የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication This is The official Butajira City Gov't COMM.fb page-ይህ ትክክለኛው የቡታጅራ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን (fb)ፔጅ ነው፦

በከተማዋ በ2017 የተሰሩ ስራዎች አብዛኞቹ በስኬት ተጠናቀዋል ፦ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድበከተማው በ2017 በጀት ዓመት ለመፈፀም ከታቀዱት የመሠረተ ልማትና ሌሎች ስራዎች አብዛኛዎቹ በስኬት...
21/07/2025

በከተማዋ በ2017 የተሰሩ ስራዎች አብዛኞቹ በስኬት ተጠናቀዋል ፦ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ

በከተማው በ2017 በጀት ዓመት ለመፈፀም ከታቀዱት የመሠረተ ልማትና ሌሎች ስራዎች አብዛኛዎቹ በስኬትና በውጤታማነት መጠናቀቃቸውን የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ገለፁ።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮችና አባላት በከተማው የተሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች አፈፃፀም ጥሩና አበረታች መሆኑን ገልፀዋል።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ መፈፀም ተችሏል ብለዋል።

የተመዘገበው የተሻለና አበረታች ውጤትም የአመራሩ፣ የባለሞያዎች ፣ የባለድርሻ አካላትነ እና የማህበረሰቡ ቁርጠኝነትና በኃላፊነት የመትጋት ውጤት መሆንንም አንስተው ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል

በከተማው አንዱ ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራው የከተማዋ "መገለጫ የሆነው የሰላም ጉዳይ ነው"።

ሰላምን አስጠብቆ ለማስቀጠል ከህዝባችን እና ከፀጥታ መዋቅሩ በቅንጅት በቁርጠኝነት ተሰርቷል፤
የ24 ሰዓት ያልተገደበ እንቅስቃሴ ያለበት መሆኑን እና ሰላምን አስጠብቆ ማስቀጠል ተችሎል።

25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለመስራት ታቅዶ በመጀመሪያው ምዕራፋ 17.5 ኪ.ሜ መካከል 13.17 ኪ.ሜትሩ ወደ ተግባር ተገብቶ እየተገነባ ነው።ከዚህም መካከል 8.35 ኪ.ሜትር አብዛኛው ስራ ማጠናቀቅ ተችሏል ።

ሌላው ከንቲባ አቶ አብዱ በከተማው ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራው የምዕራፍ ሁለት በ150 ሚሊየን ብር የአስፓልት ግንባታ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ የተቻለ መሆኑንም ገልፀዋል።

በከተማው በ334 ሚሊየን ብር የአስፓልት ግንባታም እየተሰራ ይገኛል።

በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት የህዝቡ ጥያቄ የነበረውን የማህበረሰብ ዓቀፍ መድሃኒት መደብር ደረጃውን በጠበቀና ስታንዳርድ ባሟላ ሁኔታ በሁለት ወር ተሰርቶ መድሃኒት መሟላቱንም አስታውቀዋል።

ሰው ተክር የሆኑ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን አንስተው ከውሃ ልማት ፣የማብራት አቅርቦት በተመሳሳይ በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው።

በሁሉም የመንግስት ትምህርት ቤቶች 1600 ለቅድመ አንደኛ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት መስጠት ተችሏል።

በ1.3 ቢሊየን የአስተዳደር ህንፃ እየተሰራ መሆኑንና 680 ሚሊየን በመጀመሪያው ምዕራፍ ወጪ የሚደረግ መሆኑን ከንቲባ አብዱ ገልፀዋል።

ከንቲባ አብዱ በከተማው ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶች ለመገንባትም ታቅዶ ተገብቷል ብለዋል፤የአዳሪ ትምህርት ፣ ቡታጅራ ፓርክ በቀጣይ ይሰራል።

ከተማው ከዚህ በላይ ለምቶና አድጎ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከአመራሮቻችን ከባለሙያዎች እና ከማህበረሰቡ በቁርጠኝነት እንሰራለን።

የተመዘገበው የተሻለና አበረታች ውጤትም የአመራሩ የባለሞያዎችና የማህበረሰብ ቁርጠኝነትና በኃላፊነት የመትጋት ውጤት መሆኑንም አንስተው በከተማ አተዳደሩና በራሳቸው ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

(ሐምሌ 14/2017 የመንግስት ኮሙኒኬሽን)

በከተሞች እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው አመላካች ነው - ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ (ሐምሌ 14/2017)፣የማ...
21/07/2025

