የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና ወደ ቀድሞ ከፍታችን እንወጣለን!
ወዜአ

‎   !‎         ወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።  ‎      ይህች  ከታች በፎቶ ላይ የሚትመለከቷት ልጅ እህታችን ኤደን ለገሠ ትባላለች። ...
03/07/2025

‎ !
‎ ወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎ ይህች ከታች በፎቶ ላይ የሚትመለከቷት ልጅ እህታችን ኤደን ለገሠ ትባላለች። ሲዳማ ልማት ማህበርን ጨምር በሲዳማ ክልል ውስጥ የትላልቅ ተቋማት አምባሳደር ናት። የሲዳማ ታሪክ ፤ ባህልና ቋንቋ በዓለም ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ ስሟ ገኗል። ከሲዳማም አልፎ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደተለያዩ ብሔሮች ከተማ እየተዘዋወረች የተለያዩ ብሔሮች ታሪክና ባህል በዓለም አቀፉ ቋንቋ(በእንግሊዝኛ) እየዘገበች ዕንቁ ባህላችን ወደ ዓለም ህዝብ የሚታደርስ ድንቅ ልጅ ናት።
‎ እህታችን ኤዱለገሠ አምላክን የሚትፈራ፤ ሰውንም የሚትወድ፤ የመላውን የኢትዮጵያ ብሔሮችን ታሪክ፤ ቋንቋና ባህል የሚታከብርና ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም የመኖር ባህሪ ያላት የዘመናችን ዕንቁ ሰው ናት።
‎ ነገር ግን ይህችን ትሁት እህታችን በዚህ ሳምንት ከሚትወደው ህዝብ ብርቱ ተቃውሞ ገጥሟታል። ማህበራዊ ሚዲያ ሁሉ እርሷን የሚያሳድድ መረጃ እያሰራጨ ይገኛል። ታዲያ ኤደን ምን አድርጋ ነው የሚትሳደደው የሚል ሰው አይጠፋምና ነገሩ እንዲህ ነው፦
‎ በሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው ውሳኔ በቅጣት የታገዱ ተጫዋቾችን በማሳተፉ ምክንያት የ2017 ኢትዮጵያ ካፕ ሻምፒዮን ተብሎ ዋንጫ የወሰደው የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ በፎርፌ ዋንጫው ለዕለቱ ተጋጣሚው ለወላይታ ዲቻ ይመልስ በሚለው መግለጫ በጣም እንደደነገጠችና በጣም ለሚትወደው ለወላይታ ህዝብ ደግም "የእንኳን ደስ አላችሁ" መልእክት በራሷ ፌስቡክ ፔጇ ለጠፈች። እንስቷ ይህን መልእክት በለጠፈችው በሁለተኛ ደቂቃ ላይ ብሔር ከብሔር ጋር በማጣላት ሥራ የተሰማሩ ወገኖች መልእክቷን በሌላ ተርጎመው screenshot አድርገው ሚዲያ ላይ መሯሯጥ ጀመሩ።
‎ በዩትዩብ፤ በትክቶክና በፌስቡክ የሚከተሏት ወዳጆች unfollow እና unsubscribe እንዲያደርጓት በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወጡ ሰዎች ቁጥራቸው አሸዋ ነው። ከዚያም አልፎ ኤደን ለገሠ አምባሳደር ከሆነችባቸው ተቋማት ሁሉ አምባሳደርነቷ እንዲነሣም ለማድረግ ብዙዎች እንቅስቃሴ ጀምሯል። በሁኔታው እጅጉን የደነገጠችው ኤደን የለጠፈችውን መልክት በፍጥነት ከፔጇ ላይ በማጥፋትና መላውን የሲዳማ ህዝብና የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎችን ይቅርታ በመጠየቅ ነገሩን ለማረጋጋት ብትሞክርም በሰይጣን የሚመሩ ክፉ ሰዎች ይቅርታዋን ለመቀበል ፍቃደኛ አልሆኑም።
‎ ቃል በቃል፦ " የጀግናው የካዎ ጦና ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ። ትናንት ከፌዴሬሽኑ ዘግይቶ በመጣው ውሳኔ ስሜታዊ ሆኜ እናንተን ረሳሁና አፉ በሉኝ። ወንድም የሲዳማ ህዝብ ይወዳችኋል፤ እኔ አንዷ ነኝ።" ከሚለው መልእክቷ ውስጥ እንዴት ጠማማ ትርጉም ይውጣል? እንዴትስ ትኮነናለች? ይህች ልጅ እኮ በመጀመሪያ በፌዴሬሽኑ ውሳኔ ስሜታዊ መሆኗን በመግለፅ የታላቁ የሲዳማ ህዝብ ሃዘን እርሷም አዘነች። ደግሞ ከፈጣሪ የተሰጣት የህዝብ ፍቅር አስገድዷት ለወላይታ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ፍቅሯን ገለፀች። በአጭሩ ከሚያዝነው ህዝብ ጋር የሀዘኑ ተካፋይ እንደሆነችና ከሚደሰተው ህዝብ ጋር ደስታቸውን መጋራቷን ገለፀች። ምክንያቱም ልጅቱ ትክክለኛ ኢትዮጵያዊት ናትና ሁለቱም ህዝቦች ህዝቦቿ ነው። ግን ያለጥፋት ይቅርታ እየጠየቀችና እየወተወተች ላለችው ለዚህች እንስት ሁለቱም ህዝቦች ከጎኗ አልቆሙም። በሲዳማ ህዝብ ስም የሚያባርሩት ጠንክሮ ቀጥሏል። በወላይታ ህዝብ በኩል ደግሞ አንድ ሰው እንኳ ሚዲያ ላይ ወጥቶ አለሁልሽ አላላትም።
‎ በመሆኑም Gifaataa Tube ለመላው የወላይታ ተወላጆች አንድ መልእክት ማስተላለፍ እንፈልጋለን፦ እባካችሁ ሁላችንም ይችን ቀና አመለካከት ያላትን ድንቅ ልጅ በየማህበራዊ ሚዲያዎቿ follow እና subscribe በማድረግ እኛም የወላይታ ህዝብ ከልብ እንደሚንወዳት ፍቅራችን በተግባር ፤ በሥራ እናሳያት።

