Wogeta FM 96.6

Wogeta FM 96.6 ZOOXANAWU ZIRXXATETTAANNE TUMATETTAA !

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና ! This is the official Facebook home of wogeta FM 96.6 Come and join us!

Diligence and loyalty for prosperity !!

ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u live FM 96.6 studio tel:- 046 180 99 99

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በህገወጥ መንገድ የተወረሩ ከ3 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን የወል መሬት ወደ መሬት ባንክ መግባቱ ተገለፀ ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የደቡ...
05/07/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በህገወጥ መንገድ የተወረሩ ከ3 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን የወል መሬት ወደ መሬት ባንክ መግባቱ ተገለፀ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ዓመታዊ ጉባኤ በዎላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንዳሉት መሬት ለኢኮኖሚ መሠረት ነዉ።

ያለመሬት ብልጽግና ማረጋገጥ እንደማይቻል የገለፁት ኃላፊው፤ ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመከላከል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለዜጎች በፍትሃዊነት ተደራሽ እንዲሆን አመራሩና ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ዶክተር መሪሁን አሳስበዋል።

የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ አቶ ኖህ ታደለ፤ ህገወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

በዚህም ባለፉት ጊዜያት በህገወጥ መንገድ የተወረሩ መሬቶችን የመከላከሉ ስራ ዉጤት ማስዝገቡን ጠቁመው፤ ከ3 ሺህ 3 መቶ ሄክታር በላይ የሚሆን የወል መሬት ወደ መሬት ባንክ ስለመግባቱ ጠቁመዋል።

በቀጣይም ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

"መሬት የሀብት ሁሉ ምንጭ ነዉ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚሁ መድረክ፤ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካለት እየተሳተፉ መሆኑን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

የኅብረተሰቡ ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና የላቀ ነው፦አቶ ዘውዱ ሳሙኤልዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የዎላይታ...
05/07/2025

የኅብረተሰቡ ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና የላቀ ነው፦አቶ ዘውዱ ሳሙኤል

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የዎላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የ2ኛ ዙር የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር ፎረም መድረክን በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በፎረሙ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዎላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዱ ሳሙኤል ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በምናደርገው ርብርብ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

በዞኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር መወያየትና መሰራት እጅግ ወሳኝ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በመንግስት አቅም መሸፈን የማይቻለውን ክፍተቶች እየለዩ ከፍተኛ አሰተዋጽኦ እያበረከቱ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ግብርናን ማዘመን ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው ለዚህም በግብርናው ዘርፍ አቅዶ የሚሰሩ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፋቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በጤናው፣ በትምህርት እና በሌሎች ዘርፎች ላይ ተሰማርተው በመሰራት ለወጣቶች ስራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በአስተሳሰብ ላይ አቅዶ እየሰሩ ያሉ ስራዎችን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዲሁም ሴትችንና ህጻናት የመደገፍና የማብቃት ተግባራት እያከናወኑ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍ እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ኃላፊው ይህንን በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ አሠራር ስርዓት መዘርጋትና ፍታሃዊ ተደራሽነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አመላክተዋል።

የዎላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት በለጠ በበኩላቸው መንግስት በብዙ ዘርፎች አቅዶ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሌት ቀን ርብርብ እያደረገ ባለው ረገድ የሲቪል ማህበረሰብ ሚና የላቀ ነው ብለዋል።

በዞኑ 50 ሲቪል ማህብረሰብ ድርጅቶች በ78 ፕሮጀክቶች ከ3.8 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ እየሰሩ መሆናቸው አስታውቀዋል።

እነዚህ ድርጅቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና በሌሎች አገልግሎት ዘርፎች አይተኬ ሚናውን እየተጫወቱ እንደሚገኙም ገልፀዋል።

ፎረሙ በመንግስትና በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እጅግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

የዎላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የ2ኛ ዙር የመንግስት እና የስቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛልዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) መድረኩ...
05/07/2025

የዎላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የ2ኛ ዙር የመንግስት እና የስቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) መድረኩም "ብልጽግናችን ለማረጋገጥ የስቭል ማህበረሰብ ድርጅቶች አጋርነት ወሳኝ ነው" በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው ።

የዎላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የ2ኛ ዙር የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር ፎረም መድረክን በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መምሪያው "ብልፅግናችንን ለማረጋገጥ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አጋርነት ወሳኝ ነው" በሚል መሪ ቃል የ2ኛ ዙር የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር ፎረም መድረክን በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ የዎላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዱ ሳሙኤልን ጨምሮ የዞን አጠቃላይ አመራር፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

በቴክሳስ በደረሰ የጎርፍ አደጋ 24 ሰዎች ሞቱ ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) በአሜሪካዋ የቴክሳስ ግዛት በደረሰ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ 24 ሰዎች ሲሞቱ፣ ...
05/07/2025

በቴክሳስ በደረሰ የጎርፍ አደጋ 24 ሰዎች ሞቱ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 28/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) በአሜሪካዋ የቴክሳስ ግዛት በደረሰ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ 24 ሰዎች ሲሞቱ፣ 25 የሚደርሱ ሕጻናት ጠፍተዋል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ክስተቱን "አስደንጋጭ እና አሰቃቂ" ያሉት ሲሆን፣ የፌደራል ባለሥልጣናት የሕይወት እርዳታ ለመስጠት ቃል መግባታቸውን የቴክሳስ አስተዳዳሪ ግሬግ አቦት ተናግረዋል።

የቴክሳስ ባለሥልጣናት የጠፉትን ሰዎች ቁጥር ማረጋገጥ ባይችሉም ፍለጋው እና የነፍስ አድን ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

"የጓንዳሉፔ ወንዝ በ45 ደቂቃ ውስጥ 26 ሜትር ከፍታ ጨምሮ በሕይወት እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል" ሲሉ ነው የቴክሳስ ምክትል አስተዳዳሪ ዳን ፓትሪክ የተናገሩት።

ፓትሪክ በነፍስ አድን ሥራው ምንም ዓይነት ተጨማሪ መሣሪያ እንደማያስፈልጋቸው በመጥቀስ፣ የግል ሄሌኮፕሮች እና ድሮኖች እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸዋል በማለት የዘገበው ቢቢሲ ነው።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

ውክልና የሚፀናው ውክልና ለማረጋገጥ እና  ለመመዝገብ ሥልጣኑ በተሰጠው የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ ወይም ይህ ስልጣን በሕግ  በተሰጣቸው አካላት ፊት ተረጋግጦ ሲሰጥ እና ሲመዘገብ...
04/07/2025

ውክልና የሚፀናው ውክልና ለማረጋገጥ እና ለመመዝገብ ሥልጣኑ በተሰጠው የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ ወይም ይህ ስልጣን በሕግ በተሰጣቸው አካላት ፊት ተረጋግጦ ሲሰጥ እና ሲመዘገብ መሆኑን የዎላይታ ዞን ፍትህ መመሪያ ከፍተኛ ዐ/ሕግ ዘውዱ ቡቃቶ ገለፁ።

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)

ውክልናውም ወካይ በፈለገ ጊዜ የመሻር ስልጣን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 2226( 1)የተደነገገ መሆኑን ተናግረዋል ።

የፍ/ብ/ሕ/ቁ 2199"ውክልና ወካይ ለተወካዩ እንደራሴው ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ሕጋዊ ሥራዎችን በወካዩ ስም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ነው ።

