Wollo Addis

Wollo Addis Our Website www.wolloaddis.com

11/01/2026

የታኩር መኪና ተገዛ'' አቶ ወርቁ አይተነው ቃል በገቡት መሰረት ከዱባይ መኪናው ተገዝቶል፣ ታኩር በቅርቡም ይረከባል

''የግል ጥቅም ለማግኘት ሲባል በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የተለያዩ የጌጣጌጥ ማዕድናትና ጌጦችን በህገወጥ መንገድ ወደ ሱቅ በማስገባት እና በዶላር በመሸጥ በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያ...
11/01/2026

''የግል ጥቅም ለማግኘት ሲባል በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የተለያዩ የጌጣጌጥ ማዕድናትና ጌጦችን በህገወጥ መንገድ ወደ ሱቅ በማስገባት እና በዶላር በመሸጥ በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ያሉ የመንግስት ተቋም አመራሮችን በተመለከተ እውነተኛ ሚስጥራዊ መረጃ''

ይድረስ ለወሎ አዲስ ሚዲያ!
ባላችሁበት የአክብሮት ሠላምታችን ይድረስ
ወደ ጉዳያችን ከመግባታችን በፊት ከሁሉ አስቀድመን በተለያዩ ተቋማት በተለይም በኢትዮጵያ
ማዕድን ኮርፖሬሽን ውስጥ በበላይ አመራሩ አስተባባሪነት እየተሠሩ የሚገኙ ብልሹ አሰራሮችን
እና በግልጽ የሚሰሩ ወንጀሎችን ሚስጥራዊነቱን በጠበቀ መልኩ በፍጥነት በማጥራት እውነታው
ለህዝብ እንዲሁም ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ድረስ እንዲደርስ ሚድያው ያደረገው
አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ ወሎ አዲስ ሚድያን እኛ የተቋሙ የውስጥ ሰራተኞች እጅግ ከልብ
እናመሰግናለን ለማለት እንወዳለን፡፡

ይህንን ካልን ዘንድ የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን በተመለከተ ከዚህ ቀደም በሚዲያችሁ በዝርዝር የቀረቡት ሚስጥራዊ መረጃዎች እንደተጠበቁ ሆነው ከዚያም በተጨማሪ ሌላ አንድ አዲስ ተጨማሪ መረጃ በፖስታ መልዕክት ለሚዲያችሁ ለማድረስ ወደድን፡፡
ይህ የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነው የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን የተለያዩ የጌጣጌጥ ማዕድናትን እና ጌጦችን በማምረት ለገበያ በማቅረብ ላይ ያለ ሲሆን እነዚህን ምርቶች በአሁኑ ሰዓት በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ባለ ሱቅ በኢትዮጵያ ብር እንደዚሁም ለዚሁ ሽያጭ በሚል በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአለም አቀፍ በረራ በሚደረግበት የመንገደኞች ተርሚናል ውስጥ ደግሞ በአሜሪካ ዶላር ሽያጭ ለመፈጸም በከፍተኛ ገንዘብ ሱቅ ተከራይቶ እየሸጠ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ ከኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር ቅርርብ ያላቸው አንዳንድ የኮርፖሬሽኑ እንስት የሽያጭ ሰራተኞች ለማመን እጅግ በሚያዳግት ሁኔታ የኮርፖሬሽኑ ንብረት ከሆኑ የጌጣጌጥ ምርቶች ጋር ሌሎች የኮርፖሬሽኑ ንብረት ያልሆኑ የተለያዩ የግለሰብ ጌጣጌጦችን በፈረቃቸው ወደ ሱቁ በሚገቡበት ወቅት ተውበው የመጡ በሚመስል ሁኔታ በአንገት፣ በጣት፣ በእጅ እና በጆሯቸው ላይ በማንጠልጠል እንዲሁም ሌሎች የህገወጥ መንዶችን ተጠቅሞ ወደ
ሱቆቹ ተቀላቅለው እንዲገቡ በማድረግ በህገወጥ መንገድ በመሸጥ ላይ ይገኛሉ፡፡

የሽያጭ ሰራተኞቹ ይህንን ህገወጥ ድርጊት የሚፈጽሙት በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር
ግቢ ውስጥ በሚገኘው ሱቅ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተለይም በአሜሪካ ዶላር በሚሸጥበት በኢትዮጵያ
አየር መንገድ የመንገደኞች ተርሚናል ውስጥ ተከራይቶ በሚገኘው ሱቅ ውስጥም ጭምር ነው፡፡

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ምርቶቹ የሚሸጡት በተለየ ሁኔታ በአሜሪካ ዶላር ብቻ ሲሆን ይህንን እንደጥሩ አጋጣሚ በመጠቀምና የጥቅም ትስስር በመፍጠር በሱቁ የሚሰሩ አንዳንድ የኮርፖሬሽኑ ሴት የሽያጭ ሰራተኞች ህገወጥ ድርጊቶችን ለመፈጸም እንዲያመች ይረዳ ዘንድ የሽያጭ ሂደቱ ላይ የቁጥጥር ስርዓት ለመዘርጋት እንዲሁም የምርቶችንም ደህንነት ለመቆጣጠር ታልሞ ከዚህ ቀደም በውጭ ድርጅት በኩል በሱቁ ውስጥ ተገጥመው የነበሩ የደህንነት ካሜራዎች (security camera) የተለያዩ ሰበቦችን በመፍጠር ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆኑ በማድረግ፤
በማስከተልም የኮርፖሬሽኑ ንብረት ያልሆኑ የተለያዩ የጌጣጌጥ ምርቶችን በተለያዩ ጊዜያት በድብቅ ተመሳጥሮ በማስገባት እና በህገወጥ መንገድ ያለ ደረሰኝ በዶላር በመሸጥ ኮርፖሬሽኑን ለከፍተኛ ኪሳራ ከመጣል በተጨማሪ ሀገራችንም ከማዕድኑ ሽያጭ ማግኘት ያለባትን የውጭ ምንዛሪ ጥቅም በማሳጣት በሀገር ላይ ከፍተኛ የሚባል ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛሉ፡፡

