Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ

Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ Dawuro Zone Health Department supports zonal health system both in preventive and curative approaches.

It is known that prevention is less prodigal than treatment that is 1 dollar to 34 dollars.

15/08/2025

በታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል ከሚከሰቱ የሞት ሁኔቶች የእናቶች ሞት በልዩነት በሆስፒታሉ የእናቶች ሞት ቅኝት እና ምላሽ ቡድን( MDSR team) በጥልቀት እንደምገመገግም የሆስፒታሉ ሜድካል ዳይሬክተር ዶ/ር አስራት ጌርሾንገልጸዋል። በሆስፒታሉ በ2017 በጀት ዓመት 2200 እናቶች የወሊድ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን በበጀት ዓመቱ እሰከ ስኔ 30/ 2017 ድረስ ምንም የእናቶች ሞት አልተመዘገበም ነበር ። 2017 በጀት ዓ/ም ከወለዱ እናቶች 532 በኦፕራሲዮን የወለዱ ስሆን፡ 16 እናቶች ማህጸን በምጥ ምክንያት መፈንዳት (uterine rupture) ምክንያት ዉስብስብ ቀዶ ህክምና ተደርጎላቸዋል ። በተጨማሪም 187 እናቶች በወሊድ ጊዜ ደም አስፈልጓቸው የተሰጣቸው ስሆን፡ 68 እናቶች የሞት አፋፍ ላይ(maternal near miss) እና 48 እናቶች ከወልድ በኋላ ማያቋርጥ መድማት (PPH) ኖሯቸዉ ከፍተኛ ህክምና ተደርጎላቸው መትረፋቸውን የክፍሉ አስተባባሪ ዶ/ር ወንድማገኘሁ ሲሳይ ገልጸዋል። ከወሊድ ጋር በተያያዘ 8 እናቶች ወደ ከፍተኛ ህክምና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ሪፈር ተደርገዋል።
የተለያዩ የማህጸን ችግሮች ያሉባቸው 2336 እናቶች ተኝተዉ የታከሙ ስሆን ከእነዚህ ዉስጥ 386 እናቶች ከፍተኛ የማህጸን ቄዶ ህክምና እና ለ100 እናቶች የነጻ የማህጸን ዉልቃት ቄዶ ህክምና መደረጉን ዶ/ር ወንድማገኝ ጨምረው ገልጸዋል ። በሆስፒታሉ በቅርብ ወራት ተጨማር የማህፀን እና ፅንስ ስፐሻሊስት ሀኪም የተቀጠረ ስሆን በእናቶች ክፍል በአሁኑ ሰዓት 1 subspecialist ፡1 specialist ፡1 የድንገተኛ ቄዶ ጥገና ፡ 28 አዋላጅ ነርስ ፡ 5 ስክረብ ነርስ ፡ 3 ጠቅላላ ሀክሞች፡5 አነስቴዥያ ባለሙያዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የሆስፒታሉ ሰራ አስክያጅ አቶ ያዕቆብ ሌንጫ ገልጸዋል ። በክልሉ የእናቶች ህክምና አገልግሎት በሰብስፔሻሊት የምሰጥበት ብቸኛ ሆስፒታል መሆኑ ይታወቃል ። በሆስፒታሉ በቅርብ ቀን የተከሰተውን የአንዲት እናት ሞት የሆስፒታሉ እናቶች ሞት ቅኝት እና ምላሽ ቡድን ከእለቱ ተረኛ ባለሙያዎች ጋር ጥልቅ ውይይት እና ግምገማ ማድረጋቸውን ዶ/ር ወንድማገኘሁ ጨምረው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታ የእናት ሞት እንዳይከሰት በሆስፒታሉ ባለሞያዎች አቅም መደረግ ያለበትን ሁሉ ለማድረግ መስማማታቸውን ገልጸዋል። አንዳንድ ቡድኖች የምስክን እናቶች ሞት ለፖለቲካ መጠቀሚያ በማድረግ እና የተቋሙን እና የባለሞያዎችን ስም ለማጠልሸት የምሄዱት አካሄድ መሬት ላይ ያለዉን እውነት የማይገለጽ መሆኑን ዳይረክተሩ ዶ/ር አስራት ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ እንደዚህ አይነት ነገር ስከሰት መጠየቁ በሆስፒታሉ እና ባለሙያዎች ያላዉን አመነታ እና ባለቤትነት የሚያሳይ ስለሆነ በቅንነት እንደምቀበሉት ገልፀዋል። በሆስፒታሉ ለወሊድ የሚመጡ እናቶች ሁሉም በሚባል ደረጃ በስፔሻሊሴት ሀኪሞች እንደምታዩ እና ባለፈዉ ዓመት የእናቶች ህክምና ቡድኑ በሳምንት 2 ቀን በዓመት 104 ቀን በየቀኑ የተሰሩ ስራዎች እና ክስተቶችእየገመገሙ መምጣታቸውን አሳውቀዋል ። ሆስፒታሉ ከ12 ወረዳዎች እና አጎራባች ዞኖች የሚመጡ ዉስብስብ የጤና ችግር ያለባቸውን እናቶች ተቀብሎ የምያስተናግድ መሆኑን በመገንዘብ የተለያዩ አካላት ድጋፍ እንድያቀርቡ ጥሪ አቅርቧል። በተለይ በዝናብ ወቅት አብዛኛው የወረዳ መንገዶች የመዘጋጋት ሁኔታ እናቶች ዘግይተው ደክመዉ እንድደርሱ ምክንያት እንደሆነ ጠቅሰው የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ደም በመለገስ ጭምር ህይወት የማዳን ስራ እየሰሩ መሆኑ ይታወቃል።
(ታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል)

