Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ

Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ Dawuro Zone Health Department supports zonal health system both in preventive and curative approaches.

It is known that prevention is less prodigal than treatment that is 1 dollar to 34 dollars.

የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ለሁሉም ህፃናት ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት  ተገለፀሀዋሳ: ሕዳር 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ለ...
06/12/2025

የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ለሁሉም ህፃናት ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት ተገለፀ

ሀዋሳ: ሕዳር 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ለሁሉም ህፃናት ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ።

‎መምሪያው 4ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ላይ ለጤና ባለሙያዎች የአስልጣኞች ስልጠና በዞኑ ዋካ ከተማ ሰጥቷል ።

‎በስልጠናው ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ያዕቆብ ሌንጮ የፖሊዮ ክትባት ለሁሉም ህፃናት ማለትም ከአምስት አመት በታች የሚገኙ ህፃናት ቤት ለቤት በመጎበኝት መሰጠት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል ።

‎ስለሆነም በስልጠናው የተገኙ ባለሙያዎች ስልጠናውን በአትኩሮት ተከታትለው ለሌሎችም ሙያተኞች በተገቢ ሁኔታ እንደሚያሰለጥኑ እምነታቸው እንደሆነ ተናግረዋ ።

‎ስልጠናው የፖሊዮ ክትባት የተከተቡትም ያልተከተቡት ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች ለሆኑ ህፃናት የመለየትና የመከታተል አገሎትም ተያይዞ እንደሚሰጥ የመምሪያው ሃላፊ ተናግረዋል ።

‎ስልጠናውን ከሰጡት አስልጣኞች መካከል በጤና መምሪያው ድንገተኛ አደጋ ቅኝት ምላሽ ዋና ስራ አስተባባሪ አቶ ወልዴ በካሎም በበኩላቸው በዞኑ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ቤት ለቤት መሰጠቱ በርካታ ጥቅም መኖሩን ተናግረው ለዚህም ተግባር ሙያተኞቹ በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው ሌሎቹን እንዲያሰለጥኑ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል ።

‎ስልጠናው ከፓሊዮ ክትባት በተጨማሪ የዞረ እግር፣ የከንፈርና የላንቃ መሰንጠቅ፣ የምግብ እጥረት ልየታ ፣ የአዲሱ ማርበርግ ቫይረስ ልየታና ህክምና አስጣጥ ሁኔታና ተያያዥ ጉዳዮች ለአሰልጣኞች በበቂ ሁኔታ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል ።

‎ከሰልጣኞቹ መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከመስጠታችን በፊት ስልጠና መስጠቱ የበለጠ ግንዛቤ እንደሚጨምር ተነጋግረዋል ።

‎የፖሊዮ ክትባትን ጨምሮ በሌሎችም በሽታዎች ዙሪያ ያገኘነውን ግንዛቤ ሌሎች ሙያተኞች በተገቢው ሁኔታ በመሰልጠን ወደ ተግባሩ እንደሚገቡም ተናግረዋል ።

‎ስልጠናው ከወረዳውና ከከተማ አስተዳደር የሚመለከታቸውን የዘርፉ ሙያተኞች ለተከታታይ ለሁለት ቀናት የተሰጠ ሲሆን፥ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከአምስት አመት በታች ለሚገኙ ህፃናት ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ/ም ድረስ ቤት ለቤት በሚደረግ ጎብኝት እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል ።

‎ዘገባው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ነው።

አገር አቀፍ የወባ ጠቋሚ ጥናት የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለዉ ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነዉ____________አገር አቀፍ የወባ ጠቋሚ ጥናት ለሚያካሄዱ መረጃ ሰብሳቢዎችና አስተባባሪዎች...
01/12/2025

አገር አቀፍ የወባ ጠቋሚ ጥናት የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለዉ ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነዉ
____________

አገር አቀፍ የወባ ጠቋሚ ጥናት ለሚያካሄዱ መረጃ ሰብሳቢዎችና አስተባባሪዎች ስለጠና እና የስራ መመሪያ ተሰጥቷል።

በስልጠና ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ወባን ለማስወገድ እየተከናወኑ ያለውን ጥረት ለማሻሻል በጥናት ለይቶ በስራ ላይ ያለውን የወባ ስትራቴጂ ዕቅድ ለማሻሻል፤ ሳይንሳዊ መረጃ ለማመንጨት እና የመከላከልና የመቆጣጠር ስራዎችን ለማጠናከር አገር አቀፍ የወባ ጠቋሚ ጥናት ማካሄድ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

