Naod Tube

Naod Tube like like

የትግራይ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ በትግራይና አፋር ክልሎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው የትግራይ አፈንጋጭ TDF እና ከህወሓት የተገነጠሉ ታጣቂ ቡድን ዛሬ በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃ...
10/08/2025

የትግራይ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ በትግራይና አፋር ክልሎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው የትግራይ አፈንጋጭ TDF እና ከህወሓት የተገነጠሉ ታጣቂ ቡድን ዛሬ በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት አድርሷል በማለት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ከሷል።

ቢሮው፣ ታጣቂ ቡድኑ “ጠብጣብ” በተባለ ቦታ ላይ አደረሰው ባለው ጥቃት የአንድ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አባል ሕይወት መጥፋቱን ገልጧል። ይህ አጥፊ ተግባር ከቀጠለ ቡድኑን በሚመሩና በሚያስተባብሩ አካላት ላይ ርምጃ እወስዳለሁ በማለት ያስጠነቀቀው ቢሮው፣ ደም መፋሰሱ ባስቸኳይ ይቁም በማለት ጥሪ አድርጓል።

ሰበር ዜና‼️ ጃል-መሮ ታፈነ!➖➖➖➖የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ዋና አዛዥ እና የህወሓት ተለላኪው ጃል-መሮ በጓዶቹ ተጠልፎ ለደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ተላልፎ መሰጠቱ ከተማኝ ምንጮች አረጋግጠናል። እነዚ...
08/08/2025

ሰበር ዜና‼️
ጃል-መሮ ታፈነ!
➖➖➖➖

የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ዋና አዛዥ እና የህወሓት ተለላኪው ጃል-መሮ በጓዶቹ ተጠልፎ ለደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ተላልፎ መሰጠቱ ከተማኝ ምንጮች አረጋግጠናል።
እነዚህ ምንጮች እንደገጹት ከሆነ የጀዋር እጅ ሳይኖርበት አይቀርም የተባለ ሲሆን ጃል መሮን ዓፍነው ለደቡብ ሱዳን አሳልፈው የሰጡት የጃል-መሮ ጓዶች ከጀዋር ቅርበት እንዳላቸው እነዚህው ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል። ጃል-መሮ በዚህ ሰዓት በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

የህወሓት አርሚ 70 ሰበር መረጃ‼️ማይካድራን ጨምሮ ወልቃይት ውስጥ ዘግናኝ ጭፍጨ’ፋ ፈጽመው ወደሱዳን በሸሹ ወንጀለኞች የተደራጀው የአርሚ 70 ከፍተኛ አመራር የነበረ ገ/ሄር መስፍን (ወዲ ...
07/08/2025

የህወሓት አርሚ 70 ሰበር መረጃ‼️

ማይካድራን ጨምሮ ወልቃይት ውስጥ ዘግናኝ ጭፍጨ’ፋ ፈጽመው ወደሱዳን በሸሹ ወንጀለኞች የተደራጀው የአርሚ 70 ከፍተኛ አመራር የነበረ ገ/ሄር መስፍን (ወዲ መስፍን) ከአርሚ 70 ኮር 1 የተውጣጡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ታጣቂዎች በመያዝ በመተማ በኩል ወደኢትዮጵያ ሰርጎ በመግባት ከተለላኪው ፋኖ ጋር በመቀላቀል የሽብር ጥቃት ለመክፈት ሲንቀሳቀስ በመረጃና ማስረጃ ሲከታተል የቆየው የኢትዮጵያ አስተማማኝ ደጀን የሆነው ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት Surgical operation በመስራት ያሰለፋቸውን ታጣቂዎች ሙ’ት፣ ቁስለኛ እና ምርኮኛ ያደረገ ሲሆን የሽብር ቡድኑ መሪ የነበረው ገ/ሄር መስፍን (ወዲ መስፍን) ተማርኳል።

አስደሳች ዜና!የሁመራ አቅጣጫ  እንዳይታሰብ ተደርጎ   አስፈላጊም ከሆነ ወደ ፊት እንዲገሰግስ ሆኖ  በኢፌዴሪ  መከላከያ ሜካናይዝድ እግረኛ አየር ሃይል  ጦር  ክርችምችም ተደርጓል ።  ሻዕ...
06/08/2025

አስደሳች ዜና!