የውክልና አሰጣጥ በሕግ ምሪት የሚመራ ሲሆን አስቀድሞ የመወሰን ስልጣን የተሰጠው አካል በፌደራል ደረጃ በወሰናቸው አዋጆች መሠረት የወጡ ደንብና መመሪያ አሟልቶ ሲገኝ የሚሰጥ መሆኑን የዎላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ከፍተኛ ዐ/ሕግ አቶ ዘውድ ቡቃቶ ገልጸዋል ።

ውክልና በግልጽ ወይም በዝምታ እንደሚሰጥ ሕጉ ቢፈቅድም የጽሑፍ ውክልና በሚያስፈልግባቸው ጉዳዮች ውክልና ይሰጣል ያሉት አቶ ዘውዱ ለውክልና መሟላት ያለባቸው ነገሮች እንደውክልና ዓይነቶችም እንደሚለያዩ ተናግረዋል።

ውክልና የሰጠ ሰው በፈለገበት ጊዜ የመሻር ወይም የማንሳት ስልጣን እንዳለው አንስተው
ልዩ ውክልና የተሰጠው ሰው ውክልናው ላይ የተጠቀሱትን ተግባራት እና ከተግባራቱ ባህርይ ጋር የሚያያዙ አስፈላጊ ነገሮችን ማከናወን ይችላል ብለዋል።

ውክልናውን ወካይ በፈለገው ጊዜ የመሻር ስልጣን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 2226(1) የተሰጠ መሆኑን አቶ ዘወዱ ተናግረዋል።

ለማንኛውም ውክልና ሲሰጥ ወይም ወኪል ስንሆን የውክልናውን አሰጣጥ በሕጉ አግባብ መሆን እንዳለበት የዎላይታ ዞን ፊቲ መምሪያ ከፍተኛ ዐ/ሕግ አቶ ዘውዱ ቡቃቶ አሳስበዋል ።

በወይንሸት ኤካ

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ ማስተካከያ ተደረገበት።ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)   የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ ስርዓት ኮሚቴ የኢ...
04/07/2025

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ ማስተካከያ ተደረገበት።

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ ስርዓት ኮሚቴ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት በሲዳማ ቡና፣ መቻል እና ሀዋሳ ከተማ ክለቦች ላይ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ሶስቱ ክለቦች በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የክለቦች ክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያን በመተላለፍ እግድ ከተጣለባቸው ተጫዋቾች መካከል ቢያንስ አንዱን አሰልፈው ስለማጫወታቸው ጨዋታውን ከመሩት ዳኞች በቀረበው ሪፖርት ተረጋግጦ ውሳኔዎች መተላለፋቸውን ኮሚቴው ገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት ክለቦቹ ተጫዋቾቹን በመጠቀም ያደረጓቸውን ጨዋታዎችን በፎርፌ እንዲሸነፉ በዚህም ለተጋጣሚዎቹ በሙሉ 3 ነጥብና 3 ንጹህ ግቦች እንዲሁም ለሶስቱ ክለቦች ደግሞ በእያንዳንዱ ጨዋታ 0 ነጥብ እና 3 የግብ እዳ እንዲመዘገብ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

በተሰጡት የፎርፌ ውሳኔዎች መሰረት የ2017 የፕሪሚየር ሊግ ደረጃና ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃ መስተካከሉንም ነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ውድድር አመራርና ስነ ስርዓት ኮሚቴ ያስታወቀው፡፡

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

በክልሉ ከ2 ሚሊዮን በላይ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለአርሶአደሩ ተሰራጭቷል -የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ  ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 9...
04/07/2025

በክልሉ ከ2 ሚሊዮን በላይ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለአርሶአደሩ ተሰራጭቷል -የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ዓመታዊ ጉባኤ በወላይታ ሶዶ እያካሄደ ይገኛል ።

ጉባኤው የዘመነ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስርዓት ለማስፈን የሚያግዝ መሆኑ ተመላክቷል።

የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ አቶ ኖህ ታደለ በዚህ ወቅት እንደገለፁት በክልሉ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