በከተሞች እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው አመላካች ነው - ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

(ሐምሌ 14/2017)፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶች ምልከታ አድርገዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለጹት የመስክ ምልከታው አብይ ዓላማ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታቀዱ ተግባራት ከወረቀት ሪፖርት ባለፈ ምን ያህል ተፈጻሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነው።

በክልሉ የመስክ ምልከታ በተደረገባቸው ከተሞች የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው የምክር ቤት አባላት ተገንዝበዋል ሲሉም ዋና አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።

እንደ ሀገር በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሰጡ ኢኒሼቲቮችን በማሳደግ በክልሉ ተግባራዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ዋና አፈ ጉባኤዋ በአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ አመራሩ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀምና የህብረተሰብ ተሳትፎን በማጎልበት ማልማት ከተቻለ በአጭር ጊዜ ለውጥ እንደሚመጣ የተናገሩት ዋና አፈ ጉባኤዋ በተለይ የከተማ ኮሪደር እንዲሁም ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በከተሞች የሚካሄደው የልማት ስራ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲካሄድ ከማስቻል ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ዋና አፈ ጉባኤዋ አብራርተዋል።

የክልሉ ህዝብ የመንግስትን የልማት ግብ ውጤታማ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ላይ የላቀ አቅም እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል።

በመስክ ምልከታው በዚህ አመት ግንባታቸው እየተካሔደ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት በላቀ ቁርጠኝነት በፍጥነት ወደ ተግባር መግባታቸውን ዋና አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

ክልሉ ተመስርቶ ስራ ሲጀምር በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ በማለፍ ነበር ያሉት አፈ ጉባኤዋ ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች በጽናት በማለፍ የአዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሔደ መሆኑን ተናግረዋል ።

በክልሉ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚያስችሉ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ተፈጻሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ ለአብነት የማህበረሰብ መድሀኒት ቤቶችን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የተገነቡ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን የገለጹት ዋና አፈ ጉባኤዋ በተለይ የውጭ ምንዛሬን ማስገኘት የሚያስችሉ ኢንዱስትሪዎች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አዎንታዊ ሚና እንዳላቸው አብራርተዋል።

በከተማው የኑሮ ውድነትን ለማርገብ የተቋቋሙት የሰንበት ገበያዎች በአምራቹና ሸማቹ መካከል ጤናማ የንግድ ስርዓት እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል።

በመስክ ምልከታው የምክር ቤት አባላት ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኑን ስለመገንዘባቸው ዋና አፈ ጉባኤዋ ገልፀዋል።

የምክር ቤት አባላት በከሰዓት ውሎ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የልማት ስራዎች ምልከታ እንደሚያደርጉ ተጠቁሟል።
የክልሉ ኮሙኒኬሽን

"በመትከል ማንሰራራት" የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በቡታጅራ ከተማ አሻራቸውን አኖሩ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮ...
21/07/2025

"በመትከል ማንሰራራት" የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በቡታጅራ ከተማ አሻራቸውን አኖሩ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ እየተካሄዱ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ አድርገዋል።

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ የምክር ቤት አባላት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል ቃል የአረንጓዴ አሻራ በቡታጅራ የማህበረሰብ አቀፍ መድሀኒት መደብር እና በከተማዋ ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ አሻራቸውን አኑረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ 7.5 ቢሊዮን ችግኝ በመትከል ማንሰራራት አካል የሆነው የችግኝ ተከላ አሻራ የማኖር መርሃ -ግብር የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ እንዳልካቸው ጌታቸው ፣የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ፣ የክልል ፤የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች አሻራቸውን አኑረዋል።

(ሐምሌ 14/2017 የመንግስት ኮሙኒኬሽን)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው (ሐምሌ 14/2017)የምክር ቤቱ አባላት በከተማዋ እየተነገባ  ያለውን...
21/07/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው

(ሐምሌ 14/2017)የምክር ቤቱ አባላት በከተማዋ እየተነገባ ያለውን የኮሪደር ልማት፣የከተማ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገድ፣የክልል ተቋማት የግንባታ ፕሮጀክቶች፣የማህበረሰብ አቀፍ መድሀኒት ቤት፣የአረንጓዴ መናፈሻ ስፍራዎችን እና ሌሎች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ ልማት አውታሮችን እየተመለከቱ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ መንግስት የተቀረጹት በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው።