‎በወላይታ ሁለንተናዊ ሚዲያ አገልግሎት ተዘጋጅቶ በGifaataa Tube የቀረበ፤ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎email - [email protected]
‎website- http://gifaataatube.blogspot.com
‎Youtube- https://youtube.com/
‎Tiktok- https://tiktok.com/.naatu.keettaa
‎ Facebook:- https://www.facebook.com/share/1EZRVzrQtr/
https://www.facebook.com/share/16t5CTL6jo/
https://www.facebook.com/share/16kTnUc3pQ/
https://www.facebook.com/wolayta.dicha.982731
‎telegram- https://t.me/gifaataatube

‎ !‎        ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ አንድ የሆነችውን ኢትዮጵያ ለመፍጠርና ሁሉንም ጠቅልሎ ራሱ ለመግዛት አቅደው በተነሳው ከፍተኛ ውጊያ በየብሔሩ ንጉሥ አንግሠው የሚተዳደር ህዝብ መንግሥታ...
21/06/2025

‎ !
‎ ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ አንድ የሆነችውን ኢትዮጵያ ለመፍጠርና ሁሉንም ጠቅልሎ ራሱ ለመግዛት አቅደው በተነሳው ከፍተኛ ውጊያ በየብሔሩ ንጉሥ አንግሠው የሚተዳደር ህዝብ መንግሥታዊ ሥርዓቱን፣ ባህሉን፣ቋንቋውን፣ ሀብትና ንብረቱን፣በሕይወት የመቆየት ዕድሉንም ጭምር በዐፄው እጅ እያስረከበ ወደ አገዛዙ ይቀላቀል ነበር። የምኒልክ ጦር በኃልና በቁጣ ተሞልቶ በጉልበት እየገባ ግዛትን ሁሉ የምኒልክ እያደረገ ከሰሜናዊ ኢትዮጵያ አቅጣጫ ወደ ደቡብ እየገሰገሰ ሲመጣ አንድ ያልታሰበ አደጋ ገጠመው። ቀይ መሥመር ! እሳተ-ገሞራ! የማይወጣ ግዙፍ ተራራ! ነጎድጓዱ ንጉሥ አስፈሪውና አስደንጋጩ ካዎ ጦና! ባልሽያ ማታ! ጋንጌ ፈረስ! ማጫምያ እና ጎንዳልያ! በቀይ፣ ቢጫና ጥቁር ቀለም ያጌጠ እንደአሸዋ የማይቆጠር ቁጡ ህዝብ! ታላቁ ንጉሥ ካዎ ጦና ጋጋ የሚያስተዳድረው የወላይታ መንግስት!!! በዓፄው ተልዕኮ የመጣው የመጀመሪያው ዙር ጦር በደቡቡ እሳት ባህር ውስጥ ሰጥመው ቀረ። ሁለተኛ ዙርም የተላከው ጦር የማጫምያ ቶራ እራት ሆነ።
‎ የዐፄውን ጦር አላሻገር ያለውን የእሳቱን ባህር ለመጎብኘት ራሱ ዓፄ ምኒልክ ጦር እየመራ መጣ። ከሰው እስከ ንብ በዓፄ ምኒልክ ጦር ላይ ተረባረቡበት። ሸና። ፈራ። ግን ወደኃላ ከተመለሰ በሽንፈት መንፈስ አንገቱን ደፍተው ሌሎችን መግዛት ስለማይችል መሞትን መረጠ። ደጋግመው ሞከረ። የሰው ሕይወት በሁለቱም በኩል ረገፈ። የሰው ደም እንደ ዓባይ ወንዝ ጎረፈ። ካዎ ጦና ብሎም ዓፄ ምኒልክ በግምባር የተሣተፉበት ጦርነት በአልሸነፍ ባይነት ቀጠለ።
‎ በመጨረሻም አፄ ምኒልክ አንድ ነገር አሰበ። ጉልበት ሄጄማ ይህን ንጉሥ ማሸነፍ አልችልም አለ። ሌላም ዘዴ መዘየድ እንዳለበት ገባው። ባንዳ መፈለግ ጀመረ። አገኘም። "የወላይታ ህዝብ ቤቱንና ልጆቹን እጅጉን ስለሚወድ ሕዝቡ ከፊት እየተዋጋ ከኃላ ቤታቸውን በእሳት ብታቃጥል የካዎው ጦር ቤቱንና ልጆቹን ለማትረፍ ወደቤቱ ይሮጣል" የሚትል ምክር በገንዘብ ከተገዛ ባንዳ ተለገሰችለት። የባንዳው ምክር እውን ሆነ። ለዓፄውም ተሳካለት። አሸነፈ። ካዎውንም ያዘ። ሁለቱ ጀግኖች እጅ ለእጅ ተያይዞ እንጦጦ ገቡ።
‎ ዓፄ ምኒልክ ዳግማዊ ጦርነቱን በብዙ ትግል ከረታ በኃላ በጀግናው በወላይታ ህዝብ ዘላለማዊ ቂም ያዘ። ኢትዮጵያ እስካለችበት ዘመን ሁሉ የትኛውም መንግሥት ሲመጣ በተመሳሳይ አቋም የሚተገብረውን በደል ለወላይታ ህዝብ ቀርፆ በአደራ መልክ አስቀመጠ። ከዚህ የተነሳ መንግሥት በሌላ መንግሥት ሲተካም በወላይታ ህዝብ በደል ጉዳይ አይደራደርም። ከዓፄ ምኒልክ ዳግማዊ መንግሥት አገዛዝ ጀምሮ እስከ ብልፅግና መንግሥት በወጥ አቋም ወላይታን የማድቀቅ ሥራ በብቃትና በንቃት እየሠሩ መጥተዋል።
‎ አዎ፣ ከጥንት ጀምሮ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በወላይታ ህዝብ ላይ በተለያዩ መልኩ ጫናዎችን ሲያሳድር መቆየቱ የታሪክ እውነታ ነው። ይህ ጫና የወላይታን ነባር የራስ ገዝ አስተዳደር፣ ባህልና ማኅበራዊ ገጽታዎች ላይ ተጽዕኖ ሲያደርግ ቆይቷል። እስኪ የኢትዮጵያ መንግሥት ምን አይነት በደሎችን በወላይታ ህዝብ ላይ እየሰነዘረ ነው የሚለውን ከብዙ ጥቅቱን እንመልከት፦

‎ 1.