በክልሉ የመሬት አጠቃቀም ስራን በተደራጀ መንገድ በማከናወን አርሶአደሩ የይዞታ መብት እንዲያረጋግጥ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል ።

በዚህም ባለፉት ጊዜያት ከ2 ሚሊዮን በላይ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለአርሶአደሩ ስለመሰጠቱ ገልፀው ፣በቀጣይ ከ1ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ለመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል።

መሬትን መንከባከብ ለማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ መኖሩን የገለፁት አቶ ኖህ፣ያለ መሬት ልማትን ማረጋገጥ እንደማይቻል አስረድተዋል ።

በክልሉ በ48 ወረዳዎች ፣የኢንፎርሜሽን ሲስተም የመሬት አስተዳደር ስርዓት ውስጥ መካተቱን ጠቁመዋል ።

በክልሉ የወል መሬት ወራራን በመከላከል በተሰሩት ስራዎች ዉጤት መመዝገቡን የገለፁት አቶ ኖህ፣ከዚህም ለወጣቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።

"መሬት የሀብት ሁሉ ምንጭ ነዉ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚሁ መድረክ ፣የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣እንዲሁም ባለድርሻ አካለት እየተሳተፉ መሆኑን ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል ።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

በ 2017 በጀት ዓመት ጭማሪ ያሳየው የትራፊክ አደጋዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)በ2017 በጀት አመት የተከሰተው የትራፊክ አደጋ ቁጥር ከ2016 አንጻር ጭማሪ ማሳ...
04/07/2025

በ 2017 በጀት ዓመት ጭማሪ ያሳየው የትራፊክ አደጋ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)
በ2017 በጀት አመት የተከሰተው የትራፊክ አደጋ ቁጥር ከ2016 አንጻር ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ ።

በ2016 ዓ.ም ዘጠኝ ወራት 2,248 ሞት ተመዝግቦ የነበር ሲሆን በ2017 ተመሳሳይ ወራት በ2016 ከተመዘገበው የሞት መጠን በ489 ከፍ በማለት 2,722 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል ።

የመንገድና ደህንነትና መድህን ፈንድ " ጥያቄ ይዘን እንውጣ " በሚል መሪ ሀሳብ አሳሳቢውን የትራፊክ አደጋ መቀነስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል ።

በኢትዮጵያ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን የሞት ፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመቀነስ የተለያዩ ስራዎች ቢሰሩም አሁንም አሳሳቢ መሆኑ ተነስቷል ።

በኢትዮጵያ ከሚደርሰው የትራፊክ አደጋ 82 በመቶ የሚሆነው በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ችግር ፣ በአሽከርካሪዎች እና በእግረኞች የጥንቃቄ ጉድለት መሆኑ ተገልጿል ።

በተደጋጋሚ አደጋ ከሚያደርሰው ተሽከርካሪዎች መካከል የንግድ ተሽከርካሪዎች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ የሲቪክ ድርጅቶች እና የመንግስት ድርጅት መኪኖች ተከታዩን ደረጃ ይይዛሉ።

በውይይቱ የሲቪል ማህበራዊት ግንዛቤ ከመፍጠር አንስቶ የትራፊክ አደጋን በመከላከልና በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተነስቷል።
እነዚህ ማህበራዊ ከመንግሥት በመቀጠል ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጥ እና በመቀነስ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ሲሉ የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አባሶ ተናግረዋል ።

የትራፊክ አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ መንገድ መሰረተ ልማት ምቹ ማድረግ፣ የትራፊክ ቁጥጥር ስርዓት ማዘመን እና የትራንስፖርት ስርአቱን ማሻሻያ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

አውሮፕላን ሸሽቶ በመኪና ህይወቱን የተነጠቀው ኮከብ ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)ቶተንሀም ሆትስፐርን ከሊቨርፑልን ያገናኘው የ2019 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ...
04/07/2025