በከተሞች እየተገነቡ የሚገኙ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎች ፕሮጀክቶችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ገንብቶ የማጠናቀቅ ልምድ ማዳበር የተቻለበት ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው ብለዋል።

የምክር ቤቱ አባላት እንደ ሀገር "በመትከል ማንሰራራት"በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሔደውን የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ለማጠናከር በቡታጅራ ከተማ አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።

የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ተሰርተው ለምርቃት ስለበቃው የማህበረሰብ ዓቀፍ ፋርማሲ እንዳሁም ሌሎች መሰረተ ልማቶች አስመልክቶ ገለፃና ማብራሪያ እየሰጡ ነው የምናደርሳችሁ ይሆናል።

ሌሎች የክልል የዞን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የሰላም ሰገነት አብነት የሆነችው ቡታጅራ ከተማ እንግዶቿን በምሽት እየተቀበለች ነው !! (ሆሳዕና፣ሐምሌ 13/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ...
20/07/2025

የሰላም ሰገነት አብነት የሆነችው ቡታጅራ ከተማ እንግዶቿን በምሽት እየተቀበለች ነው !!

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 13/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ እየተነገባ ያለውን የኮሪደር ልማት ምልከታ እያደረጉ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለጹት ከነገ ሐምሌ 14/2017 ጀምሮ የምክር ቤት አባላት በክልሉ በልዩ ልዩ ከተሞች እየተካሔዱ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ ይደረጋል ብለዋል።

የዚሁ መርሐ ግብር አካል የሆነው የቡታጅራ ከተማ የኮሊደር ልማት ስራ በምክር ቤቱ አባላት የምሽት ድባብ ምልከታ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ እንደገለጹት
በከተማዋ 25 ኪሜ የኮሪደር ልማት ስራ ለመስራት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።

እስካሁን ባለው ሂደት 13 ነጥብ 17 ኪሜ የኮሪደር ልማት ስራ ተግባራዊ ማድረግ እንደተቻለም ተጠቁሟል።

በከተማዋ 8 ነጥብ 37 ኪ/ሜ የኮሪደር ልማት ለምረቃ ስለመብቃቱም ለምክር ቤቱ አባላት ገለጻ አድርገዋል።

ከተማዋን ለኑሮ፣ለንግድ፣እና ለኢንቬስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ሂደት ውጤታማ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን መግለፃቸውን ከክሌሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በነገው እለት በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የልማት ስራ በምክር ቤቱ አባላት ምልከታ ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አገኘች(ሐምሌ 13/2017 )ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከ18 እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡በሴቶች የ800ሜ ከ...
20/07/2025

ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አገኘች

(ሐምሌ 13/2017 )ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከ18 እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡

በሴቶች የ800ሜ ከ18 ዓመት በታች የፍፃሜ ውድድር ኤልሳቤጥ አማረ በበላይነት በማጠናቀቅ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።

አትሌት ሕይወት አምባው በሴቶች ከ18 ዓመት በታች 5 ሺህ ሜትር ርምጃ ውድድር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ ማግኘቷ ይታወሳል።

የውድድር ስፍራዎቻችንን ለበጎ ዓላማ መጠቀም!!በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው 2018 የበጎ ፍቃድ ስራዎች የአብዛኛው ወ...
20/07/2025

የውድድር ስፍራዎቻችንን ለበጎ ዓላማ መጠቀም!!

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው 2018 የበጎ ፍቃድ ስራዎች የአብዛኛው ወጣት መዋያ የሆነው የስፖርታዊ ውድድር ስፍራዎችን ለበጎነት መጠቀም ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።

የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ አሰፋ በጎነት ለሌሎች ደስታ ምክንያት መሆን፣ ለሀገር የጎደለውን የመሙላት ተግባር ነው።

በዚህ ዓመት በክረምት ወቅት ከሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች አንዱ በውድድር ስፍራዎች ላይ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን ማከናወን አንዱ ተግባር በመሆኑ ችግር ያለባቸውን አቅመ ደካሞችና በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ትምህርት ያቋረጡ ህጻናትን ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ከአልባሳት ማሰራጨት ባለፈ የቤት ግንባታና እድሳት፣ የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣ የማስተማርና ሌሎችንም የበጎ ፈቃድ ስራዎች በክረምቱ ወቅት የሚከናወኑ ተግባሮች መሆናቸውንም አቶ አለሙ ተናግረዋል።

በከተማው በጤና ቡድኖች ውድድር እየተሳተፈ የሚገኘው የዚቱ እግር ኳስ ቡድን አስር ደርዘን ደብተር እና አራት ፖኬት እስኪርቢቶ ለተማሪዎች