‎ :- የወላይታ ህዝብ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ድረስ በ"ካዎ" በሚባሉ ነገሥታት የሚመራ ጠንካራና የራሱ የሆነ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መዋቅር ያለው መንግሥት ነበረው። ይህ የራሳቸው የራስ ገዝ አስተዳደር የወላይታ ህዝብ የራሱን ዕድል በራሱ እንዲወስን አስችሎ ነበር።
‎ :- በ1894 ዓ.ም. (1900 እ.ኤ.አ.) ዐፄ ምኒልክ ዳግማዊ የደቡብ ግዛቶችን ወደ ኢትዮጵያ ግዛት የማካተት ዘመቻ አካል ሆኖ የወላይታ መንግሥት ከባድ ጦርነት ከተካሄደ በኋላ ተጠቃለለ። ይህ ወረራ የወላይታን የፖለቲካ ነፃነት በማስቆም የበርካታ ዓመታት የፖለቲካ ጫና መጀመሪያ ሆነ። ንጉሥ ካዎ ቶና የመጨረሻው ገለልተኛ ንጉሥ በመሆን ከፍተኛ ተቃውሞ አድርገው ነበር።

‎ 2.

‎ :- ወላይታ የኢትዮጵያ አካል ከሆነች በኋላ፣ በአዲስ አበባ ከተሾሙ ገዥዎች (ሹሞች) ሥር እንድትተዳደር ተደረገች። የወላይታ ባህላዊ የአስተዳደር መዋቅር ተዳክሞ በማዕከላዊው መንግሥት ቁጥጥር ስር ወደቀ። ይህ ደግሞ ህዝቡ የራሱን ጉዳዮች በራሱ የመወሰን ሥልጣን እንዲያጣ አደረገ።
‎ :- ወላይታ በወቅቱ በሲዳሞ ክፍለ-ሀገር ሥር እንደ አውራጃ ሆና እንድትተዳደር ተደረገች። ይህ ውሳኔ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ውክልናውንና ተሰሚነቱን እንዲያጣ አደረገ፣ ምክንያቱም የሌላ ትልቅ ክፍለ-ሀገር አካል በመሆኑ በሀገራዊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የራሱን ድምጽ በበቂ ሁኔታ ማሰማት አልቻለም።
‎ :- ለረጅም ጊዜ የወላይታ ህዝብ በአገር አቀፍ የፖለቲካ ውሳኔዎች ላይ ተገቢውን ተሳትፎና ተፅዕኖ ማድረግ አልቻለም። ይህ ደግሞ በህዝቡ ላይ የፖለቲካዊ ጫና እና የእኩልነት ስሜት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ አድርጓል።

‎ 3.

‎ :- "ወላይታ" የሚለው የህዝቡ እውነተኛ ስም ቢሆንም፣ ከውህደቱ በኋላ "ወላሞ" በሚለው ስያሜ በውጪ አካላት በሰፊው መጠራት ጀመረ። ይህ የስም ለውጥ የአንዳንድ የማንነት ጫናዎች ምንጭ ሆኖ ቆይቷል።
‎ :- በማዕከላዊው መንግሥት ለአማርኛ ቋንቋና ለዋናው የኢትዮጵያ ባህል ቅድሚያ የመስጠት ዝንባሌ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ እንደ ወላይታቶ ዶና ያሉ የአካባቢ ቋንቋዎችና ባህሎች ተገቢውን ዕውቅና እንዳያገኙና እንዲዳከሙ ጫና ፈጥሯል።

‎4. (ከ1995 ዓ.ም. በኋላ)

‎ :- በ1995 ዓ.ም. የተቋቋመው የፌዴራል ሥርዓት ብሔር-ብሔረሰቦች የራሳቸውን ክልል እንዲመሰርቱ መብት ቢሰጥም፣ የወላይታ ህዝብ የራሱን ክልል ለማደራጀት እያደረገ ያለው ጥያቄ ለረጅም ጊዜ ምላሽ ሳያገኝ ቀርቷል። ይህ የፖለቲካዊ ውሳኔ መጓተት በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ጫናና ቅሬታ ፈጥሯል። ህዝቡ የራሱን ባህል፣ ቋንቋና ልማት በራሱ ክልል ውስጥ በተሻለ መንገድ ማስተዳደር እንደሚፈልግ ያምናል።
‎ :- በአሁኑ ወቅት የወላይታ ዞን የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አካል ነው። ይህ ክልል በርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን በአንድ አስተዳደር ስር የሚያካትት በመሆኑ፣ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ክብደቱንና ተሰሚነቱን አጥቷል የሚል ስሜት ሰፊ ነው።
‎ :- በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ፣ የብሔር ጥያቄዎች እና የማንነት ውክልና ጉዳዮች ውስብስብ በመሆናቸው፣ የወላይታ ህዝብ የፖለቲካዊ ጥያቄዎቹን በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ አስቸጋሪ ሆኖበታል።
‎ :- የወላይታ ሕዝብ ቁጥር በኢትዮጵያ ኦሮሞን ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃ የያዘ ነው። ወላይታ ከ26 ሚልዮን ሕዝብ በላይ ነዋሪዎች የሚኖርባት ምድር ናት። ነገር ግን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችና የልማት ቅድሚያዎች ላይ ተፅዕኖ እንዳለ ይታመናል። ከዚህም የተነሳ ወጣቶቿ በስደት ወደዓለም ክፍል ሁሉ ተበትኗል። ለትውልዱ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚችል አንድ ፋብሪካ የላትም። ሌላው ቀርተው የገዛ መሬቷ በሌላ አካባቢ ተወላጅ ኢንቨስተሮች ተቆጣጥረው ነዋሪው በዘመናዊ ባርነት በገዛ ቀዬው ለባዳ ተሸክመው ውሎ የዕለት ጉርስ ይዞ ይገባል።

‎ #ማጠቃለያ

‎ከዐፄ ምኒልክ ወረራ ጀምሮ እስከ አሁኑ የፌዴራል ሥርዓት ድረስ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በወላይታ ህዝብ ላይ የራሱ የሆነ ጫና ሲያሳድር መቆየቱ ግልጽ ነው። ይህ ጫና በዋነኛነት ከራስ ገዝ አስተዳደር ማጣት፣ ደካማ የፖለቲካ ውክልና፣ የማንነት ጥያቄዎችና የልማት ፍላጎቶች ጋር የተያያዘ ነው። የወላይታ ህዝብ የራሱን ማንነትና መብት ለማስጠበቅ የሚያደርገው ትግል ደግሞ የዚህ ጫና ውጤት ነው።