ከዚህ ቀደም ይህ አይነቱ ህገወጥ ስራ በየሱቆቹ ውስጥ እየተሰራ በመሆኑ ህጋዊ ተጠያቂነት ያለበት
የቁጥጥር ስርዓት ይዘርጋ በሚል አንድ በተቋሙ የሚሰሩ የሽያጭ ባለሙያ ለኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ
አስፈጻሚ ሪፖርት አድርገው የነበረ ቢሆንም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ በኮርፖሬሽኑም ሆነ
በሀገር ላይ እየደረሰ ያለውን ይህንን ዝርፊያ ከማስቆም እና ይህንን ህገወጥ ድርጊት እየሰሩ ያሉ
አካላት ላይ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ከዚህ ፍጹም ተቃራኒ በሆነ መልኩ
እንስቶቹን ለምን ነካችሁብኝ በሚመስል ሁኔታ ይህንን ጥቆማ ያቀረቡትን የሽያጭ ሰራተኛ
በቅድሚያ ያላቸውን የአመት እረፍት በሙሉ ያለ ፍላጎታቸው በጉልበት እንዲወጡ (Force
Leave) በማድረግ ከዚያም ከአመት እረፍታቸው በሚመለሱበት ወቅት ደግሞ ፍጹም ሞራላቸውን
በሚነካ መልኩ ከሽያጭ የስራ ክፍል እንዲርቁ በማለም ወደ ስርዓተ ጾታ የስራ ክፍል ከተወሰኑ
ወራቶች በፊት በቀጥታ እንዲዘዋወሩ አድርገዋል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ከዚህ ቀደም ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደሚገኘው ሱቅ መደበኛ የኮርፖሬሽኑ ምርት በሚገባበት ጊዜ እንደተለመደው የኮርፖሬሽኑ ንብረት ያልሆነ ጌጣጌጥ ወደ ሱቁ በሚገባበት ጊዜ ይህ በህገወጥ መንገድ የገባ ማዕድን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ ሲደረግበት ቆይቷል፡፡

ይህ የወንጀል ምርመራ እየተደረገ ባለበት ሁኔታ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ይህ ምርት በህገወጥ መንገድ እንዲገባ ከፍተኛ ሚና የተጫወተችውን የሽያጭ ሰራተኛ ምርመራው እስኪጠናቀቅ በአሰራሩ መሠረት ከስራ እንዲታገዱ ከማድረግ ይልቅ ወደ ተቋሙ ከገባች ገና ዘጠኝ ወር አከባቢ የሚጠጋ ብቻ የስራ ልምድ ያላትን ይህችን ተጠርጣሪ የሽያጭ
ሰራተኛ ከነበረችበት ከሽያጭ ሰራተኝነት የስራ መደብ በማንሳት ከእሷ የተሻለ የትምህርት ዝግጅት እና በዘርፉ ለረጅም ዓመት በመስራት የስራ ልምድ ያካበቱ ሌሎች ባለሙያዎች በስራ ክፍሉ ውስጥ ያሉ መሆናቸው እየታወቀ ያለምንም ማስታወቂያ እና ውድድር በዋና ስራ አስፈጻሚ ትዕዛዝና የግል ፍላጎት ብቻ ላይ ተንተርሰው የስራ መደቡ የሚፈልገውን የስራ ልምድ እንደማያሟሉ እየታወቀ ለጊዜው አያስፈልግም ተብሎ ከዚህ ቀደም በኮርፖሬሽኑ የስራ አመራር ቦርድ ታምኖበት የተዘጋ የስራ መደብን በመክፈት ተጠርጣሪዋ ከሽያጭ የስራ መደብ በቀጥታ የኮርፖሬሽኑ “የማርኬቲንግ እና ብራንዲንግ ማናጀር” ሆነው ያለ አቅማቸው እና ችሎታቸው
እንዲመደቡ ያደረጉ ሲሆን ከዚያን ወቅት ጀምሮ እኚህ አዲስ የተመደቡት የስራ ክፍሉ ማናጀር
ሌሎች የሽያጭ ሰራተኞችን “ከዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር ጥብቅ ግንኙነት ስላለኝ ልክ እንደ ሌሎቹ
እንድትባረሩ አደርጋችኃለሁ” በማለት በማስፈራራት እና በዛቻ ይህ የተጀመረው የህገወጥ የማዕድን
ዝውውር እና ሽያጭ የበለጠ ተጠናክሮ እንዲጧጧፍ አድርገዋል፡፡

ምንም እንኳን ቀጥሎ የሚቀርበው ጉዳይ የግል ጉዳይ ቢሆንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ባለትዳርና
የልጆች አባት ቢሆኑም ነገር ግን ካሉበት ከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ እንዲሁም የትዳር ሁኔታ ፍጹም
በማይመጥን ሁኔታ ይህችን አዲስ ሹመኛ የስራ ኃላፊ በመዲናችን ካሉ የተለያዩ አከባቢዎች በተጨማሪ በማይመለከታት ስራ ሁሉ ለስራ ጉዳይ በሚል ወደ ክልል ባሉ የኮርፖሬሽኑ ቅርንጫፍ መ/ቤቶች ድረስ ይዘዋት በመሄድ የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች በግልጽ በሚመለከቱበት ሁኔታ አብሮ በመንቀሳቀስ ከአዲሷ የስራ ኃላፊ ጋር ያላቸውን የጠበቀ ግንኙነት ቅርንጫፍ መ/ቤት ያሉ የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞችም ጭምር እንዲያውቁት ሲጥሩ ተስተውሏል፡፡