የበጎ ፍቃድ ተግባራት በሌሎችም ቡድኖች ድጋፎች እንደሚቀጥሉና ይህንን ስጦታ ላበረከቱት የዚቱ የእግር ኳስ ቡድን አባላትን የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ አሰፋ ምስጋና አቅርበዋል።

በክልሉ የፖለቲካ ምህዳሩን ሰፊ ከማድረግ አንጻር የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው - ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር ) ( ሐምሌ13/2017 )  "2017 ዓ.ም የትጋትና የስኬት ዓመት " በሚል መሪ...
20/07/2025

በክልሉ የፖለቲካ ምህዳሩን ሰፊ ከማድረግ አንጻር የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው - ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር )

( ሐምሌ13/2017 ) "2017 ዓ.ም የትጋትና የስኬት ዓመት " በሚል መሪ ሀሳብ ክልል አቀፍ የ 2017 ዓ.ም የፓርቲ ስራዎች ማጠቃለያ ግምገማና የ 2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር እንደገለጹት በ2017 በጀት ዓመት በርካታ ተግባራት የተከናወኑበት እና በዚያው ልክ የላቀ ስኬት የተመዘገበበት ነበር ብለዋል።

በክልሉ የተጀመሩ የፖለቲካና የመንግስት ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል እየተካሔደ እንደነበር ኃላፊው አመላክተዋል።

በክልሉ የፓርቲ እና የመንግስት አጠቃላይ የተቋም ግንባታ ላይ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዶ/ር ዲላሞ አስረድተዋል።

በክልሉ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ውይይት መካሔዱን የገለጹት ኃላፊው ይህን ተከትሎም በአሰራር ስርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

የተቋም ግንባታ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ካለው የላቀ ፋይዳ አንጻር ዘርፈ ብዙ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራት ለመጠገን የፖለቲካ ባህል የመቀየር ጉዳይ ወሳኝ ስለመሆኑ የገለጹት ኃላፊው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የትብብር እና የፉክክር ሚዛን መጠበቅ ተገቢ መሆኑን ዶ/ር ዲላሞ አመላክተዋል።

በክልሉ የፖለቲካ ምህዳሩን ሰፊ ከማድረግ አንጻር ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ተግባብቶ በመስራት እንዲሁም የሲቪክ ማህበረሰቦች እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራ መከናወኑን ኃላፊው አብራርተዋል።

ባለፉት ዓመታት የነጠላ ትርክቶች ጎልተው የታዩበት እና አሁንም ያልተሻገርነው ጉዳይ ነው ያሉት ኃላፊው በፓርቲ እና በመንግስት የላቀ ጥረት በወል ትርክት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በክልሉ የሀብት አስተዳደር ስርዓትን በማጠናከር የተቋማት ግንባት እየተካሔደ መሆኑን ኃላፊው ጠቅሰዋል።

2017 ዓ.ም የትጋትና የስኬት ዓመት እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ዲላሞ በአፈጻጸም ረገድ የተስተዋሉ መልካም ልምዶችን አጠናክሮ በመቀጠል በጉድለት በተለዩ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት መስራት ተገቢ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን
በበኩላቸው ፣ ዞኑ የተረጋጋና ሰላም የሠፈነበት እንዲሆን፣ በተለይም በመስቃን ቤተ ጉራጌና በማረቆ ህዝቦች መካከል የነበሩ አለመግባባቶች እንዲፈቱ ፓርቲው ጉልህ ሚና ተጫውቷል ማለታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አስተዳዳሪው አክለውም በየደረጃው ያሉ የማረቆና የመስቃን አመራሮች በቀጠናው ሠላም ይሰፍን ዘንድ ለነበራቸው ከፍ ያለ ሚና አመስግነዋል ።

የቡታጅራ ከተማ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት የ2018 የሥራ ፈላጊዎች ልየታ የንቅናቄ መድረክ በቀበሌዎች ተካሂደ።ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ከተማ አቀ...
19/07/2025

የቡታጅራ ከተማ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት የ2018 የሥራ ፈላጊዎች ልየታ የንቅናቄ መድረክ በቀበሌዎች ተካሂደ።

ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ከተማ አቀፍ የሥራ ፈላጊዎች ልየታ የንቅናቄ መድረክ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል።

