01/06/2025
የ19 አመቷ የሚስ ወርልድ ውድድርን ከዓለም 2ኛ በመሆን ያጠናቀቀችው ሃሴት ማናት?
በህንድ እየተከናወነ ያለው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር የ109 አገራት ቆነጃጅት የተሳተፉ ሲሆን ‹‹ሚስ ወርልድ›› የሚል መጠሪያ በማግኘት የዘንድሮውን ዘውድ የጫነችው ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሱቻታ ሆናለች፡፡
እሷን ተከትላ ኢትዮጵያን የወከለችውና በውድድሩ ላይ ‹‹ሚስ ኢትዮጵያ›› ተብላ ስትጠራ የነበረችው ሀሴት ደረጄ ከአለም 2ተኛ ትሁን እንጂ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ተመርጣለች።
ሃሴት ደረጄ እድሜዋ 19 ሲሆን በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ናት።
ከአሽከርካሪ አባቷ እና ከፖሊስ እናቷ በአዲስ አበባ የተወለደችው ሃሴት የሚስ ወርልድ ውድድርን ከዓለም 2ተኛ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን አጠናቃለች።