ግለሰቧ ከዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር እጅግ የጠበቀ ግንኙነት ያላት ቢሆንም ከዚያ በተጨማሪም ዋና ስራ አስፈጻሚው በህገወጥ መንገድ ካቋቋሙት የኮርፖሬሽኑ ስትራቴጂክ ማኔጅመንት አባላት ጋር በተለይም ከዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር ጥቅምን መሠረት ያደረገ የቅርብ ወዳጅነት ካላቸው ከፋይናንስ ዳይሬክተሩ እና ከፕላንት ኦፕሬሽን ዳይሬክተሩ ጋርም እጅግ የጠበቀ ቀረቤታ ያላቸው ሲሆን ይህም ይህንን ከጊዜ ወደጊዜ በተቋሙ እየተባባሰ የመጣውን ህገወጥ የማዕድን ዝውውር እና ሽያጭ ያለማንም ከልካይ በልበሙሉነት ለማከናወን አቅም የሆናቸው ሲሆን በዚህም በአየር መንገዱ ከተከናወነ ህገወጥ የማዕድናት ሽያጭ ብቻ ግለሰቧ በአጠቃላይ ከአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ ብር (1,500,000.00ብር) በላይ ገቢ ሳያገኙ እንዳልቀረ ይገመታል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ኮርፖሬሽኑ የጌጣጌጥ ማዕድናቱን ሽያጭና ተደራሽነት እንዲኖረው በሚል በፒያሳ
አከባቢ የሚገኘውን የቀድሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ህንጻ ዜሮ ወለል ላይ በከፍተኛ ጥረትና የዋጋ ድርድር አዲስ የጌጣጌጥ መሸጫ ሱቅ ተከራይቶ የሽያጭ ስራውን ከጀመረ ከጥቂት ወራቶች በኃላ እኚህ አዲስ የስራ ኃላፊዋ ከግል ፍላጎት በመነጨ የሱቁ የውስጥ ዲዛይን ጥሩ አይደለም በማለት የሽያጩን ስራ በማስቆም በከፍተኛ ወጪ ተሰርቶ የነበረውን የሱቁ የውስጥ ዲዛይን ሙሉ በሙሉ እንዲፈርስ ያደረጉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም ሱቁ ሙሉ በሙሉ ስራ አቁሞ ሌላ ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት በአዲስ ዲዛይን እየተሰራ ያለበት ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡

በአየር መንገድ ሱቅ ካለው ህገወጥ የጌጣጌጥ ማእድናት ሽያጭ ጋር ተያይዞ እየደረሰባቸው ያለውን
ዛቻና ማስፈራሪያ በመቋቋም በዚህ ህገወጥ ስራ ላይ እየተሳተፉ የማይገኙ ሌሎች አንዳንድ የኮርፖሬሽኑ የሽያጭ ሰራተኞች ይህ ዝርፊያ ከዛሬ ነገ ይቆማል በሚል እሳቤ በትዕግስት ሲሰሩ የቆዩ ቢሆንም ይህ ከመሆን ይልቅ ዝርፊያው የበለጠ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ምክንያት አንዳንዶቹ የሽያጭ ሰራተኞች ለግል ጥቅም በሚል ይህንን ወንጀል በመፈጸም በኮርፖሬሽኑም ሆነ በሀገር ላይ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለማድረስ ከምንተባበር ይልቅ ተቋሙን መልቀቅ ይሻለናል በማለት ልክ እንደ ሌሎች የተቋሙ የቀድሞ የስራ ባልደረቦች እንዳደረጉት ሁሉ ተቋሙን በገዛ ፈቃዳቸው ለመልቀቅ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡

ከዚህ ህገወጥ የማዕድን ዝውውር እና ዝርፊያ ጋር በተያያዘ ተቋሙን በበላይነት የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከዚህ ቀደም ይህ ዝርፊያ በኮርፖሬሽኑ ሱቆች ውስጥ እየተፈጸመ መሆኑን መረጃ እንዳለውና በአፋጣኝ ማስተካከያ እና የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ ለኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጥብቅ አቅጣጫ ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ግን ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ምንም አታመጡም አይነት በሚመስል ሁኔታ ከአንዳንድ እንስት የሽያጭ ሰራተኞች ጋር ያለውን ግልጽ የጥቅም ኔትወርክ የበለጠ በማጠናከር ለዚህ ህገወጥ ስራ ያመች ዘንድ ከተቋሙ የስራ ኃላፊዎች መካከል አቅም ያላቸውን በተለይም ከማዕድናቱ ጋር
በተያያዘ የተሻለ ዕውቀት እና ልምድ ያላቸውን የተቋሙን ነባር የስራ ኃላፊዎች ከጊዜው ጋር ፈጽሞ የማይሄድ የአመራር ዘዴ በመተግበር በማንነታቸውና ሌሎች ሰበቦችን ፈልጎ ጫናዎችን አሳድሮ ከተቋሙ እንዲለቁ በማድረግ የተቋሙ ሱቆች ላይ በተለይም ያለፈው የ2017 በጀት አመት አመታዊ የሽያጭ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሽቆለቁል በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱና አሁንም እያደረሱ ሲሆን በዚህም ተቋሙን ወደ ከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ እንዲገባ ከማድረግ በተጨማሪ ሀገራችንም ከማዕድኑ ሽያጭ ማግኘት ያለባትን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በማሳጣት በሀገር ላይ እጅግ ክፉኛ የሚባል ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛሉ፡፡