በከተማ ደረጃ የተካሂደው መድረክን ተከትሎ በከተማው ባሉ ሦስት ( እሬንዛፍ ፣እሬሻ እና ዘቢዳር) ቀበሌዎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ በየቀበሌዎች በ2017 የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ዕቅድ ክንውን ላይ ግምገማና ውይይት ተደርጓል ።

የከተማው ምክትል ከንቲባና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጀ ጥላሁን ዕቅድ ክንውን ላይ በጥናካሬ እና ጉድለቶች ልየታ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ የተሻሉ ስራዎችን በማስቀጠል ክፍተቶችን ለማስተካከል ይሰራል።

የዘጠና ቀናት የንቅናቄ ተግባራት ዕቅድ ክንውን አፈፃፀም የቀበሌዎች የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና ተግባራትም ተገምግሟል።

ምክትል ከንቲባ አቶ ደረጀ የሥራ ፈላጊዎች (አጥ) ልየታ ተግባር በከተማው በሦስቱም ቀበሌና መንደሮች ለማስኬድ የሚያስችል የባለድርሻ አካላትና የባለሙያዎች ስምሪት ተሰጥቶ ተግባሩ የሚጀመርም እንደሆነም ጠቁመዋል።

(ሐምሌ 12/2017 የመንግስት ኮሙኒኬሽን)

 !!12/11/2017 ዓ.ም_ቡታጅራ!!በቡታጅራ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን በከተማዋ በሶስቱም ቀበሌ ድጋፍ ለማድረግ የአመራር ስምሪት ተግባራትን እያከናወነ ነው።የሱፐ...
19/07/2025

!!

12/11/2017 ዓ.ም_ቡታጅራ!!

በቡታጅራ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን በከተማዋ በሶስቱም ቀበሌ ድጋፍ ለማድረግ የአመራር ስምሪት ተግባራትን እያከናወነ ነው።

የሱፐርቪዥኑ ቡድን የመጀመሪያውን ድጋፍ በእሬሻ ቀበሌ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ በቀን 11/11/2017ዓም የጀመረ ሲሆን እስከ 12/11/2017ዓም አካሄዷል።

ቡድኑ አጠቃላይ የሶስትዮሽ ውይይት በመጀመሪያው ያደረገ ሲሆን አጠቃላይ የነባራዊ ሁኔታ ትንተና እና ዋና ዋና የመንግስት ተግባራትን ሪፖርት ቀርቦ በቀበሌው ገምግሟል።

አጠቃላይ ቡድኑ በሁሉም ማህበራዊ መሠረት ሁለት የብልፅግና ሕብረት እና በስሩ ያለ ሁለት የብልፅግና ቤተሰብ የ2017ዓም አፈፃፀም እና የ2018ዓም የእቅድ ዝግጅት ድጋፍና ሱፐርቪዥን ለማድረግ ተከፋፍሎ እየሰራ ይገኛል።

አጠቃላይ በቀበሌው ባለው ቆይታ ዛሬ ከአደረጃጀት ድጋፉ ጎን ለጎን የሁለት የብልፅግና ሕብረት ቢሮዎችን አጠቃላይ ከቀበሌው አመራር ጋር ከግንባር ቀደሞች ጋር በመሆን እየሰራ ይገኛል።

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በከተማ ፓርቲ ደረጃ በተቀመጡ በድስፕሊን ከሚፈፀሙ ተግባራት መካከል ሌላኛው የሌማት ቱርፋት ተግባርን በቀበሌው አስጀምሯል።

በመትከል ማንሰራራት !! በሚል መርሃ ግብር የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቀበሌው ደረጃ በለምባዲና የወጣት ማዕከል የአቦካዶ ፍራፍሬ ችግኝ ተግባራዊ አድርጓል።

መረጃው የቡታጅራ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ነው።

እንኳን ደስ አላችሁ፦የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሞዴል ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል በመገንባት የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።የክልሉ ንግድና ገበያ ል...
18/07/2025

እንኳን ደስ አላችሁ፦

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሞዴል ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል በመገንባት የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት ተግባር አፈፃፀም ሴክቶሪያል ጉባኤ በሆሳና ከተማ አድርጓል።

በመድረኩ በተደረገ የዞኖችና ልዩ ወረዳዎች እውቅናና ሽልማት ፕሮግራም የቡታጅራ ከተማ በልዩነት ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል የፌድራል የሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል እስታንዳርድ ባሟላ መልኩ በመገንባት የህብረተሰቡ የኑሮ ውድነት ከማረጋጋት አንፃር በክልሉ ካሉ 151 የሰንበትና ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መካከል የተሻለና ሞዴል በመሆን ዋንጫና የሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶለታል።