የሁመራ አቅጣጫ እንዳይታሰብ ተደርጎ አስፈላጊም ከሆነ ወደ ፊት እንዲገሰግስ ሆኖ በኢፌዴሪ መከላከያ ሜካናይዝድ እግረኛ አየር ሃይል ጦር ክርችምችም ተደርጓል ። ሻዕቢያ " በሁመራ ገብቼ መከላከያን ቢዚ አድርጌ የጉዞ አሰብን ጉዳይ አጨናግፋለሁ" ሚለው ቅዥቷ በህልም እንኳን የማይሞከር ሆኗል ። በተቃራኒው በኢትዮጵያ በኩል ከቡሬ ወደ አሰብ ሁሉ ነገር በተጠንቀቅ ላይ ይገኛል ።

ሻዕቢያ ተስፋ ያረገቻቸው የህውሃት አዛውንታት የትግራይ ህዝብ ተነስቶባቸዋል ፣ መዋቅራቸው ተበትኗል፣ ህዝብ አንቅሮ ከመትፋት አልፎ በየቀበሌ በወረዳና ዞኖቹ የሚገኙ መዋቅሮታቸው እያፈራረሳቸው ይገኛል። የህውሃት ነገር በትግራይ ክልል ህዝብ እግ ፍፃሜው ላይ ደርሷል።

በዚህ ብቻ ሳያበቃ ህዝባዊ ማዕበሉ ወደ አስመራ ሊያመራ አንድ ሀሙስ የቀረው ደረጃ ላይ እንገኛለን ፣ በአዲሃሎ ኢትዮጵያ የምታስቀምጣቸው መሪዎች ከወዲሁ ዝግጅታቸውን አገባደው ፊሽካ እየተጠባበቁ ይገኛል ፣ በተመሳሳይ የ34 ዓመታት ዕስር ያጎሳቆለው የአስመራ ህዝብም የነፃነት ቀኑን በጉጉት መጠበቅ ይዟል።

ከዚህ ሁሉ ጀርባ ግዙፉ የኢትዮጵያ ህዝብና ፣ጦር መኖር ሲታከልበት ኢትዮጵያ ባህርበሯን ተረክባ አስመራ የራሷን ሰው የመሾሟን ነገር አይቀሬነትን ከነኢሳያስ በላይ ፍንተው አርጎ የተረዳ የለም ።

በእርግጥም በነ አዛውንቱ ኢሳያስ አዲሃሎ ቤተ-መንግስት መንደር ሁሉ ነገር ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ከሆነ ሰነባብቷል ፣ ለዚህም ከአሜሪካ እስከ አንታርክቲካ የማይጠሩት የሃገር ስም፣ የማይማፀኑት ሽፍታ ቡድን ከሱማሊያ እስከ ሱዳን የማይለማመኑት ዲፕሎማት የለም ፤ ነገር ግን ጉዳዩ አክትሟል ! እንደ አትሌቶቿና እንደ ጥንተ ታሪኳ የጀመረችውን በድል ሳታገባድድ የማታፈገፍገው ኢትዮጵያ የመንገዱን ግማሽ አጠናቃለች።

ቁጥራችው ከ300 በላይ የሆኑና በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪውን በመቀበል ከነትጥቃቸው ለመከላክያ ሰራዊት እጃቸው ሰጥተዋል::ሰላም ለኢትዮጵያ ሰላም ለአማራ ክ...
06/08/2025

ቁጥራችው ከ300 በላይ የሆኑና በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪውን በመቀበል ከነትጥቃቸው ለመከላክያ ሰራዊት እጃቸው ሰጥተዋል::

ሰላም ለኢትዮጵያ ሰላም ለአማራ ክልልና ህዝብ

በህወሓት ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል አሁንም እንደቀጠለ ነው።አለም ገብረዋህድ 25 ማዕከላይ ኮሚቴ ይዞ ህወሓትን ለሁለት እንደከፈለው የደረስንበት መረጃ ይጠቁማል። እነ ደብረፅዮን ሞንጀሪኖን ...
04/08/2025

በህወሓት ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል አሁንም እንደቀጠለ ነው።አለም ገብረዋህድ 25 ማዕከላይ ኮሚቴ ይዞ ህወሓትን ለሁለት እንደከፈለው የደረስንበት መረጃ ይጠቁማል።

እነ ደብረፅዮን ሞንጀሪኖን የያዘ ጥቂት ቡድን አሁንም ስልጣን ወይ ሞት እያለ ይገኛል።

ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል የመንግስትንና የፖርቲ መደበ...
03/08/2025

ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል

የመንግስትንና የፖርቲ መደበላለቅ እንዲለያይ በጥናት የተደገፈ መፍትሄ ለህወሓት ቢቀርብም በክልሉ ለ30 ዓመታት በብቸኝነት ተቆጣጠሮ የቆየው የህወሓት አስተሳሰብና አሰራር ሊያሰራን አልቻለም::

ባደረግነው ጥናት የ19 ወረዳ አመራሮች በምክር ቤት ሳይሆን በህወሓት የተሾሙ ሆኖው ነው ያገኘናቸው፤ ይህንን ለመቀየር ብዙ ርቀት ብንሄድም ለዓመታት በህወሓት የተተበተበው ኔትወርክ ሊያሰራን አልቻለም:

እኔ ስመራው የነበረው የነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡትን ሃላፊነቶች እንዳይወጣ በተለይ የያኔው ምክትል ፕሬዚዳንት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) የሚመራው የፀጥታ ሃይል አኗኗሩ እንዲበላሽ በማድረግ በጊዚያዊ እስተዳደሩ ተቃዉሞ እንዲኖረው በመስራት ለስልጣን መወጣጫ ተጠቅሞበታል::

ታደሰ ወረደና ከኮር በላይ የሰራዊት አመራር ነን “ የሚሉ በግላጭ የህወሓት ደጋፊ የሆኑ አካላት ጊዚያዊ አስተዳደሩን አላሰራ አላንቀሳቅስ ነው ያሉን በሰአቱ የተከመሩ ችግሮችን ፣ የውጭውን ይቅርና የውስጥ ስራዎችን ለመስራት አልቻልንም ነበር::

በአሁን በስልጣን ላይ ያለው ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ቡድንም አስተዳደርም ለውጥ የማምጣት አቅምና ቅንነት የለውም:: ያለፉት 30 ዓመታት በትግራይ የነበረው መንግስትና ፓርቲ አንድ ናቸው የሚል የቆየ አስተሳሰብ ነው እያራመደ ያለው ፤ በዚህ መሰል መንገድ ደግሞ በአሁናዊ የትግራይ ሁኔታ ህዝብን የሚጠቅም ለውጥ ማምጣት አይቻልም “

የጀመርነው ለውጥ የእኛ ሳይሆን የተተኪው ሃይል ድርሻ ነው ፣ እኛ እያደርግን ያለነው ለተተኪው መንገዱን የማሳየት ስራ ነው፣ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ የጀመርነው እንቅስቃሴ ባለቤት መሆኑ ማወቅና መደገፍ አለበት ፣ የፌደራል መንግስትም ይህንን የለውጥ ጥያቄ የመደገፍ ሃላፊነት አለበት “

ህዝቡ ምርጫዬ ሰላም ነው እምቢ ለጦርነት ማለት መቻል አለበት ፣ የአንድ ፓርቲ የእድሜ ልክ አገዛዝ በቃኝ የብዙሃን አመራር ነው የምፈልገው ማለት መቻል አለበት

ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ

ከእገታ ማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት ህፃን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ተገድሎ ተጥሎ ተገኘ።ከ5 ቀናት በፊት የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ከተማ ቀበሌ 01 ነዋሪ የሆነው ...
02/08/2025

ከእገታ ማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት ህፃን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ተገድሎ ተጥሎ ተገኘ።

ከ5 ቀናት በፊት የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ከተማ ቀበሌ 01 ነዋሪ የሆነው ህፃን ናኦድ ተኽላይ ብርሃነ በአጋቾች ታፍኖ መወሰዱንና አጋቾቹ ለማስለቀቅያ 2 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው የሚጠቅስ በህፃኑ ፎቶ የታጀበ ፅሁፍ በበርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፆች ሲዘዋወር ነበር።

ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች ወደ ህፃኑ ቤተሰብ ደውለው ነው የማስለቀቅያ ብሩን የጠየቁት ይላል ሲዘዋወር የቆየው ፅሁፍ።

ዛሬ ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም የተሰማው ግን እጅግ አስደንጋጭ መርዶና ከሰውነት የወጣ የጭካኔ ተግባር ነው።

ህፃን ናኦድ ተኽላይ በጭካኔ ተገድሎ የፀጥታ አካላት በተገኙበት አስክሬኑ በፍሳሽ መተላለፍያ ቦይ ተጥሎ ተገኝቷል።

የሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ አስክሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መላኩን ተሰምቷሎ።

Via Tikva

ትራምፕ ለኢሳያስ ደብዳቤ ላኩየአሜሪካው ፕረዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ከትናንት በስተያ በጻፉት ደብዳቤ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማደስ አስተዳደራቸው ዝግጁ መ...
01/08/2025