በአሁኑ ሠዓት ይህ ወንጀል በተለይ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለው ሱቅ ውስጥ እየተሰራ ያለው ህገወጥ ንግድ ስራ እየተባባሰ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በተቋሙ ውስጥ ይህንን ዝርፊያ በመፈጸምና
በማስፈጸም ግንባር ቀደም በመሆን የምትሰራው ይህች ከዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር እጅግ የቀረበ
ወዳጅነት ያላት እንስት መሆኗን በተመለከተ ወሬ በከፍተኛ ሁኔታ በመሰራጨቱ ምክንያት ዋና
ስራ አስፈጻሚው ጉዳዩ ከመነሻው ገለልተኛ በሆኑና በተለይም ከከበሩ ማዕድናት ጋር በተያያዘ በቂ
እውቀትና ግንዛቤ ባላቸው አካል እንዲጣራ ከማድረግ ይልቅ ይህንን ወሬ ለማዳፈን ወይም ወንጀሉን አደባብሶ ለማለፍ በሚመስል ሁኔታ ከዋና ስራ አስፈጻሚው ጋር ግልጽ የሆነ የጥቅም ትስስር ካላቸው ሌሎች የኮርፖሬሽኑ የስራ ኃላፊዎች መካከል ከማዕድናቱ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ወይም በቂ እውቀትና ግንዛቤ የሌላቸውን ሶስቱን በመምረጥ ጉዳዩን በማጣራት ሪፖርት የሚያቀርቡ በሚል ዋና ስራ አስፈጻሚው ሰብሳቢ ጸሐፊ እና አባል በማለት በቁጥር ሶስት አባላት ያሉት አንድ የዲሲፕሊን ኮሚቴ ከሰሞኑ አዋቅረዋል፡፡

ከዚህም የኮሚቴ አወቃቀር ጋር ተያይዞ በተቋሙ ውስጥ ይህ ጉዳይ ላይ ለምን ሌሎች የስራ ክፍሎች አይሳተፉበትም ወይም በሌሎች ገለልተኛ አካላት እንዲጣራ አይደረግም የሚሉ ወሬዎች በመበራከታቸው ምክንያት ሽያጩ ህገወጥና ሰነድ አልባ የሆኑ የጌጣጌጥ ሽያጮች (ማለትም
በድብቅ እንጂ በህጋዊ መንገድ ተመዝግቦ ያልገቡና ሲሸጡም ደረሰኝ ሳይቆረጥላቸው) የተፈጸሙ
ረቂቅ ወንጀሎች እንደመሆኑ መጠን ጉዳዩ በቀጥታ በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንዲመረመር ከማድረግ ይልቅ ግኝቱ ተጨባጭ በሆነ መልኩ በውስጥ ኦዲት ምርመራ የማይገኝ መሆኑ እየታወቀ የሽያጩን ሁኔታ ኦዲትም እያስደረግን ነው ለማለት በሚያስመስል ሁኔታ ከዲሲፕሊኑ ኮሚቴ ስራ ጎን ለጎን ከጌጣጌጥ ማዕድናቱ አመታዊ ቆጠራ ጋር ተያይዞ እንኳን ከዚህ ቀደም በደረሰበት ጫና ምክንያት በቂ እና ተጨባጭ የሆነ ወቅታዊ መረጃም ሆነ ማስረጃ የሌለውን የኮርፖሬሽኑ የውስጥ ኦዲት የስራ ክፍልም የራሱን ምርመራ እንዲያደርግ በሚል በዋና ስራ አስፈጻሚ አቅጣጫ ተሰጥቶበት ከመደበኛው የኦዲት ምርመራ አሠራር ውጭ በሆነ ሁኔታ ከሰነድ ይልቅ የሽያጭ ሰራተኞችን ቃለመጠይቅ በማድረግ የሚገኝ መረጃን መሠረት ያደረገ የይስሙላ
የኦዲት ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል፡፡

ከዚህ ቀደም ለሚዲያችሁ በተላከው ጥቆማ ለመግለጽ እንደተሞከረው ዋና ስራ አስፈጻሚው ወደ
ተቋሙ ከመጡ ገና አንድ አመት እንኳን ሳይሞላቸው በመንግስት የተሠጣቸውን ከፍተኛ ኃላፊነትና አደራ ወደ ጎን በመተው ሪፎርም በሚል ሰበብ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ማንነትን መሠረት ያደረገ የጥቅም ኔትወርክ በመዘርጋት ራሳቸው ካቋቋሟቸው የስራቴጂክ ማኔጅመንት አባላት ጋር በመመሳጠር (both Reciprocal & Entitlement nepotism የሚባሉትን ከፍተኛ የሙስና ወንጀሎች በመፈጸም) ይህንን ጨምሮ ለመቀበል የሚከብዱ ነገር ግን በግልጽ የተፈጸሙ ሌሎች በርካታ የሙስና ስራዎችን እና ህገወጥ አሰራሮችን ሲፈጽሙ እና ሲያስፈጽሙ በመቆየታቸው በአሁኑ ሰዓት ተቋሙን ወደባሰ ኪሳራና አዘቅት ውስጥ በመክተት በከፍተኛ ሁኔታ ዋጋ እያስከፈለ ይገኛል፡፡