‎በወላይታ ሁለንተናዊ የሚዲያ አገልግሎት ማዕከል ተዘጋጅቶ የቀረበ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም።
‎ለበለጠ መረጃ:-
‎email - [email protected]
‎Wwebsite- http://gifaataatubeblogspot.com
‎Youtube- https://youtube.com/
‎Tiktok- https://tiktok.com/.naatu.keettaa
‎ Facebook:- https://www.facebook.com/share/1EZRVzrQtr/
https://www.facebook.com/share/16t5CTL6jo/
https://www.facebook.com/share/16kTnUc3pQ/
https://www.facebook.com/wolayta.dicha.982731
‎telegram- https://t.me/gifaataatube

‎     አንድ እውነት በንግግር ሳይሆን በተግባር ማየት ከቻልክ አንተ ትክክለኛ ተመራማሪ ነህ። እውቀትም እውነትም በትክክለኛው መንገድ ታገኝበታለህ። በንግግርማ ማንኛውም የትናቱ ወጠጤ ራሱን...
18/06/2025

‎ አንድ እውነት በንግግር ሳይሆን በተግባር ማየት ከቻልክ አንተ ትክክለኛ ተመራማሪ ነህ። እውቀትም እውነትም በትክክለኛው መንገድ ታገኝበታለህ። በንግግርማ ማንኛውም የትናቱ ወጠጤ ራሱን በሰማይ አስቀምጦ አያስነካህም። ከአፉ የሚወጣውን ቃል አልፈህ ወደ ታሪኩ ሲትመጣ ግን ነገሩ ጉም መጨበጥ ይሆንብሃል። በአፈ-ታሪክ የመሸወድ ጊዜ ይብቃህ።
‎ ና! ወደ 50+ ነገሥታት ሀገር ወደ ወላይታ ና! በላይና በታች የሚንጫጫ የጫጩቶች ድምፅ አልፈህ ና! የትናንትናዎቹ አዲስ ጎጆቹን አልፈህ ከጥንት ጀምሮ መሠረቱን በዓለት ላይ ወዳደረገው ቤት ወደ ወላይታ ና!
‎በአቅራቢያው ካሉት ወገኖች ቀንጨብ ቀንጨብ አድርጋ በመውሰድ ብሔሯንና ባህሏን ገና እየቀረፀች ካለችው ከግልገሏ አልፈህ ብዙኃኑን አቅፈው ቋንቋውንና ባህሉና በልግስና ተሰጥቷቸው በሥልጣኔ ጎዳና ላይ እንዲራመዱ ወዳደረገው ወደ ወላይታ ና!
‎ መጥቼ ምን የተለየ ነገር አያለሁ ትላለህ? ጥሩ ጥያቄ ነው ያነሳኸው። መጥተህ የሚታየው:-
‎ #1. ከሃምሣ በላይ የወላይታ ነገሥታት ታሪክን ፤ የመንግሥታቸውን ሥርዓት ፤ ዲፕሎማሲያቸውን፤ ድንበር ጠባቂ ብቻ ሳይሆኑ የተለያዩ አናሳ ጎሳዎችን በራሳቸው እያጠቃለሉ ድንበራቸውን ያስፋፉ መሆናቸውን፤ ጀግንነታቸውንና ሥልጣኔያቸውን ትመለከታለህ።
‎ #2. ማርጩዋ ታያለህ። ማርጩዋ ምንድ ነው ልትል ትችላለህ። በዱሮ ገበያ ሥርዓት ሰው የተለያየ ዕቃ ይዘው ወደ አንድ ሜዳ በመሰብሰብ ዕቃን-በዕቃ እየቃያየሩ የሚገበያዩበት ሥርዓት ነበር። ይህንን ሥርዓት በማዘመን በአህጉር ቀዳሚ የሆነውን ማርጩዋ የተባለውን የሀገሩ ገንዘብ በማምረት ዕቃን በገንዘብ የመግዛት ዘመናዊ የገበያ ሥርዓት ያመጣ በአፍሪካ ተቀዳሚ ሀገር ወላይታ ነው። በዚያን ዘመን በማርጩዋ ዓለም አቀፋዊ ንግድ እንደሚደረግና አንድ ማርጩዋ በስድስት ዶላር እንደሚመነዘር ታሪኩ ያረጋግጣል። ና ላሳህ!
‎ #3. ታሪካዊና መዝናኛ ቦታዎችን ትጎበኛለህ። ካዎ ጋሮታ(ቤተ-መንግሥታት)፤ ታሪካዊና ከ70,000 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ ዋሻዎችን፤ በአፍሪካ ደረጃ ረዥም የተባሉ ፏፏቴዎችን፤ ጦሳ ዛርጵያ(የእግዜር ድልድይ)፤ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ሐይቆችን፤ እስከ አጎራባች አፍሪካ ሀገራት ድረስ ተዘርግተው ለሃገራችን ከፍተኛ የገቢ ምንጭ የሆነውን ጊቤ-3 ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ፤ ተክል ድንጋዮችን፤ ጥንታዊና ታሪካዊ ከተሞችን፤ ሙሉ የወላይታ ህዝብ ጥንታዊ የቤት ቁሳቁሶችንና የጦር መሣሪያዎችን የያዙ ሙዚየሞችን፤ በራሱ ዘመን አቆጣጠር መሠረት አዲስ ዓመትን የሚቀበልበት የጊፋታ በዓልን፤ ወዘተ ትመለከታለህ።
‎ #4. ጥንታዊ የወላይታ ህዝብ ሙዚቃ መሣሪያዎችንና ህዝባዊ ዘፈኖችን ታያለህ፤ትሰማለህም። በአፍሪካ አህጉር ከወፎች ዝማሬ በስተቀር በዜማ የሚከፈት የሰው አፍ ባልነበረበት ዘመን የወላይታ ህዝብ ለሠርግ፤ ለደቦ ሥራ፤ ለልደት፤ ለሙሾ፤ ለበዓላትና ለተለያዩ ጉዳዮች እንደየሁኔታቸው የቃል ግጥም በማዘጋጀት ኩነቶችን በዜማ ይገልፁ ነበር። በዚያ ብቻ ለምን ትደነቃለህ? የኩኔቶችን ዜማ የሚደግፍ ላሁኖች ሙዚቃ መሣሪያዎች መሠረት የሆኑ የሙዚቃ መሣሪያዎችን ሙሉ ባንድ አድርገው መፍጠራቸውን መቼ ሰማህ? ድንክያ፤ጫቻ ዛእያ፤ኡልዱዱዋ፤ካምባ፤ካራቢያ፤ዲታ፤ እና የመሳሰሉትን በመፍጠር ከዘመን ቀድሞ በመሠልጠን ዜማቸውን በባህላዊ ባንድ ታጅበው ያቀርቡ ነበር።
