13/10/2025
የስልጤ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት የወረዳና ከተማ አስተዳደሮችን የ2018 የሩብ ዓመት አፈጻጸም ገመገመ።
ጥቅምት 3/2018 :-የስልጤ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በተያዘው 2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራት እቅድ ክንውን በመገምገም በቀጣይ ተግባራት ላይ የጋራ አቅጣጫ አስቀምጧል።
በመድረኩ ላይ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤቶች ባለፉት ሶስት ወራት ያከናወኗቸውን ተግባራት እቅድ ክንውን አቅርበው ውይይት ተደርጓል።
በቀረቡ ሪፖርቶች ላይ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤቶች በእቅድ ዝግጅት፣ በፈጻሚን ማዘጋጀት ሒደት፣ በአባላት መዋጮ አሰባሰብ ላይ፣ በአባላት ስነ ምግባር፣ በአቅም ማጎልበቻ ስልጠና፣ በተቋማዊ አደረጃጀትና ግብዓት አቅርቦት፣ በድጋፍና ክትትል እንዲሁም የፓርቲ ስርዓትን በተገቢው ከመዘርጋትና ከሌሎች የፓርቲ ዲሲፕሊን ስራዎች ጋር ተያይዞ ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራትን እቅድ ክንውን በማቅረብ ጉድለቶችን የለየ ውይይት ተደርጓል።
በዚህም በየደረጃው የፈፃሚ ማዘጋጃ መድረኮችን በወቅቱ በማካሄድ ፈጥኖ ወደ ተግባር ምዕራፍ መሸጋገር፣ ከዞን ጀምሮ እስከ ህብረት ኮሚሽን ድረስ የሩብ ዓመቱን ኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን በጊዜው በማካሄድ ለኮሚሽንና ለፓርቲ አደረጃጀቶች ግብረ መልስና የግኝት ምክረ-ሀሳብ መስጠት፣ ከ2 በላይ የብልፅግና ህብረት ኮሚሽን ባለባቸው ቀበሌዎች ህብረቶቹን እንደ ቀበሌ የሚያስተባብሩ የቀበሌ ኮሚሽኖች እንዲደራጁ የተቀመጠውን አቅጣጫ ፈጥኖ ተግባራዊ ማድረግና የመሳሰሉት በመድረኩ በጥንካሬ ታይተዋል።
በሌላም በኩል የአደረጃጀቶችን አፈፃፀም ከማመጣጠን አንፃር ጉድለቶች የሚስተዋሉ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኘው የኮሚሽን ስራ አመራር ኮሚቴ ለተቋማዊ አቅም ግንባታ ስራ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ተነስቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ በቅ/ጽ/ቤቶቹ ላይ በበጀት ዓመቱ 1ኛ ሩብ ዓመት ከተደረገ ድጋፍና ክትትል መነሻ የተዘጋጀ ግብረ መልስ ቀርቦ በጉድለቶች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል፡፡
የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ አቶ ሽኩር ጀማል ባስተላለፉት የማጠቃለያ መልዕክት የሁሉም መዋቅር የኢንስፔክሽን ጽ/ቤቶች ግብና ተልዕኳቸውን በውል ተገንዝበው በቀጣይ ወራት የጽ/ቤቱን እቅዶች በተሻለ ለመፈጸም መስራት እንዳለባቸው አስረድተዋል።
ጽ/ቤቱን በግብዓት በማደረጃትና የግንዛቤ ማስጨበጫ አማራጮችን በማስፋት በሁሉም ዘርፎች ጥንካሬዎችን ማስቀጠልና ጉድለቶችን ማረም እንደሚገባም አቶ ሽኩር አስገንዝበዋል።
Via ስልጤ ዞን ብልፅግና ፓርቲ