አውሮፕላን ሸሽቶ በመኪና ህይወቱን የተነጠቀው ኮከብ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 27/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)
ቶተንሀም ሆትስፐርን ከሊቨርፑልን ያገናኘው የ2019 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በማድሪድ ዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስቴዲየም ሊደረግ ሰዓታቶች ብቻ ይቀራሉ፡፡ በዚህ ሰአት አንድ አስደንጋጭ ዜና ተሰማ፡፡ በማድሪድ ዋና ከተማ::

የሚደረገውን ጨዋታ ለመታደም ወደ ቦታው ሲያመራ የነበረው የቀድሞው የአርሰናል አማካይ ጆሴ አንቶኒዮ ሬስ በመኪና አደጋ ህይቱ አለፈ፡፡

ለሁለቱም የማድሪድ ከተማ ክለቦች አትሌቲኮ እና ማድሪድ ተጫውቶ ያሳለፈው አማካይ በሰአት 116 ኪሎ ሜትር ማሽከርከሩ ለአደጋውም ለህልፈቱም ምክንያት እንደነበር ፖሊስ ይፋ አደረገ፡፡

ከ6 አመት በኋላም በዚያው በስፔን የዲየጎ ዦታ ህይዎት በተመሳሳይ መኪና አደጋ ተነጠቀ፡፡

የሊቨርፑሉ አጥቁ በስፔን ዛሞራ ሴርናዲላ በምትባል ቦታ ከታናሽ ወንድሙ ጋር በሚጓዙበት ሰአት ነው አደጋው ያጋጠማቸው፡፡ ለመሆኑ የ28 አመቱ ፖርቹጋላዊ ስፔን እንዴት ተገኝ ?

የሊቨርፑል የቅድመ ውድድር ዝግጅት በመጭው ማክሰኞ የሚጀመር በመሆኑ ሁሉም ተጫዋቾች እንዲገኙ አርን ስሎት ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡

ዲየጎ ዦታም በተባለው ቀን እንግሊዝ ለመድረስ መነሻውን ከትውልድ ቦታው ፖርቶ አድርጎ ወደ
ስፔን በግል መኪናው መጓዝ ይጀምራል፡፡

ለመሆኑ ከፖርቹጋል ወደ እንግሊዝ ለመጓዝ ስለምን የየብስ ትራንስፖርትን መረጠ ካላችሁ መልሱ ይሄ ነው፡፡

ዦታ አጋጥሞት በነበረው ህመም መጠነኛ የሳንባ ቀዶ ህክምና አድርጓል፡፡ ይህንን ተከትሎ የህክምና ባለሙያዎች ተጫዋቾች ላልተወሰነ ጊዜ በአውሮፕላን እንዳይጓዝ መክረውታል፡፡

በመሆኑም ዦታ እስከ ሰሜን ስፔን በመኪና ከዚያም በጀልባ እንግሊዝ ለመድረስ ጉዞውን ቢጀመርም ካሰበበት ግን አልደረሰም፡፡

ከፖርቹጋል 190 ማይል ርቀት ላይ በምትገኘው የስፔን ግዛት ዛሞራ ውስጥ በአጋጠመው የመኪና አደጋ ላይመለስ አሸለበ፡፡

እግር ኳስ ተጫዋች ከሆነው ታናሽ ወንድሙ ጋር ህይወቱ ያለፈው ዲየጎ ዦታ ቀድሞም ቢሆን ከረጅም
ጊዜ የልጅነት ጓደኛው ጋር ጋብቻውን ለመፈጸም ወደ ሀገሩ ፖርቹጋል የተመለሰው በመኪና እና በጀልባ ጉዞ ነበር፡፡

የሶስት ልጆች አባት የሆነው ዲየጎ ዦታ ለ13 አመት አብራው ከነበረችው የፍቅር ጓደኛው ሩት ካርዶስ ጋር የሰርግ ስነ ስርአቱን ባደረገ በ11ኛው ቀን በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል፡፡