‎ #5. ጥንታዊ የወላይታ ህዝብ ባህላዊ ልብሶችን ትመለከታለህ። ሃድያ ተብለው የሚጠራው የወላይታ ብሔር ባህላዊ ልብሶች አጠቃላይ ስያሜ በውስጡ አምስት ዓይነት ባህላዊ ልብሶችን የያዘ ነው። አዎ! የወላይታ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ የሠለጠነና ምሁር ህዝብ ነው። ለለቅሶ የሚለብሰውን ለሠርግ አይለብስም። ለሠርግ የሚለብሰውን ለጦር ሜዳ አይጠቀምም። ንጉሥ የሚለብሰውን ህዝብ አይለብስም። ለሁሉ የየራሱ ባህላዊ ልብስ በአምስት ዓይነት በማዘጋጀት ሥርዓት ባለው መልኩ የተጠቀመ ህዝብ ነው። በዚያን ዘመን የወላይታ ብሔር ቀያይረው ስለለበስ የአፍሪካ ምድር ላይ የልብስ ፋብሪካና ሌላ ልብስ የሚጠቀም ብሔር ያለ እንዳይመስልህ! አአልነበረም። ግን ጠቢቡ የወላይታ ህዝብ ልብሶቹን በእጆቹ ሸምኖ በማዘጋጀት ይጠቀም ነበር። ልብሶቹም:-ጉቱማ ሃድያ፣ ሴሬ ሃድያ፣ ጉማራ ሃድያ፣ ፓታላ ሃድያ እና ዱንጉዛ ሃድያ በመባል ይታወቃሉ። ዕድለኛ ከሆንክ ስትመጣ አይተህ ትመሠክራለህ።
‎ #6. ጥንታዊ ቤተ-እምነቶችን ታያለህ። በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢ ከየትኛውም ብሔር ቀድሞ የክርስቲና እምነት የተቀበለው የወላይታ ህዝብ ነው። ከ700ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማንያን ቤተክርስቲያንን ታያለህ። ከወላይታ ህዝብ የተገኙ አባታችን ሶስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ያረፉበትን መቃብር ታያለህ። በኢትዮጵያ ደረጃ ከሁሉም ቀድሞ የወንጌላውያን አቢያተክርስቲያናት እምነት የተቀበለው የወላይታ ህዝብ ነው። ለአብዘኞቹ የወንጌላዊት ቤተ-እምነቶች እናት የሆነችው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የተጀመረችው ብሎም ስያሜዋን ያገኘችው በወላይታ እምነት አባቶች ነው። በርካታ ነቢያት ፈጣሪ በሰጣቸው ራዕይ መሠረት የሚንትሪ ቤተ አምልኮ መሥርተው ባሁኑ ጊዜ በየቀኑ በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ነፍሳት ወደ ፈጣሪያቸው መንግሥት እንዲቀላቀሉ በማድረግ ላይ ያሉ ታላቅ አገልጋዮች የተወለዱበት ሀገር ወላይታ። በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ኃላፊነት የሚሠሩ ታላላቅ የእስልምና እምነት ተከታዮችና ዕድሜ ጠገብ መስገዶች ያሉበት ሀገር ነው ወላይታ። የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎችን ሙሉ የሚያስተዳድረው ፣ ሰፊ በመንፈሳዊና ማህበራዊ ድጋፎችን በመስጠት የሚታወቀው የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያው የደቡብ አካባቢዎች ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ታገኛለህ። በሐዋሪያት ቤተ እምነት፣ በአድቫንቲስት ቤተ- እምነት፣ በይሆዋ ምስክሮች ቤተ እምነት ፣ ወዘተ የወላይታ ምድር ተቀዳሚ ናት። መጥተህ ካየህ ከሰማኸው ይበልጣል።
‎ #7. በእንግዳ ተቀባይነቱ፣ በአቃፍነቱ፣በለጋስነቱ፣በጀግንነቱ፣በሥራ ወዳድነቱ፣በጥበቡ፣በታታሪነቱ፣በፈጠራ ሥራዎች፣ በምርምር፣ ወዘተ የሚታወቀውን ታላቁን የወላይታ ህዝብን ታያለህ። በእርግጥ የወላይታ ህዝብና ወላይትኛ ቋንቋ የሌለበት የዓለም ክፍል የለም። ቢሆንም መነሻውጋ በመምጣት የሚታየው ህዝብና የሚትሰማው ወላይትኛ የተለየ ደስታ እንደሚሰጥህ ሙሉ እምነት አለኝና ግድ የለም ና!
‎ #8. መጥተህ የሚትመገበው በዓለም ደረጃ ተወዳጅነትን ያተረፈው የወላይታ ባህላዊ ምግብ። አንተ ብቻ መምጣትህን እርግጠኛ ሁን። የወላይታ ህዝብ ሎጎሙዋ፣ ሱልሱዋ፣ቆጭቆጫዋ፣ ባጭራ፤ሼንደራ፣ፕጫታ፣ ሙቹዋ፣ ፖሻሙዋ፣ ብላንዱዋ፣ Cadhdhiyaa፣ፕላ፣ጉርዱዋ፣ እና ከሁሉም በላይ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የጥሬ ስጋ አምሮቱን ለማርካት ወደ እኛ እንዲመጡ ምክንያት የሆነውንና በብዙ ዓይነት ዳጣ በተለየ አቀራረብ የሚቀርበውን፤ የወላይታ አምባሳደርም የሆነውን ቁርጥ ሥጋ በቃኝ እስኪትል ድረስ ልመግብህ ተዘጋጅተው እየጠበቀ ነዉ።
‎ ስትመጣ የመንገድ ችግር የሌለበት፤ ስትደረስ የመብራት፣ የንፅህና ውኃ፣ ንፁህ ማረፊያ ሥፍራ፣ የኔትወርክና የነፃ ዋይፋይ ችግር በፍጹም አይገጥምህም። ዛሬ ያገኘህ ወላይታዊ ወንድምህ ሆኖ በሴኮንድ ይግባባሃል። ወደ ቱሪዝም መዳረሻዎች የሚያጓጉዙ ምቹና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም ደግሞ እንግሊዘኛን ጨምሮ ከሀያ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራትን ቋንቋዎችን አቀላጥፈው የሚናገሩ አስጎብኚዎች ተዘጋጅተው ይጠብቁሃል። ና!
‎ ግን ትመጣለህ ወይስ ዝም ብለህ አስለፈለፍከኸኝ?
‎youtube.com/