ትራምፕ ለኢሳያስ ደብዳቤ ላኩ

የአሜሪካው ፕረዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ከትናንት በስተያ በጻፉት ደብዳቤ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማደስ አስተዳደራቸው ዝግጁ መሆኑን ገለጹ።
ፕረዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ የቀድሞው የጆ ባይደን አስተዳደር በአለም ዙሪያ ያደረሰውን አሉታዊ እና ጎጂ ጉዳት እየቀለበሱ እንደሆነ በገለጹበት ለአስመራው መሪ በላኩት ደብዳቤ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማሻሻል አስተዳደራቸው ቁርጠኛ መሆኑን አስፍረዋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአሜሪካ እና በኤርትራ መካከል "በሃቀኝነት፣ በመከባበር እና በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር ዙሪያ ሰላምና ብልጽግናን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ባሉ ዕድሎች ላይ የተመሰረተ ገንቢ እና ፍሬያማ አገራዊ ግንኙነት እንደገና ለመመስረት አስተዳደራቸው ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለላኩላቸው የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት ለአስመራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ያላቸውን አድናቆት ገልጸውላቸዋል ሲል የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማኔ ገ/መስቀል በX ገጻቸው ያጋሩት መረጃ ያመለክታል።

01/08/2025

Alert News 👀

በሱዳን የሚገኘውና አርሚ 70 በማለት የሚጠራው የህወሃት ታጣቂ ቡድን በሱዳን በኩል አልፋሽካ አካባቢን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች እንዲሰማሩ በሱዳን የጦር አዛዦች መመሪያ እንደተሰጠ ታውቋል::

የስምረት ፓርቲ ፅ/ቤት በታጣቂዎች  ተዘረፈ - ምንጮችበአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ስምረት ፓርቲ፣ ባለፈው ሳምንት በመቀሌ ከተማ የከፈተው ዋና ጽ/ቤቱ በታጣቂዎች መዘረፉ ተሰማ፡፡ትናንት ማታ ...
30/07/2025

የስምረት ፓርቲ ፅ/ቤት በታጣቂዎች ተዘረፈ - ምንጮች

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ስምረት ፓርቲ፣ ባለፈው ሳምንት በመቀሌ ከተማ የከፈተው ዋና ጽ/ቤቱ በታጣቂዎች መዘረፉ ተሰማ፡፡

ትናንት ማታ 4:45 ገደማ ማንታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ዘበኞችን አስፈራርተው ወደ ጽ/ቤቱ በመግባት የፓርቲውን ንብረቶች መዝረፋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ የቀሩትን ሰባብረውና ወረቀቶችን ቀዳደው ከስራ ውጪ ማድረጋቸውን አመልክተዋል፡፡፡

ፓርቲው በቅርቡ በመቀሌ በከፈተው ዋና ጽ/ቤቱ ሊሰጥ የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ ባልታወቀ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ የሚታወስ ነው።

29/07/2025

በአላማጣ ከተማ 04 ቀበሌ ዞን 1፣ በታዋቂው ባለሀብትና ስራ ፈጣሪ በአቶ ሰለሞን አያሌው መኖሪያ ቤት ላይ ሰኞ ምሽት በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት፣ የ16 እና የ12 ዓመት ልጆቻቸው ህይወት ማለፉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ።

በጥቃቱ፣ ባለሀብቱ አቶ ሰለሞን እና ባለቤታቸውም ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለተጨማሪ ህክምና ወደ መቀሌ ከተማ ተወስደው ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑ ታውቋል።

ምንጮች እንደገለጹት፣ ጥቃቱን የፈጸሙት ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ሲሆኑ፣ ድርጊቱን የፈጸሙበት ምክንያት እስካሁን በግልጽ አልታወቀም።

የሟች ህጻናቱ አስከሬን ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 22, 2017 ዓ.ም. የቀብር ስነስርዓታቸው የተፈጸመ ሲሆን፣ በከተማው ህዝብ ዘንድ ጥልቅ ሐዘንን ፈጥሯል።

የጸጥታ አካላት በጉዳዩ ላይ ምርመራ መጀመራቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ስለክስተቱ ዝርዝር ሁኔታ ተጨማሪ መረጃዎችን እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል። ይህ አሰቃቂ ጥቃት በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ስጋትን የፈጠረ ሲሆን፣ የጸጥታው ሁኔታም አሳሳቢ መሆኑን ያመለክታል ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።

Address


Telephone

+251948830777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Naod Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Naod Tube:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share