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሻፊ ሽፋ ከተማ አስተዳደሩ የህብረተሰቡ የኑሮ ጫና በመገንዘብ በበጀት ዓመቱ ከ700,000 ሺ ብር በላይ በመመደብ ከሰንበት እስከሰንበት ገበያ ማዕከል በመገንባት በርካታ ምርቶች ያቀረበ ሲሆን የበርካቶችም ስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

ከተማ አስተዳደሩ በጀት ከመመደብ ባለፈ ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ ቦታ ከህብረተሰቡ ችግር አይበልጥም በማለት አስተባባሪዎች ቦታ በመለየት የገበያ ማዕከል እንዲሆን ከመወሰን ባሻገር የገበያው ግንባታ ሂደት በመከታተል ለውጤት እንዲበቃ አድርገዋል። የጽ/ቤት ኃላፊው ለአስተባባሪዎች ለጽ/ቤቱ ማኔጅመንትና ለጠቅላላ ባለሙያ ምስጋና አቅርበዋል።

በቡታጅራ ከተማ 2 ከሰንበት እስከ ሰንበት ገበያ ማዕከል እና 1 ቅዳሜ ገበያ በማቋቋም የህብረተሰቡ ምርት እየቀረበ ሲሆን ተጨማሪ ሰንበት ገበያ ለመገንባት 465,000 ብር በጀት በመመደብ ግዥ ተፈፅሞ ቀጣይ ወደ ግንባታ የሚገባ ይሆናል።

ከዚህ በተጨማሪ 15,000,000 ሚሊየን ብር በመመደብ ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል ግንባታ ላይ ያለ ሲሆን የህብረተሰቡ የኑሮ ወድነት በአንፃራዊነት ያረጋጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ሀሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩና ሰላምን ለመንሳት በሚንቀሳቀሱ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል የከተማዋን ሁለንተናዊ ሰላምና ልማት ለማደናቀፍ ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት የመንግስትና የህዝብ መደበኛ ...
18/07/2025

ሀሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩና ሰላምን ለመንሳት በሚንቀሳቀሱ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል

የከተማዋን ሁለንተናዊ ሰላምና ልማት ለማደናቀፍ ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት የመንግስትና የህዝብ መደበኛ ስራዎችን ለማደናቀፍ በሚሰሩ ጥብቅ ቁጥጥር እና ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል፦ በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ ፖሊስ

የቡታጅራ ከተማ ፖሊስ ዋና አዛዥ ም/ሳጂን ሙህዲን አምዛ የመንግስትና የህዝብን መደበኛና የልማት ስራዎችን ሊያደናቅፉ የሚችሉ ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩ ተስተውሏል።

ከተማዋን ገቢ ለማሳጣት በመንግስትና በሚመለከተው አካል ያልተላለፈ ሀሰተኛ መረጃ በማቀነባበር ህዝቡን ለማሳት በሚያሰራጩ ህጋዊ የእርምት እርምጃ ይወሰዳል።

በተለይ ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያዎችን በማዘጋጀት ፕሮፓጋንዳ የሚለጥፉ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ እርምጃ ይሰዳል ብለዋል።

የከተማዋና የአካባቢዋ ማህበረሰብ የከተማውን ልማት ሰላምና ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማደናቀፍ በሚሰራጭ ሀሰተኛ መረጃ ትኩረት አለመስጠትና ከመንግስት መደበኛ ሚዲያዎች መረጃ መውሰድ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ቡታጅራ ከተማ የ24 ሰዓት ሰላማዊ እንቅስቃሴ መኖሩን አንስተው በቀጣይም ከማህበረሰቡ እና ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ጥቃቅን ወንጀሎችን ጭምር በመቆጣጠርና በመከላከል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥልም እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ማህበረሰቡ ከተማው እንዳይረጋጋ የሚንቀሳቀሱትን ለፀጥታ አካል አሳልፎ እንዲሰጥ ም/ሳጂን ሙህዲን ጥሪ አቅርበዋል።

(ሐምሌ 11/2017 የመንግስት ኮሙኒኬሽን)

ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን፦
tiktok https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8v44ergN5SJ&_r=1
ቴሌግራም፦ https://t.me/ButajiraCommunication/58
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/buta1921/
ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/
X ፦ https://mobile.twitter.com/ButajiraB
ኢንታግራም፦ https://www.instagram.com/butajirab

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication:

Share