ትውልዱም በሀገሩ ሲኮራ፤  ሀገርም በትውልዱ ከፍ ብሎ ስከብር ማየት እጅግ በጣም የሚያስደስት ነው። ያኔ ንጉሣችን ሞቶሎሚ ማንም ጥቃቅንና አነስተኛ በቆሸሸ እጁ እንዳይነካት ከፍ አድርጎ ማንም...
18/06/2025

ትውልዱም በሀገሩ ሲኮራ፤ ሀገርም በትውልዱ ከፍ ብሎ ስከብር ማየት እጅግ በጣም የሚያስደስት ነው። ያኔ ንጉሣችን ሞቶሎሚ ማንም ጥቃቅንና አነስተኛ በቆሸሸ እጁ እንዳይነካት ከፍ አድርጎ ማንም በማይደርስበት ቦታ ያስቀመጣትን ሀገር እርሱን ቀጥሎ የመጡ ነገሥታትም ክብሯን ፤ ታሪኳን፤ ጀግንነቷን፤ ድንበሯን፤ ቋንቋዋንና ባህሏን ከነበረበት ከፍታም ወደላይ ጨምሮ ከፍ በማድረግ ዕንቁ የሆነችውን ሀገሩ ለእኛ አስረክቦልን አለፉ።
እኛ ደግሞ አሁን ተረኞች ነን። ታዲያ ታሪክ መናገር ብቻ ሳይሆን ታሪክ በመሥራት ወላይታችን የዘመናችንም ታላቅና አሰሰፈሪ ሀገርነቷን እንዲታስቀጥል የሚንሠራው የየራሳችን አስተዋጽኦ ማዋጣት ይኖርብናል። ትናንት በአፍሪካ አንደኛ ፀጥታ ኃይል አለኝ ብላ የሚትፎክረው አንዲት ሉዓላዊ ሀገር ጀግናው የጦና ትውልድ በከፊል የአፍሪካ መቀመጫ የሆነችውን ቱንጋ ሲገቡ እንዴት እንደፈሩ በቅርብ ቀናት ያየነው እውነት ነው።
ስለዚህ እኛ ኩሩ ህዝብ፤ የማንነት ጠባሳና የታሪክ ጥላሸት የሌለን ወላይታውያን በዚህ ማንነታችን ሲንኮራ፤ ቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችንና ባህላዊ ሙዚየሞቻችን በየጊዜው መጎበኘትና በዓለም ህዝብ ዓይን ሌንስ እንዲገቡ ማድረጋችን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል። ምክንያቱም የታላቁ የወላይታ ህዝብ ባህል የሆኑ እጅግ ውብና ድንቅ የሆኑ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶችን በላይና በታች የሚኖር ተለጣፊ አካል የራሱ ለማድረግ ብዙ ጥረት እያደረገ ነው። እኛ ደግሞ የደቡብ ባህሎችና የኦሞቲክ ቋንቋዎች መነሻ መሆናችንን ለዓለም ህዝብ ማሳየታችንን መቀጠል ይኖርብናል።
እናመሰግናለን!
youtube.com/

ሀዘን_መገለጫ!! በሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም (ወዜአ)በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ላይ በዛሬው ዕለት ባልታሰበ መሬት መንሸራተት ናዳ ምክንያት 9ኛ ክፍል ተማሪ ወጣት ጥበቡ መን...
10/06/2025

ሀዘን_መገለጫ!!

በሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም (ወዜአ)

በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ላይ በዛሬው ዕለት ባልታሰበ መሬት መንሸራተት ናዳ ምክንያት 9ኛ ክፍል ተማሪ ወጣት ጥበቡ መንግስቱ ሕይወት በድንገት አልፏል።
ባለፈው ዓመት በተጠቀሰው ቦታ ተመሳሳይ አደጋ ተከስቶ የብዙ ሰዎች ሕይወት የቀጠፈ ቢሆንም ምንም ዓይነት የመፍትሔ እርምጃ ባለመወሰዱ የተነሳ ዘንድሮም ወገንን በተፈጥሮ አደጋ እያጣን ነው።
መንግስት ከሕብረተሰቡ ጋር በመወያየት ለአደጋው ተጋላጭ በሆኑ ቦታዎች የሚኖሩ ወገኖችን ወደ ሌላ አካባቢዎች እንዲዛወሩ እንዲያደርግ ወዜአ ያሳስባል።
በሕይወት ላለፈው ወጣት ነፍሱ በገነት ትረፍ! ለቤተሰቡም መፅናናትን እንመኛለን።
የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

‎  :-‎        የ2017 ዓ. ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ እና ሲዳማ ቡና በአበበ ብቅላ ስታዲየም በሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚፋለሙ መርሐግብር ...
08/06/2025