በወባ ጠቋሚ ጥናት የወባ መከላከያ ግብዓቶች ተደራሽነትና አጠቃቀም፤ የህክምና አገልግሎት፤ የእናቶችና ህፃናት የወባ ስርጭት እንዲሁም ሌሎችም የጥናቱ ማጠንጠኛ ተግባራት መሆናቸውን የተናገሩት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ሲሆኑ በቂና ጥራት ያለው መረጃ እንዲሰበሰብ ማህበረሰቡ ለመረጃ ሰብሳቢዎችና አስተባባሪዎች አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሁሉም ክልሎች በወባ ጠቋሚ ጥናት በጤና ተቋማት የማይገኙ መረጃዎችን ቤት ለቤት በመዘዋወር በተመረጡ 560 ጣቢያዎች ከ14,000 በላይ የሚሆኑ አባወራዎች የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለወባ ጠቋሚ ጥናት መረጃ ሰብሳቢዎችና አስተባባሪዎች የሰባት ቀን ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ እየሰጠ ነው፡፡
ዘገባው የጤና ሚኒሰትር ነው።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተግባርን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሁለም በባለቤትነት ሊሰራ እንደምገባ ተጠቆመየዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ እና የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ሚዛ...
30/11/2025

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተግባርን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሁለም በባለቤትነት ሊሰራ እንደምገባ ተጠቆመ

የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ እና የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ሚዛን አማን ቅርጫፍ ጽ/ቤት የ2017 አፈፃፀም እና የ2018 ዕቅድ ዙሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን የንቅናቄ መድረክ በታርጫ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የዳውሮ ዞን ዋና አሰተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበዩሁ በበኩላቸው በጤናው ዘርፍ የማህበረሰብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከላይ ጀምሮ እሰከ ታችኛው መዋቅር በባለቤትነትና በቁርጠኝነት ልሠራ ይገባል ብለዋል።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ክፍያ መክፈል ያልቻሉ የማህበረሰብ ክፍሎችን በመደገፍ የማህበረሰብ ጤና ከማረጋገጥ አንፃር ሁሉም የበኩሉን ልወጣ እንደምገባ አቶ ዳዊት ገልፀዋል።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት በታቀደው ልክ ለማሳካት ቅንጅታዊ የአመራር ስረዓት መዘረጋት ይገባል ያሉት አሰተዳዳሪው ድጋፍ ክትትልም ልጠናከር እንደምገባ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ሚዛን አማን ቅርጫፍ ጽ/ቤት ዋና ሥራ ስራአስኪያጅ አቶ ታከለ ታደሰ በ2017 ዓ/ም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያደረጉት አስተዋጽኦ የተሻለ ነው በማለት የ2018 በጀት ዓመት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል።

የጤናው ዘርፍ ሰራተኞች በወረደው መመሪያ መሰረት የሚጠበቅባቸውን መረጃ በማቅረብ በማህበራዊ ጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆኑም አሳስበዋል።

የዳውሮ ዞን ጤና መምርያ ኃላፊ አቶ ያዕቆብ ለንጫ በመደበኛ ባልሆነ ክፍለ ኢኮኖሚ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የማህበረሰብ አቀፍ ኣባልነት መዋጮ በመክፈል የማዐጤመ ደብተር በመያዝ ግደታቸው እንድወጡ አሳስበዋል።

ማዐጤመ የማህበረሰብ ጤና ከመጠበቅ አንፃር ጉል ሚና እንዳለው በመጠቆም ባለድርሻ አካላት በታቀዴው ልክ ማሳካት የሁሉም ማህበረሰብ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም በ2017 በጀት ዓ/ም በማዐጤመ አፈፃፃም የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና ባለድርሻ አካላት ዕውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቷል።
ዘገባው የዳውሮ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

📌የሀዘን መግለጫ፨፨፨፨፨፧፨፨፨፨፨፨የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ባለደረባ የነበሩት እና ከአመታት በፊት በእድሜ ብቁነት ጡረታ የወጡት አንጋፋ  አቶ ነጋሽ ኃይሌ ጫሬ ባደረባቸው የጤና እክል በታር...
30/11/2025

📌የሀዘን መግለጫ
፨፨፨፨፨፧፨፨፨፨፨፨
የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ባለደረባ የነበሩት እና ከአመታት በፊት በእድሜ ብቁነት ጡረታ የወጡት አንጋፋ አቶ ነጋሽ ኃይሌ ጫሬ ባደረባቸው የጤና እክል በታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው እለት ህዳር 20/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም በማረፋቸው ጤና መምሪያው የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።
አቶ ነጋሽ ኃይሌ በጤናው ዘርፍ በየዓመቱ ለሚመዘገበው አመርቂ ውጤት ካስመዘገቡ ጤና ባለሙያዎችና አመራሮች መካከል አንዱ እና ለሥራ ታታሪ ሰው ወዳድ በተሰማሩበት ቦታ ሁሉ ብቁና ጠንካራ ለማንም የማይበገር ጀግና ባለሙያና አመራር ነበሩ።
ለመላው ቤተሰባቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለቀድሞ ለሥራ ባልደረቦቻቸው በሙሉ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እንመኛለን።

የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍትሐዊነት ላይ ትኩረት ተሰጥተዉ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፤ህዳር 16/2018 ዓ.ም በታርጫ ዙሪያ ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ምጣኔ ለማሳድግ...
25/11/2025

የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍትሐዊነት ላይ ትኩረት ተሰጥተዉ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፤
ህዳር 16/2018 ዓ.ም በታርጫ ዙሪያ ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ምጣኔ ለማሳድግ ቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሰራ መሆኑን የታርጫ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ በቀለ ገልጾል፡፡

ኃላፊዉ አክለዉም ከወረዳ ጤና ጽ/ቤት የተደራጀ ግብረ ኃይል በአባ እና በዋራ ጤና ጣቢያዎችና በስሩ በሚገኙ ጤና ኬላዎች የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የገጠር ጤና ትራንስፎርሜሽን ተግባራት አፈፃፀም መነሻ መረጃ የማጥራትና ማረጋገጥ(Verification) በህፃናት ጤና አገልግሎት ዘርፍ በዕድሚያቸዉ ዘመን ያልተከተቡና ክትባት ጀምሮ ያቋረጡ ህፃናት ልየታ በማድረግ እንድከተቡ ማድረግ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን claim ኦዲት እንድሁም የቅድመ ዝግጅት ሥራ እንደተሰራ መሆኑን አብራረቷል፡፡

በወረዳዉ የተደራጁ ቡድን ባለፉት ሁለት ሳምንት በተደረገዉ መረጃ ማጥራትና ማረጋገጥ /Verification/ ግብረ መልስ ሪፖርት ቀርበው ተገምግሟል። የግብረ መልስ ሪፖርት እንደሚያሳየዉ በገጠር ጤና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃፀም መነሻ አባ ጤና ጣቢያ self-Assessment average score 89% ስሆን፤ የወረዳ ቬሪፊኬሽን ቡድን ባደረገዉ ማረጋገጫ 55% ዋራ ጤና ጣቢያ self-Assessment average score 91.2 ስሆን፤ የወረዳ ቬሪፊኬሽን ቡድን ባደረገዉ ማረጋገጫ 63.4% የህፃናት ክትባት አገልግሎት ጋር በተያያዜ ዜሮ ዶዝ ክትባት ለማስከተብ ዕቅድ 1430 እስካሁን የተከተቡት 832 ሽፋን 58.1 ክትባት ጀምሮ ያቋረጡ ህፃናት ለማስከተብ ዕቅድ 2808 ስሆን እስካሁን የተከተቡት 2366 ሽፋን 84.2 መሆኑን ቬሪፊኬሽን ቡድን ሰብሳቢና በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ቡድን መሪ ገልፃል፡፡

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ከማፍራት አኳያ ዝርዝር ተጋጅተዉ ለሁሉም ቀበሌዎችና ጤና ጣቢያዎች የተሰጠ ስሆን እስካሁን በቁጥር 54 አባላት ተመዝግበዉ የአባልነት መዋጮ ገንዘብ 69,848 ብር ገቢ ማድረጋቸዉ በግብረ መልስ መድረክ ተገምግሟል፡፡

በስተመጨረሻ እንደወረዳ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ተግባራትን በማስቀል መሻሻል ያለባቸዉና በዚህ ዙር የታዩ ጉድለቶች ከሁሉም በላይ የመረጃ ጥራትና ሙሉነት እንድሁም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ምጣኔ ላይ ቀጣይ ጊዜ ትኩረት እንደሚሰራና ለተግባራዊነቱ የዞን ጤና መምሪያ ማናጅመንትና አመራሮች እንድሁም የወረዳ አስፈፃሚ አካላትና የሚመለከታቸዉ አካላት ድጋፍ እንደሚያሰፈልግ የጽ/ቤቱ ኃላፊና ማናጅመንት አባላት በአፅዕኖት አሳስቧሉ፡፡

በግብረ መልስ መድረክ ላይ የተገኙት የዞን ጤና መምሪያ ድጋፊ ባለሙያ አቶ ስዩም ከበደ የወረዳጤና ጽ/ቤት ኃላፊና ማናጅመንት አባላትን ጨምሮ ሁሉም ባለሙያዎች ተገኝቷል፡፡
ዘገባዉ የዳዉሮ ዞን ጤና መምሪያ ነዉ፡፡

ማስታወቂያ ለአዲስ ተመራቂ እና ላልተቀጠሩ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ..!!
21/11/2025

ማስታወቂያ
ለአዲስ ተመራቂ እና ላልተቀጠሩ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ..!!