ሚያዚያ ወር ላይ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ያነሳው አጥቂ በግንቦት ደግሞ ከሀገሩ ጋር የኔሽንስ ሊግ ክብርን አሳከክቷል፡፡

በሰኔ ወር የተሞሸረው ሰው በሀምሌ ወር መሞቱ ተሰማ፡፡ ህመሙን ላለማባባስ ከአውሮፕላን ጉዞ የራቀው አዲሱ ሙሽራ የባሰው አጋጠመው፡፡

ለተከላካዮች ፈተና የሆነው ሁለ ገቡ አጥቂ አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ፖርቶ፣ ዎልቭስ እና ሊቨርፑል
ተጫውቶ ያሳለፈባቸው ክለቦች ሲሆኑ በተለይ በመርሲሳይዱ ክለብ በተሰለፈባቸው 182 ጨዋታዎች 65 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

የፕሪሚየርሊግ፣ የኤፍ ኤ ዋንጫ እና የሊግ ካፕ በቀዮቹ ቤት ያሳካቸው ክብሮች ናቸው፡፡

ገና በልጅነቱ ተሰጥኦውን ያዩ ፖርቹጋል ክርስቲያኖ ሮናልዶን የሚተካ ከኮብ አገኘች ብለው የመሰከሩለት፣ ከቁመቱ በላይ በሚያስቆጥራቸው የጭንቅላት ኳሶች አድናቆትን ያገኝው አጥቂ ለክቡም ለሀገሩም ብዙ በሚሰራበት ዕድሜው መኪና ህይወቱን ነጠቀው፡፡

ከሀገራት መሪዎች ጀምሮ እንደ ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ አይነት ከዋክብት ሀዘናቸውን ሲገልጹ የሊቨርፑል የከተማ ተቀናቃኝ የሆነው የኤቨርተን ደጋፊዎችም ጭምር ሰብአዊነትን በሚያስቀድመው እግር ኳስ አንድ መሆናቸውን ያሳዩበትም ሆነ፡፡

ሊቨርፑል ዲየጎ ዦታ ይለብሰው የነበረው 20 ቁጥር መለያ ከዚህ በኋላ እንዳይለበስ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

የዲየጎ ዦታ እናት እና አባትም በአንድ መጥፎ አጋጣሚ ሁለት ልጆቻቸውን ያጡበትን መጥፎ ቀን ለማሳለፍ ተገደዱ፡፡

የዲየጎ ዦታ እና የወንድሙ የቀብር ስነ ስርአት ነገ በተወለደባት ፖርቶ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

የ2018 የፌዴራል በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ፀደቀ ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ የቀረበውን የፌዴራል...
03/07/2025

የ2018 የፌዴራል በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ፀደቀ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ የቀረበውን የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት አፅድቋል።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 42ኛ መደበኛ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባም የ2018 የፌደራል መንግስት በጀትን 1.93 ትሪሊዮን ብር አድርጎ አፅድቋል።

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

ዲየጎ ዦታ በመኪና አደጋ ህይወቱ አለፈዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)የሊቨርፑል አጥቂ ዲየጎ ዦታ በመኪና አደጋ ህይወቱ ማፉን ጋዜጣ ዴሎ ስፖርት ዘግቧል፡፡ባጋጠመው የ...
03/07/2025

ዲየጎ ዦታ በመኪና አደጋ ህይወቱ አለፈ

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)

የሊቨርፑል አጥቂ ዲየጎ ዦታ በመኪና አደጋ ህይወቱ ማፉን ጋዜጣ ዴሎ ስፖርት ዘግቧል፡፡

ባጋጠመው የመኪና አደጋ ቤተሰቦቹ አብረው እንዳሉም እየተዘገበ ይገኛል፡፡

ፖርቹጋላዊው የቀድሞ የዎልቭስ አጥቂ በ28 አመቱ ነው ህይወቱ ያለፈወ፡፡

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦችዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6) ፦ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋልታ ነው በርካታ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍ...
03/07/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