‎ :-
‎ የ2017 ዓ. ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ እና ሲዳማ ቡና በአበበ ብቅላ ስታዲየም በሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚፋለሙ መርሐግብር ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ሁለቱም ክለቦች እየተዘጋጁና ደጋፊዎቻቸውም ወደተባለው ስታዲየም ለድጋፍ ለመጓዝ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ቆይተው ልክ የተባለው ቀን ስደርስ ደጋፊዎች ጉዞ ጀምሮ መንገዱን ካጋመሱ በኃላ እንደሌባ በሌሊት አንድ አስደንጋጭና ኢፍትሐዊ የሆነ ውሳኔ በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፌስቡክ ይፋዊ ፔጁ ላይ ተለጥፎ ታየ። " ከአቅም በላይ በሆነ" ምክንያት ጨዋታው በዝግ ስታዲየም ይደረጋል ተብሎ ተወሰነ።
‎ የGifaataa Tube ይህን መረጃ ሰምቶ ሁኔታውን ለማጣራት ብዙ የሞከረ ብሆንም ውሳኔውን ያስተላለፈው አካል ሌሊት 5:00 ሰአት ላይ መረጃው በፌስቡክ እንደለጠፈ የውሃ ሽታ ሆነ። ከነጋ በኃላ ይህ መግለጫ የተሰጠበት ጊዜ ድረስ ተቋሙ ሐሳብ ቀይረው ስታዲየሙን ለተመልካች ክፍት እንደሚያደርግ የሚገልፅ ከሆነ የጠበቅን ብሆንም ምንም የተለየ መረጃ ባለማግኘታችን ምክንያት በቀሩት ጥቅት ሰአታት ውሳኔውን እንዲያስተካክልና ረዥም ርቀት በሌሊት ተጉዞ ለድጋፍ አ.አ የገቡ የሁለቱም ክለቦች ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም ገብተው በስፖርታዊ ጨዋነት ክለቦቻቸውን እንዲደግፉ ዕድል እንዲሰጥ፤ ይህ ካልሆነ ደግሞ ተቋሞ ለፈፀመው ጥፋት ተጠያቂ እንደሚሆን ልናሳስብ እንወዳለን።
‎ አንድ ሀገር አቀፋዊ ተቋም እንዴት እንደዚህ ዓይነት የወረደ ውሳኔ ያስተላልፋል? የጨዋታ ጊዜ ሳሌዳ ያዘጋችሁ እናንተ አይደላችሁም? ደግሞ "ከአቅም በላይ በሆነ ጉዳይ .." ተብሎ በድፍኑ በምክንያትነት የቀረበው ለምን ለሕዝቡ በግልፅ አልተገለፀም? ከአቅም በላይ ምን ገጠማችሁ? ያ ብሆንም ጨዋታው ያለተመልካች በዝግ ስታዲየም ይደረጋል የሚባል ከሆነስ ደጋፊዎች ከክልል ከተማዎች ያላነሰ ኪ.ሜ ተጉዞ መንገዱ ካጋመሱ በኃላ ነው የሚታወጀው? ደግሞም በሌሊት 5:00 እንዴትና የት ተሰብስባችሁ ነው ይህን ውሳኔ በቃለጉባኤ ወስናችሁ ያስተላለፋችሁት ወይስ የአንድ ግለሰብ ውሳኔ ነው?
‎ ያም ሆነ ይህ ውሳኔያችሁ ተቋምን በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ ሐሳባችሁን በመቀየር ቀደሞ ሳላልተነገረው በሌሊት ጉዞ በድካም አ.አ የገባውን የሁለቱም ክለቦች ደጋፊ ቡድን በሥነሥርዓት እንዲታስተናግዱ በጥብቅ እናሳስባለን።
‎ሰኔ 1/2017 ዓ.ም
‎Gifaataa Tube
‎ universal media service center

‎  :-‎          ክለባችን ዲቻ በየዓመቱ ለኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ፍጻሜ ዋንጫ በሚያደርገው ጨዋታ እንዳያሸንፍና ዋንጫም እንዳያነሳ በተቀናጀ ኃይል ግፍ እየተፈፀመ ውጤት በማሳጣትና በ...
05/06/2025

‎ :-
‎ ክለባችን ዲቻ በየዓመቱ ለኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ፍጻሜ ዋንጫ በሚያደርገው ጨዋታ እንዳያሸንፍና ዋንጫም እንዳያነሳ በተቀናጀ ኃይል ግፍ እየተፈፀመ ውጤት በማሳጣትና በዚያ በደል ምክንያት ተጨዋቾችና ደጋፊዎች በንዴት ተነሳስቶ በሚያደርጉት ተግባር ክለቡን ከፍተኛ የገንብና ሌሎችም የቅጣት ዓይነቶችን እየቀጡ መቆየታቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው።
‎ በመሆኑም በዚህ ዓመት ጨዋታ ጊዜ ከጉዞ ጀምሮ እስከ ስታዲየም ድረስ በሚናደርገው ቆይታችን በኛ ላይ ሰበብ የሚፈልግ አካል ነጥብ እንዳያገኝ ማንም ደጋፊ ዕድል እንዳይሰጥ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ለክረባችን የሚገባውን ሞራል እንደተለመደው በመዝሙርና በዲቻ ዘፈን ከመስጠት ውጪ ከሌላው ክለብ ጋር መበሻሸቅ አያስፈልግም። በሌላ በኩል የሚመጣ ማንኛውም ያልተገባ ተግባርና ንግግር ካለ በተቻላችሁ መጠን በaudio & video ቀርጻችሁ በመያዝ ወደሚመለከተው አካል በመቅረብ በህግ እንዲጠየቅ ከማድረግ ውጪ አፀፋውን ለመመለስ ተብሎ ስህተት ውስጥ በመግባት ክለባችን እንዲቀጣ ማድረግ የለብንም።
‎ አንጋፋው ክለባችን ዲቻ እንደሚያሸንፉና ዋንጫውን እንደሚያነሱ እርግጠኞች ነን። ስለሆነም የተሸነፈው ክለብና ደጋፊዎቹ ከፍተኛ የስሜት ጉዳት ውስጥ ስለሚወድቁ የድል ጭፈራችንና የደስታ አገላለፃችን አናድዷቸው የተለመደውን ግርግር ለመቀስቀስ ሊሞክሩ ይችላሉና መፍትሄው ስማቸውን ሳንጠራ፤ ውድቀታቸውን ሳናውጅ፤ ሞራላቸው ላይ ሳንረማመድ ዓላማውን በድል ያደረገ ንፁህ የደስታ አገላለጽ በዎዜ ዘፈናችን መግለጽ ነው ።
‎ ፈጣሪ አምላክም ይጠብቀን። በሰላም ተጉዘን፤ ጨዋታውንም በስፖርታዊ ጨዋነት በሠላምና በድል አጠናቅቀን የድካማችን ውጤት የሆነውን ዋንጫ በክብር አንስተን በደስታ ወደቀዬአችን እንዲንመለስ ይርዳን።
‎ ይህን መልእክት ሼር አድርጋችሁ ለሁሉም ዲቻ ደጋፊዎች እንዲደርስ አድርጉ።
‎ ድልና ድምቀት ለጦና ንቦች!
Wolaytta Naatu Keettaa