በዳውሮ የታርጫ ከተማ ጤና ጣቢያ ሠራተኛ የነበረች ወጣት በልጅነቷ ተቀጨች😭
11/08/2025

በዳውሮ የታርጫ ከተማ ጤና ጣቢያ ሠራተኛ የነበረች ወጣት በልጅነቷ ተቀጨች😭

በዛሬው ዕለት የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት እና ኤችአይቪ መከ/መቆ/ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ። በውይይቱም ከወረዳና ከተማ አስ...
03/08/2025

በዛሬው ዕለት የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት እና ኤችአይቪ መከ/መቆ/ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ።

በውይይቱም ከወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ሥራ ሂደት አስተባባሪዎች፣ ዘርፈብዙ ሥራ ሂደት አስተባባሪዎችና የጤና ኤክስቴንሽን እና የመጀመሪያ ደረጃ አሃድ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።

በሁለቱም ስራ ሂደቶች የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ቀጣይ መከናወን ባለባቸው ዕቅዶች ዙሪያም ሥራዎችን በተቀናጀ መንገድ መሥራት እንደሚያስፈልግ ከመግባባትም ተደርሷል።

ለዝህም ከወባ ንቅናቄ ጋር እንዲቀናጁ ተደርገው እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ድረስ እየተመራ ያለውን ተግባር አውሰው ባልተቋረጠ መንገድ ይህም እንዲመራ ከመድረክ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በጣም የሚያሳዝን ክስተት ነው!
26/07/2025

በጣም የሚያሳዝን ክስተት ነው!

25/07/2025
25/07/2025
23/07/2025

Big shout out to my newest top fans! ብዙአየሁ ዘርሁን

 #የሀዘን  #መግለጫ በዳውሮ ዞን የገና ወረዳ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ሥራ ሂደት ቡድን መሪ ወጣት ታምራት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ከፍተኛ ሀዘን የተሰማን ሲሆን ለቤተሰቦቹና ለጤ...
22/07/2025

#የሀዘን #መግለጫ
በዳውሮ ዞን የገና ወረዳ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ሥራ ሂደት ቡድን መሪ ወጣት ታምራት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ከፍተኛ ሀዘን የተሰማን ሲሆን ለቤተሰቦቹና ለጤናው መዋቅር መጽናናትን እንመኛለን።

Address

Tarch'a Sodo

Telephone

+251912856886

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ:

Share