ተቋሙን በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስም ይህንን በሀገርና
በመንግስት ሀብት ላይ ጉዳት እያደረሱ ያሉ አካላትን ሌሎች በስሩ ያሉ ተቋማት ላይ እንዳደረገው ሁሉ ከኃላፊነታቸው በማንሳት በህግ እንዲጠየቁ ከማድረግ ይልቅ ኮርፖሬሽኑ በየወቅቱ የሚያቀርብለትን የሀሰት የፋይናንስ ሪፖርት በመመልከት ጉዳዩን በቸልተኝነት እየተመለከተው ይገኛል፡፡ ይህም ማለት ተቋሙ ባለፈው 2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ ከሀምሳ አምስት ሚሊዩን ብር (ብር 55,000,000.00) በላይ አመታዊ ኪሳራ ያስመዘገበ ሲሆን ከኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋር የጥቅም ወዳጅነት ያላቸው የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ እንዲሁም በጥቅም ጥስስር ምክንያት ወደ ኮርፖሬሽኑ የመጡት ከላይ የተገለጹት የስትራቴጂክ እና ኢንቨስትመንት
ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት በጋራ ተመሳጥረው ይህ ትክክለኛ መረጃ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንዲደበቅ በማድረግ ተቋሙ ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተደረገ ካለው ሪፎርም ጋር ተያይዞ ከፍተኛ አወንታዊ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ለማስመሰል ከሶስት ሚልዩን ብር በላይ ትርፍ እንደተመዘገበ ተደርጎ ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሀሰት ሪፖርት እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ባለንበት የ2018 በጀት አመትም ኮርፖሬሽኑ ተሰማርቶ እየሰራ ያለውን በየዘርፉ ያለው ያለፈውን ስድስት ወራት ከዕቅድ አንጻር ያለው አፈጻጸም ሲታይ
እጅግ ዝቅተኛና ተቋሙ ከማንሰራራት ይልቅ የቁልቁለት ጉዞውን ከምን ጊዜውም በላይ በከፍተኛ
ፍጥነት እየተጓዘ መሆኑን ያሳያል፡፡

