Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ

Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ Dawuro Zone Health Department supports zonal health system both in preventive and curative approaches.

It is known that prevention is less prodigal than treatment that is 1 dollar to 34 dollars.

በደቡብ ምዕራብ ክልል ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዘርፍ የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም የዳውሮ ዞን በ3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ግምገማው ተጠናቋል።ይህም ለቀጣይ ሥራ የቀሰቀሰን በመሆኑ...
07/10/2025

በደቡብ ምዕራብ ክልል ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዘርፍ የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም የዳውሮ ዞን በ3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ግምገማው ተጠናቋል።ይህም ለቀጣይ ሥራ የቀሰቀሰን በመሆኑ የሁሉም ድጋፍ ያስፈልገናል ።ለሁሉም የባለድርሻ አካላት ምሥጋና አለኝ።ቀጣይ ከፍ ላለ ደረጃ በጋራ እንሠራለን ።

https://www.facebook.com/100044559754002/posts/1385489416279704/?app=fbl
01/10/2025

https://www.facebook.com/100044559754002/posts/1385489416279704/?app=fbl

Congratulations, , for achieving Regulatory Maturity Level 3 in the World Health Organization (WHO) global classification of national regulatory authorities.

Ethiopia now joins Egypt, Ghana, Nigeria, South Africa, Tanzania, Zimbabwe, Senegal and Rwanda in reaching Maturity Level 3 on the continent.

This progress is making Africa closer to improving local production and access to safer, quality medicines and medical products.

27/09/2025
26/09/2025
24/09/2025

የጤና ሚኒስቴር እስከ መስከረም 30/2018 ዓም የታደሰ የሙያ ፈቃድ ያልያዙ እና ያላወጡ የጤና ባለሙያዎች አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ አሳውቋል።

የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድን በሚመለከት በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ ተፈርሞ በ 30/12/2017 ዓም ለሁሉም ክልሎች የተላከው ደብዳቤ " ሁሉም ክልሎች እስከ መስከረም 30/2018 ዓም ድረስ የንቅናቄ ስራ በመስራት ሁሉም ባለሙያ የሙያ ፍቃድ ይዞ እንዲሰራ እንዲደረግ አሳስባለሁ " ይላል።

" በመመሪያው መሰረት የጤና አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም ባለሙያዎች የታደስ የሙያ ፈቃድ እንዲኖራቸው ይጠበቃል " ያለው የጤና ሚኒስቴር ይህንንም ተከታትሎ ማስፈጸም በጤና ሚኒስቴር የጤናና ጤና ነክ ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ መሆኑን ይገልጻል።

በ2017 በጀት ዓመት የጤና ሚኒስቴር ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት መሰረት የሙያ ፈቃድ ሳይኖራቸዉ እንዲሁም የአገልግሎት ጊዜው ባለፈበት የሙያ ፈቃድ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ባለሙያዎችን መኖራቸዉን ማረጋገጡን ገልጿል።

በዚህ መሰረት " ሁሉም የጤና ባለሙያዎች በሙያቸው ለመስራት የታደሰ የሙያ ፈቃድ መያዝ እንደሚያስፈልጋቸው ታውቆ በክልላችሁ ስር በሚገኙ ጤና ተቋማት ላይ የሚሰሩ ጤና ባለሙያዎች እስከ መስከረም 30/2018 ዓ.ም ብቻ የሙያ ፈቃድ እንዲያወጡ " ሲል ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።

ከመስከረም 30/2018 ዓ.ም በኋላ ግን "No license,No practice" በሚል መሪ ቃል የሙያ ፈቃድ የሌላቸው ባለሙያዎች በሙያቸው መስራት እንደማይችሉ አሳውቋል።

የሙያ ፈቃድ ለማውጣት እና ለማሳደስ የተሰጠው ጊዜ እስከሚያልቅ ክልሎች አስፈላጊው የንቅናቄ ስራ በመስራት ሁሉም ባለሙያ የሙያ ፍቃድ ይዞ እንዲሰራ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ መሰጠቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከደብዳቤው ተመልክቷል።

በእዚህም መሰረት የአማራ ክልል ጤና ቢሮ በትላንትናው ዕለት ለሁሉም ዞን ጤና ቢሮዎች እና ተጠሪ ተቋማት ሰርኩላሩ ተግባራዊ እንዲሆን አሳስቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


18/09/2025
16/09/2025
በህገወጥ ተግባራት በመሰማራት ለጤና ጠንቅ የሆኑ ምግብና መጠጥ ሲያቀርቡ የነበሩ ግለሰቦች እርምጃ ተወስዶባቸዋልየክልሉ ጤና ቢሮ ጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን...
10/09/2025

በህገወጥ ተግባራት በመሰማራት ለጤና ጠንቅ የሆኑ ምግብና መጠጥ ሲያቀርቡ የነበሩ ግለሰቦች እርምጃ ተወስዶባቸዋል

የክልሉ ጤና ቢሮ ጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር በተደረገ የበዓል ወቅት ዳሰሳ በርካታ ህገወጥ ምግብና የምግብ ምርት ውጤቶች ተገኝተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የምግብና መድሃኒት ተቆጣጣሪ ባለሙያ አቶ ማርቆስ ፎላ እንደገለጸፁት፤ዳሰሳ ተደርጎባቸው ለጤና ጠንቅ የሆኑ ምግብና መጠጦች ሲያቀርቡ የቆዩ 59 ተቋማት ተገኝተዋል።

በዚህም 38ቱ በታርጫ ከተማ ቀሪው በገሳ ከተማ ጨው፣በርበሬና የታሸጉ የህጻናት ምግቦችን ጨምሮ በርካታ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ባዕድ ነገር ቀላቅለው ሲሸጡ መቆየታቸው ነው የተገለጸው።

ባጃጅ ወይም ፋጋና ተብሎ ሚጠራው መጠጥ ከተለያዩ ባዕድ ነገሮች ጋር ተቀላቅሎ ህብረተሰቡ እየተበከለ በመሆኑ ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል ሲሉ የመምሪያው በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሮክቶሬት አቶ ስዩም ከበደ ተናግረዋል።

ንግድና ኢንዱስትሪ ተቋም ከጤና ሴክተርና ከፍትህ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የማይገቡ ምግብና መጠጦች እንዲወገዱ መስራት ይጠበቅበታልም ብለዋል።

እኚህን ተግባራት የሚያከናውኑ ግለሰቦች ወይም ሆቴሎች በፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ካልተማሩ ከፍ ያለ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም የዞኑ ጤና መምሪያ ጤናና ጤና ነክ አ/ግ/ጥ/ቁ/ ዳይሮክቶሬት አቶ ፀጋዬ ፊሊሞን ገልጸዋል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አስራት ቸርነት
ተከታትሎ የማጋለጡን ተግባር በቅንጅት ልናስቀጥል ይገባል ብለዋል።

የሚዲያ ተቋማትም መሰል ተግባራትን ተከታትሎ የማጋለጥ ብሎም ህብረተሰቡን የማስተማር ኃላፊነት እንደሚጣልባቸው እንዲሁም ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑ ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ከ170 ሺ ብር በላይ የሚተመን ህገወጥ ምግብና መጠጥ ተወርሶ ተወግዷል።

በብዙፍሬ በዛብህ

ተከታተሉን

‎በፌስቡክ
https://facebook.com/

‎በዩቲዩብ
https://youtube.com/

‎በቲክቶክ
https://tiktok.com/

‎በቴሌግራም

https://t.me.com/

Address

Tarch'a Sodo

Telephone

+251912856886

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dawuro Zone Health Department የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ:

Share