ዎላይታ ሶዶ፣ሰኔ 26/2017 (ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6)

፦ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋልታ ነው በርካታ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍበት ሴክተር ነው፤ በአንድ ዘርፍ ላይ ጥገኛ የሆነ ኢኮኖሚ ስለማያዋጣ ብዝኃ ዘርፍ እና ብዝኃ ተዋናይ በማድረግ ብዙ ጥቅም ለማግኘት ነው በግልፅ መንገድ ሪፎርም የጀመርነው፡፡

፦ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አለባት፤ አምርታ መብላት የማትችል ሀገር ብሔራዊ ጥቋሟን ለማስጠበቅ ትቸገራለች፡፡

፦ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ 27 ሚሊየን ገደማ ሰዎች በሴፍቲኔት የታቀፉ ተረጂዎች ነበሩ፤ ኢትዮጵያ መለመን የለባትም ልጆቿ ተግተው፤ ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው የሚለው ዕምነት ፍሬ አፍርቷል፡፡

፦ ዘንድሮ 23 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ከሴፍቲኔት ተረጂነት መውጣት ችለዋል፤ ኢትዮጵያ ሙሉ በመሉ ከሴፍቲኔት እና ከተረጂነት የተላቀቀች ሀገር እንድትሆን ከሁላችንም ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ፡፡

፦ ባለፈው ዓመት 26 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሶ ነበር፤ በዚህኛው ዓመት ደግሞ 31 ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ተችሏል፤ ኢትዮጵያ ባፈው ዓመት በሁሉም ዓይነት የሰብል ምርቶች 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ኩንታል ምርት ነው የሰበሰበችው፣ ዘንድሮ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ኩንታል መሰብሰብ ተችሏል፡፡

፦ በዚህ ዓመት እስከ መስከረም ባለው ጊዜ ውስጥ ስድስት ከፍተኛ ግድቦች ይመረቃሉ፡፡

፦ በዓመት ሁለት እና ሶስት ጊዜ የማምረት ልምምዳችን የጨመረ ሲሆን፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ብለን የጀመርነው ሥራ በርካት ለውጦችን ማምጣት ችሏል፡፡

፦ የሌማት ትሩፋት ብለን በጀመርነው ሥራ የወተት እና የእንቁላል ምርቶችን ማሳደግ ችለናል፡፡

፦ ምርታማነት እያደገ ሲሆን ከውጭ የምናስገባቸውን ምርቶች መተካት ችለናል ይህንን አጠናክረን ከቀጠለን በብዙ ዘርፍ ውጤታም ልንሆን እንችላለን፡፡

፦ የግብርናው ዘርፍ ትልቅ ትኩረት ያገኘ እና ትልቅ ውጤት ያመጣ ነው፤ ለአጠቃላይ ዕድገታችን ከፍተኛ ድርሻ አለው፡፡

በማንኛዉም ሰዓት ጥቆማና አሰተያየት ለመስጠት
የስልክ መስመራችን ክፍት ናቸው ይደውሉ
ስልክ - 0461809999
0461801609
0964647777
በተጨማሪም ይህንን የፌስቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/wogeta?mibextid=ZbWKwL Follow, Share, Like, በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ለቀጥታ ስርጭት linkኩን ይጫኑ https://zeno.fm/radio/wogeta-fm-96-6-lw1u

ትጋትና ታማኝነት ለብልፅግና!

Address

Wolaitta S**o
S**o
001

Opening Hours

Monday 06:00 - 19:00
Tuesday 06:00 - 19:00
Wednesday 06:00 - 19:00
Thursday 06:00 - 19:00
Friday 06:00 - 19:00
Saturday 06:00 - 19:00
Sunday 06:00 - 19:00

Telephone

+251988705111

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wogeta FM 96.6 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wogeta FM 96.6:

Share