በተቋሙ ውስጥ ያለው አጠቃላይ ወንጀል እና ለመግለጽ የሚከብድ ብልሹ አሰራር በተለያዩ
ሚዲያዎች ከመጋለጡ ጋር በተያያዘ ሰሞኑን ሁላችንም የተቋሙ ሰራተኞች በተገኘንበት አጠቃላይ
የሰራተኞች ስብሰባ የተደረገ ሲሆን በስብሰባው ላይም ምንም እንኳን ሪፎርም በሚል ሽፋን
እርሳቸው በህገወጥ መንገድ በትውውቅና በዝምድና የቀጠሯቸው የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም
በጥቅም እና በማንነት የተሳሰሩ የስትራቴጂክ ማኔጅመንት አባላት በተቋሙ ውስጥ እየተከናወነ
ያለውን ግልጽ ወንጀል እና አድሏዊ አሠራር አደባብሰው ለማለፍ ቢሞክሩም ነገር ግን ዋና ስራ
አስፈጻሚው ይህ ሁሉ ስህተት የመጣው ከዚህ ቀደም ምንም አይነት የመንግስት ተቋም መርተው
ባለማወቃቸው የመጣ መሆኑን በራሳቸው አንደበት ተናግረው ያመኑ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ
በእርሳቸው ኔትወርክ ውስጥ ያልታቀፉ ሰራተኞችም በዘርፉ ስራ አቅም የነበራቸውን የተቋሙ ነባር
ሰራተኞች በተለይም የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ላይ ጫና በማሳደር እንዲወጡ ካደረጉ በኃላ
በአብዛኛው አቅምና ችሎታ የሌላቸው ነገር ግን እንዲያማክሯቸውና በተቋሙ ውስጥ ያለ ማንም
ከልካይ በበላይነት እንደፈለጉ እንዲወስኑ የመረጧቸው ጥቂት ሰዎችን በዙሪያቸው በመሰብሰብ
የመሰረቱት ይህንን ግልጽ የሆነ ጥቅም እና ማንነትን መሠረት ያደረገ ኔትወርክ እስካልበጠሱ
ድረስ ተቋሙን ወደባሰ አዘቅት ውስጥ መክተት እንጂ የተሻለ ለውጥ እንደማይመጣ ገለልተኛ
በሆኑ የተቋሙ ሰራተኞች በስብሰባው ወቅት ተነግሯል፡፡
ስለሆነም ከዚህ ቀደም በሚዲያው በኩል ለመግለጽ እንደተሞከረው ይህ በዋና ስራ አስፈጻሚ የሚመራው
በተቋሙ ውስጥ በበላይነት ተቀምጦ ፈላጭ ቆራጭ የሆነው ህገወጥ የስትራቴጂክ ማኔጅመንት አባላት
በተቋሙ ውስጥ በቆዩ ቁጥር በተቋሙም ሆነ በሀገር ላይ እያደረሱ ያለው ችግር እጅግ እየተባባሰ
በመሆኑና ይህ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ለሚመለከታቸው ለተለያዩ የመንግስት አካላት በተለይም
ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) ላሉ የበላይ አመራሮችና ኮርፖሬሽኑን በቅርበት
ለሚከታተለው ዲፓርትመንት (ፖርትፎሊዮ) በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ አካላት በተደጋጋሚ ቢነገርም
ነገር ግን EIH የመንግስትን ከፍተኛ ሀብት እንደሚያስተዳድር ተቋም የደረሱትን የተለያዩ ጥቆማዎች
ተንተርሶ በፍጥነት ተገቢውን የማጣራት ስራ በማከናወን ዋና ስራ አስፈጻሚውን ጨምሮ ይህንን
ወንጀል እየሰሩ ያሉትን የኮርፖሬሽኑ ስትራቴጂክ አባላት ከኃላፊነታቸው በፍጥነት እንዲነሱና በህግ
እንዲጠየቁ ከማድረግ ይልቅ የደረሱትን ጥቆማዎች በቸልተኝነት ተመልክቶ አሁን ላይ የኮርፖሬሽኑ
ህልውና እጅግ አደጋ ላይ ወድቆ ለእኛ ለሰራተኞቹ ወርሀዊ ደሞዝ እንኳን በአግባቡ መክፈል
የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ተቋሙን ከመፍረስ ለመታደግና የበላይ አመራሩን
ጨምሮ ከተጠያቂነት ለማምለጥ በማለም በመንግስት መዋቅር ውስጥ በመደበቅ (የብልጽግና ፓርቲ
አባል በመሆን) ይህ ጉዳት እንዲደርስ በተለያየ መንገድ ድጋፍ የሠጡት የኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ
የስትራቴጂክ ማኔጅመንት አባላት መንግስት አሁን ላይ በሌሎች ተቋማት ላይ መሰል ወንጀል እየሰሩ
ያሉ አካላትን አድኖ በመያዝ በህግ እንዲጠየቁ እያደረገ እንደመሆኑ መጠን በኮርፖሬሽኑም
ስልጣናቸውን እንደ ጥሩ መሳሪያ በመጠቀም መንግስት የሠጣቸውን ተልዕኮና ከፍተኛ አደራ ወደ ጎን
በመተው የግል ጥቅማቸውን እያካበቱ ያሉት እነዚህ ጥቂት የስራ ኃላፊዎች በተቻለ ፍጥነት
ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ እና በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ ሲባል ጉዳዩ በሚዲያችሁ በኩል
ለህዝብ እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮን ጨምሮ ለሌሎች የመንግስት አካላትም በተቻለ ፍጥነት
እንዲደርስ አስበን በዝርዝር አቅርበናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮርፖሬሽኑ አመራሮች በተለያዩ ሚዲያዎች የቀረቡትን ጥቆማዎች እንደ
ጥሩ ግብዓት ተጠቅሞ ነገሮችን በማስተካከል ተቋሙ ከገባበት አዘቅት ተስፈንጥሮ በመውጣት
እንዲያንሰራራ ጥረት ከማድረግ ይልቅ እኛ ይህንን ጥቆማ በመስጠት እያጋለጥን ያለን ሰራተኞችን
ማንነታችንን በማወቅ ልክ ሌሎች የተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ላይ እንዳደረጉት ሁሉ የተለያዩ
ጫናዎችን በማሳደር ከስራ እስከማባረር የሚደርስ እርምጃን ለመውሰድ ዋና ስራ አስፈጻሚን
ጨምሮ የስትራቴጂክ ማኔጅመንት አባላቱ በተለያየ መንገድ ለማወቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን
ስለደረስንበት እኛ ጥቆማ አቅራቢ የሆንን የውስጥ ሰራተኞች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጫናዎች ሳቢያ
ከተቋሙ እንዲወጡ እንደተደረጉት ልክ እንደ ሌሎቹ የስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ከስራችን
በመባረር ቤተሰባችንን ችግር ውስጥ መክተት የማንፈልግ በመሆኑ ሚዲያው እኛ ይህንን ጥቆማ
እያቀረብን ያለነው የኮርፖሬሽኑ የውስጥ ሰራተኞች ወንጀለኞች ለህግ እንዲቀርቡና ተቋሙን
ከመፈረስ ለማዳን ካለን ጥልቅ ፍላጎት የዘለለ ሌላ ምንም አይነት ፍላጎት የሌለን መሆኑን ተገንዝቦ
በተለመደው ሁኔታ ሚስጥራዊነቱን እንዲጠብቅልን ስንል በታላቅ ትህትና ሚዲያውን
እንጠይቃለን፡፡
ወሎ አዲስ ሚዲያ ሀገር ወዳድ እና ለእውነት የቆመ ሚዲያ እንደመሆኑ መጠን ልክ ከሰሞኑ
በመንግስት እና በሀገር ሀብት እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱ የነበሩ ሌሎች የመንግስት
አመራሮችን በማጋለጥ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱና በህግም እንዲጠየቁ እንደተደረገ ሁሉ መንግስት
በአሁኑ ሰዓት ከማዕድን ዘርፉ ከፍተኛ ገቢ ለማግኘት ከየትኛውም ጊዜ በላይ ከፍተኛ ሩጫና
ንቅናቄ እያደረገ ባለበት በዚህ ጊዜ ላይ እንደ መንግስት ተቋም ግንባር ቀደም ሆኖ ከመንግስት ጎን
በመቆም ይህንን ስትራቴጂክ እቅድ እውን ከማድረግ ይልቅ በኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን
ውስጥ ያለውም ሁኔታ እጅግ አሳሳቢና ተቋሙ የጥቂት ግለሰቦች እንጂ እውን የፌዴራል መንግስት
ተቋም የማይመስልበት ደረጃና ቁመና ላይ የደረሰ በመሆኑ ይህ ጊዜ ሊሠጠው የማይገባ ጉዳይ
በሚዲያው በኩል በተለመደው ሁኔታ ሚስጥራዊነቱን በጠበቀ መልኩ በተቻለ ፍጥነት አየር ላይ በማዋል እነዚህ በመንግስት ተቋም ውስጥ ለግል ጥቅማቸው በመሮጥ በሀገር ላይ ላደረሱት ከፍተኛ ኪሳራ በህግ እንዲጠየቁ በማድረግ የተለመደውን ሀገርን እና ተቋማትን ከጥፋት የመታደጉን ስራ እንዲቀጥል ስንል በታላቅ አክብሮት እና ትህትና የተለመደ ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡

ለእውነትና ለእውነት ብቻ የቆመው ወሎ አዲስ ሚዲያ ሀገርን ከጥፋት የማዳን ጉዳይን ከምንም በላይ በማስቀደም በተለመደው መልኩ ድምጽ ስለሚሆነን እና ወንጀለኞችን በማጋለጥ ለሀገር ስለሚያደርገው ቀና ትብብር በድጋሚ እጅግ ከልብ እናመሰግናለን እያልን ለዘገባው ያመች ዘንድ እና የዘገባው አካል እንዲሆን በሚል የኮርፖሬሽኑ ሎጎ ቀጥሎ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የውስጥ ሰራተኞች ከማይነበብ ፊርማ ጋር

ግልባጭ ይድረስ

ለፌዴራል የስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን (በፖስታ ቤት የሚላክ)

''ምን አስባ ነው ጅቡቲ የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን በአንድ ሶፋ ላይ አጭቃ ያስቀመጠችው''ይህ የሆነው ሶፋ አጥታ ሳይሆን የኢትዮ-ጅቡቲ የዲፕሎማሲ ኩስምናን ለማሳየትና ግንኙነቱ እየጠበበ መምጣ...
11/01/2026

''ምን አስባ ነው ጅቡቲ የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን በአንድ ሶፋ ላይ አጭቃ ያስቀመጠችው''

ይህ የሆነው ሶፋ አጥታ ሳይሆን የኢትዮ-ጅቡቲ የዲፕሎማሲ ኩስምናን ለማሳየትና ግንኙነቱ እየጠበበ መምጣቱን ለማስረዳት ሆን ተብሎ የተሸረበ ሴራ ነው።

11/01/2026

ሙስሊሙ፣ ፔጤ ው፣ኦርቶዶክሱ ጭምር ጠላት ሆኑብኝ'' ይህ ነው ከሀገር እንድወጣ ያደረገኝ ''ያያ ዘልደታ'' በአርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ ምክንያት ትዳሬን አጣሁ

''እናት ጎንደር ትጥራለች...............''በሚስጥራዊ ተራራዎች የተጋረደችዉ  የፀናችዉ፣ በፋሲል አብያተ መንግሥታት ግብረ ህንፃዎች የደመቀችዉ ለ300 ዓመታት ያኽል ኖረው ያለፉባትን...
10/01/2026

''እናት ጎንደር ትጥራለች...............''

በሚስጥራዊ ተራራዎች የተጋረደችዉ የፀናችዉ፣ በፋሲል አብያተ መንግሥታት ግብረ ህንፃዎች የደመቀችዉ ለ300 ዓመታት ያኽል ኖረው ያለፉባትን የ28 ነገሥታቷን አያና ከትላንት ታሪክ እየቀዳች ዘመንን አዘምና ከፍ ብላ የተቀመጠችዉ ።

በቀዳሚና ዘመናዊ አስተዳደር በኢኮኖሚ መሰረትነቷ የስነ ጥበብ፣ የትምህርት ባበከረከተችዉ አስተዋጽኦ እና ታሪክ እምብርትነቷ የከተሞች እናት እስከመባል የደረሰች

በጃንተከል ዋርካ ሥር በፍቅር የተጠለለችዉ በቃል ኪዳን የፀናችዉ ፈትፍቶ የሚያጎርስ አውልቆ የሚያለብስ መከራን አሻግሮ ከደስታ የሚያደርስ እንግዳ ተቀባይ ሕዝብ ያለባት-ጎንደር ።

ለጥምቀት የሚመጡ እንግዶቿን ለመቀበል ሽር ጉድ እያለች ነዉ ።

እርስዎም ለጥምቀት ወደ ታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ጎራ በማለት እና የ ጥምቀት በዓል በጎንደር በመታደም ከጃን ተከል ዋርካ ስር ፍቅር ። ከአርባ አራቱ አድባራት እንደጅረት የሚፈሰዉ ጥኡመ ዜማ ቅኔ አቋቀም ድጓና የትርጓሜ ሚስጥር በረከት እየተቋደሱ አብረዉን እንዲጠመቁ በረከት እንዲያገኙ ተመርጠዋል ።

እግረ መንገድዎን የመኻከለኛውን ዘመን ኢትዮጵያውያን ደርሰዉበት የነበረዉን የስልጣኔ ጥግ አለም በአንድ ቃል ተስማምቶ '' የመናገሻ ከተማነት" ክብርን የሰጠበትን ሚስጥር የጋራ ታሪካችን መገለጫ የሆኑትን በአፍሪካ አስደናቂ የምህንድስና የእምነት የትምህርትና የፍልስፍና ዉጤቶችን በዓይንዎት ተመልክተዉ የአባቶቻችን የሥልጣኔ አሻራዎች እፁብ ድንቅ ኪነ-ሕንፃ፣ ኪነ-ጥበብ፣ እደ-ጥበብ፣ ስነ ስዕል ትሩፋቶች በእጅዎት እየዳሰሱ ሃሴት ያድርጉ ።

በመላው አለም የምትገኙ ዉድ የሃገሬ ልጆች ዘንድሮ
ጥምቀትን በመማፀኛዋ ከተማ በማሳለፍ
ከገነት አቡነአረጋዊና ፣ ገለዓድ፣ቀራኒዮ ፣ ወንፊት ፣ ተራሮች ነብስ አዳሽ ንጹሕ አየርን እየማጉ ታሪክን ባህልን ኪነጥብን ስልጣኔን እየቃኙ በውበታቸዉ እንዲገረሙ ተማርከው መንፈስዎትን በደስታ እንዲሞሉ በሞቴ አፈርስሆን እያለ ከሚያጎርሰዉ እንግዳ ተቀባዩ ህዝቧ ከእልፈኞቿ ወተት ጠጅና ማር በረከቶች ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ ።

◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
Gondaritti cuuphaa irratti argamuun eebbadha

Gaarreen dhoksaadhaan marfamtee jirti, jabaadha, gamoowwan ijaarsaa bataskaanota Faasiliin calaqqisa.
Waggaa 300 kan jiraatte Ayyaana mootota 28 darban arge, ol taa'ee seenaa kaleessaa deebisee horsiisaa jira.

