sodo

Telephone

+251946323967

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodo comprehensive school posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sodo comprehensive school:

Share