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታህዳር 11/ 2018 በተጨማሪም ሶስቱ በህክምና ላይ ያሉ ታማሚዎች ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲ...
21/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታ
ህዳር 11/ 2018

በተጨማሪም ሶስቱ በህክምና ላይ ያሉ ታማሚዎች ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።

Marburg Virus Disease Daily Update
Ethiopia
November 20/ 2025



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

የገጠር ትራንስፎርሜሽን እንዲሳካ የጤናው ዘርፍ አመራር በቁርጠኝነት መስራት አለበት ሲሉ የደ/ም/ኢ/ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም ገልጸዋል።Dawuro Zone health depar...
21/11/2025

የገጠር ትራንስፎርሜሽን እንዲሳካ የጤናው ዘርፍ አመራር በቁርጠኝነት መስራት አለበት ሲሉ የደ/ም/ኢ/ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም ገልጸዋል።

Dawuro Zone health department, Regional Health Bureau

16/11/2025
በወረዳው አስከፊው የወባ በሽታ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።********በዳውሮ ዞን ዲሳ ወረዳ የወባ ጫና ባለባቸው  በ12ቱ ቀበሌ ላይ የወባ በሽታ ለመቆጣጠር ቤት ለቤት ...
14/11/2025

በወረዳው አስከፊው የወባ በሽታ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
********
በዳውሮ ዞን ዲሳ ወረዳ የወባ ጫና ባለባቸው በ12ቱ ቀበሌ ላይ የወባ በሽታ ለመቆጣጠር ቤት ለቤት የኬሚካል ርጭት እየተደረገ እንደሚገኘ የወረዳው ጤ/ጥ/ጽ/ቤት አስታወቋል።

የወባ በሽታ ሥርጭት ለመከላከል ቤት ለቤት የሚካሄደው የወባ መከላከያ ኬሚካል ርጭት በተጨማሪ ሌሎች የወባ መከላከያ ዘዴዎች በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የወረዳው ጤና ጥ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንድነት አየለ ገልጿል ።

የወባ በሽታን ለመከላከል አከባቢው የአልጋ አጎበርን በአግባቡ መጠቀም እና የቤት ውስጥ የፀረ ወባ ኬሚካል ርጭት ማካሄድ እንደሆኑ ገልጸው ርጭቱም በወረዳው ውስጥ የወባ ጫና ባለባቸው 12ቱ ቀበሌዎች ውስጥ ያለው ህዝብ ብዛት በቁጥር 45062 አባወራ ብዛት 9195 ርጭት የሚደረጉ ቤቶች ብዛት 13793 ተደራሽ እንደሚደረግም ጠቁሟል።

ኃላፊው አያይዘውም የፈደራል ጤና ሚኒስቴር፣ የክልሉ መንግስት፣የክልሉ ጤና ቢሮ፣ዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ፣የዲሣ ወረዳ መንግስት ለወረዳችን ትኩረት በመስጠት ከ22 ሚለዮን ብር በላይ በጀት መድበው ኬሚካሉን ገዝቶው በሰጡት ትልቅ እገዛ እየተሰራ መሆኑን ተናግረው የወረዳው መንግስት ርጭት ለማካሄድ በጀት መድቦ እያሰራ መሆኑንም ጭምር ገልጸዋል ።

የወረዳው በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ግዛው ጠናዬ እንደገለፁት ማህበረሰቡ በኬሚካል የተርጩ ቤቶች እስከ 6 ወር ድረስ የቤት ግርግዳ ቀለም ከመቀባትም ሆነ ወረቀት ከመለጠፍ እንዲቆጠቡ አሳስበው፤ የቀበሌ መንግስት፣ የቀበሌ ህብረተሰብ፣ ጤና ኤክስቴንሽን እና ጤና ባለሙያዎች ወቅቱ የወባ ወረርሽኝ የሚነሳበት ግዜ ስለሆነ የመከላከሉ ሥራ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ መስራት እንዳለባቸው የዲሳ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ዘግቧል።

14/11/2025

.World Health Organization (WHO) is working closely with Ministry of Health,Ethiopia , the Ethiopia Public Health Institute and regional health authorities as part of the rapid response to a suspected outbreak of a viral haemorrhagic fever (VHF) in the Southern Ethiopian Region.

8 people, including health workers, have reportedly been infected.

WHO has deployed experts to the affected towns, along with medicines and other materials to support care for people in need, and personal protective equipment for health workers.

WHO will also be supporting contact tracing in affected communities. Samples have been sent for testing. Further details are expected soon.

I have released US$300,000 from the WHO Contingency Fund for Emergencies to provide immediate support.

WHO’s offices in Ethiopia and South Sudan are collaborating closely to prevent potential cross-border transmission. WHO is ready to scale up support, as and when needed.

I commend Ethiopian health authorities for their timely sharing of information and quick response and offer WHO’s full support.

https://www.afro.who.int/news/ethiopia-reports-suspected-viral-haemorrhagic-fever-outbreak

Address

Tarch'a Sodo

Telephone

+251912856886

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ:

Share