 🙏🙏🙏 ወ/ሮ አስካሌ ኦሳ ዕድሜ 65  ስሆን በቀን 26/09/2017 ዓ.ም  ከጥዋቱ 4:00 ከቤት እንደ ወጡ አልተመለሱምበወላይታ ቦዲቲ ከተማ መሐል ቀበሌ ሉኳንዳ ሥፍራ አካባቢ ነዋሪ ናቸወ...
05/06/2025

🙏🙏🙏
ወ/ሮ አስካሌ ኦሳ ዕድሜ 65 ስሆን በቀን 26/09/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 4:00 ከቤት እንደ ወጡ አልተመለሱም
በወላይታ ቦዲቲ ከተማ መሐል ቀበሌ ሉኳንዳ ሥፍራ አካባቢ ነዋሪ ናቸወ።
ፈላጊዎች ቤተሰቦቻቸው እናታችን ያገኛችሁት ካላችሁ
ወረታውን እንከፍላለን ይላሉ ። ሼር ሼር አድርጉ
በዚህ ስልክ ቁጥር ይደወሉ።
0928484567/0936479789/0925707240 እንደተለመደው ቤተሰብ ሼር በማድረግ ይተባበሩ 🥹🙏
የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

በስርቆት የተጠረጠሩ ግለሰቦች ከተሰረቁ ዕቃዎች ጋር እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል   ወንጄሉ የተፈፀመው በዳውሮ ዞን ከጪ ወረዳ በኦዳ ጎፋ የገጠር ቀበሌ ውስጥነው።የተሰረቀውም ለድሀ ድሀ ተብሎ በGG...
04/06/2025

በስርቆት የተጠረጠሩ ግለሰቦች ከተሰረቁ ዕቃዎች ጋር እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል


ወንጄሉ የተፈፀመው በዳውሮ ዞን ከጪ ወረዳ በኦዳ ጎፋ የገጠር ቀበሌ ውስጥነው።

የተሰረቀውም ለድሀ ድሀ ተብሎ በGGGI ፕሮጀክት 100W ሶላር ለ22 አባወራዎች ተሰራጭቶ ነበር።

ከወሰዱት መኻከል አንዲት ምስክን እናት ብቻዋ ምትኖር እና በሰዉ እገዛ የምትኖር ይህች እናት በፕሮግራሙ ከተሰረጨው ሶላር እንደ አንድ አባወራ ከነመሣሪያዎች ደርሷቸዋል።

ነገር ግን ይህች እናት ደስታዋን ሳትጨርስ ከምሽቱ 8:00ሳዓት አከባብ ጦር እና የመሳሰሉትን መሳርያዎችን በመያዝ ጨለማን ተገን በማድረግ ሶላር ከኔ ምጣዱ ጭምር ሰርቀው ይጠፋሉ።

በዚህም ወንጄል ስሜታዊ የሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ብርቱ ክትትል ፣ ጥቆማና አውጫጭን ተጠርጣሪዎችን ከነተሰረቁ ዕቃዎች እጅ ከፍንጅ መያዝ ተችሏል።

የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

የ8 ዓመት ህጻን ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በ 20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።(ወዜና ፤ ግንቦት 27/2017ዓ.ም )በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ቀበሌ የአስገድዶ መድፈር ...
04/06/2025

የ8 ዓመት ህጻን ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በ 20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።

(ወዜና ፤ ግንቦት 27/2017ዓ.ም )

በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ቀበሌ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በፈጸመው ግለሰብ ላይ 20 ዓመት ፅኑ እስራት መወሰኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ።

ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማ የተባለ ግለሰብ በወላይታ ሶዶ ከተማ የጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ 12፡30 አካባቢ የግል ተበዳይ የ8 ዓመት ህፃንን ጁስ እና ኮሾሮ ገዝቶ በማታለል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙን የሶዶ ከተማ ዐቃቤ ህግ በማስረጃ ማረጋገጡን የሶዶ ከተማ ፖሊስ ታክቲክ ምርመራ ሀላፊ ኢ/ር ታመነች ባሳ ገልጸዋል፡፡

ግለሰቡ ከዚህ በፊት በነፍስ ግድያ ወንጀል ተባባሪ ሆኖ 14 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበትና የእስር ጊዜውን ሳይጨርስ በምህረት የወጣ መሆኑን ማስረጃው ያመላክታል፡፡

የወላይታ ሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት አቶ ኤፍሬም ጪማ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

የሴቶች ጉዳት ከፍተኛ የሀገር ጫና ነው ያሉት የሶዶ ከተማ ፖሊስ ሰቶችና ህፃናት ጉዳይ ምርመራ ቡድን ሃላፊ ዋና ሳጂን ታምራት ነካ በዚህ ሁኔታ የሚፈጠሩ ችግሮችን ከስር መሠረታቸው ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ በበኩላቸው በወንጀል ድርጊቶች ላይ በሚሰማሩ አካላት ላይ የሚደረግ ጠንካራ ክትትል እና ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲያገኙ ለማድረግ ከፍትህ ተቋማት ጋር የሚደረግ ጥምረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

የኢትዮጵያ አይዶል በወላይታ ሶዶ መካሄድ ጀመረከወላይታ ሶዶ እና አካባቢው የመጡ ባለተሰጥኦዎች ውድድራቸውን እያደረጉ ነው። ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 26/2017(ወዜአ) የበርካታ የሙዚቃ ባለሙያ...
03/06/2025

የኢትዮጵያ አይዶል በወላይታ ሶዶ መካሄድ ጀመረ

ከወላይታ ሶዶ እና አካባቢው የመጡ ባለተሰጥኦዎች ውድድራቸውን እያደረጉ ነው።

ወላይታ ሶዶ፣ ግንቦት 26/2017(ወዜአ)

የበርካታ የሙዚቃ ባለሙያዎች መፍለቂያ በሆነቸው የወላይታ ሶዶ ከተማ ድምፃዊ ተስፋዬ ታዬ እና ሳምራዊት አዘነ የኢትዮጵያ አይዶል ዳኛ በመሆን ተሰይመዋል።

በወላይታ ሙዚቃ ውስጥ ከፍ ያለ ስፍራ ያላቸው አለማዬሁ ዛሳ ደግሞ በተጋባዥ ዳኝነት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ አይዶል ጉዞ ጥበብን ፍለጋ በወላይታ ሶዶ በድምቀት እየተካሄደ ነው።

የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና

Address

Wolaita
S**o
WOLAITA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የወላይታ ዜና አገልግሎት ወዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share