Bulchiinsa jalqabaa fi ammayyaa, bu’uura dinagdee ishee irraa kan ka’e gumaacha aartii, barnootaa fi seenaa keessatti qabduun haadha magaalotaa jedhamuun beekamti.

Jantekel Warka jalatti jaalalaan gaaddisa godhate, waadaa irratti jabaate, uffata hiikuu, uffata hiikuu, uffata hiikuu, ummata simannaa rakkina mo'atee gammachuu fidu qabaachuu - Gondar.

Keessummoonni ishee cuuphaaf akka dhufan eegaa jirti.

Akkasumas cuuphaaf gara magaalaa seena qabeettii Gondar deemtee sirna cuuphaa Gondar, waldoota afurtamii afur Jaalalli Jaalalli itti yaa'u Jan Tekel Warka jalatti yaa'u keessaa tokko taate irratti hirmaatte.
Faaruun akka sululaatti yaa'u, walaloo akka sululaatti yaa'u, boolla bishaanii uumuu fi eebba iccitii hiikkaa, akka waliin cuuphamtanii fi karaa keessan irratti, golee qaroomina Habashoonni ga'an keessa bara giddu galeessaa, addunyaan jecha tokkoon walii galti, "Icciitii magaalaa Menageshaaf ulfina kenne."
Bu’aa ba’ii ajaa’ibaa injinariingii, amantii, barnootaa fi falaasama Afrikaa keessatti mul’ata seenaa waloo keenyaa ta’an ija keessaniin ilaalaa.
Dhaala ijaarsa ajaa'ibaa, aartii, hojii harkaa fi fakkii qaroomina abbootii keenyaa dhaga'aa.

Bara kana lammii koo kan addunyaa mara irra jirtan
Cuuphaa magaalaa iyyataa keessatti dabarsuudhaan
Kegent Abunearegawina: Gilead: Calvary: Wenfit: Gaarreen, Nebs, qilleensa qulqulluu, seenaa fi aadaa gammachuu.
Qaroomina qorachuu fi bareedina isaa ajaa'ibsiifachuuf
Hafuura kee gammachuudhaan guutuu baradhu
Namoonni keessummoota simatan eebba aannan, wayinii fi damma keessummeessitoota ishee irraa argamu akka hirmaatan afeeraa jira.

◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

ኣብ ጎንደር ኣብ ጥምቀት ምክፋል በረኸት እዩ።

ብሚስጢራዊ ኣኽራናት ዝተኸበበት እያ፣ ድልዱል እያ፣ ብናይ ፋሲል ኣብያተ ክርስቲያናት ስነ ህንፃ ህንፃታት ጐሊሑ ይርአ።
300 ዓመት ዝነብር ዝነበረ ኣያና ነቶም ዝሓለፉ 28 ነገስታት ርእያ፡ ልዕል ኢሎም ኮፍ ኢሎም ናይ ትማሊ ታሪኽ ይደግሙ ኣለዉ።

ብሰንኪ ቀዳሞትን ዘመናውን ምሕደራኣ፡ ቁጠባዊ መሰረታ ኣብ ስነ-ጥበብ፡ ትምህርትን ታሪኽን ብዘለዋ ኣበርክቶ ኣደ ከተማታት ተባሂላ ትፍለጥ።

ኣብ ትሕቲ ጃንተከል ዋርካ፡ ብፍቕሪ ተዓቚቡ፡ ኣብ መብጽዓ ጸኒዑ፡ ክዳኑ ቀንጢጡ፡ ክዳኑ ቀንጢጡ፡ ክዳኑ ዝቕንጥጥ፡ ንጸገማት ሰጊሩ ሓጎስ ዘምጽእ ተቐባሊ ህዝቢ ምህላው - ጎንደር።

ኣጋይሻ ንጥምቀት ክመጹ ትጽበ ኣላ።

ንጥምቀት ናብ ታሪኻዊት ከተማ ጎንደር እውን ከይድካ ኣብ ትሕቲ ጃን ተከል ዋርካ ካብተን ፍቅሪ ዝውሕዝ ኣርብዓን ኣርባዕተን ሰበኻታት ሓንቲ ዝኾነት ጎንደር ኣብ ዝተኻየደ ስነ-ስርዓት ጥምቀት ተሳቲፍካ።

እቲ ከም ወሓዚ ዝውሕዝ ዜማ፡ እቲ ከም ወሓዚ ዝውሕዝ ግጥሚ፡ ዒላን በረኸት ምስጢር ትርጉምን ምፍጣር፡ ሓቢርኩምን ኣብ መንገድኹምን ምእንቲ ክትጥመቑ፡ ኩርናዕ ስልጣነ ኢትዮጵያውያን ኣብ... ኣብ ማእከላይ ዘመን፡ ዓለም ብሓንቲ ቃል ትሰማማዕ፡ "ንከተማ መንገሻ ክብሪ ዝሃበ ምስጢር"።

ኣብ ኣፍሪቃ መግለጺ ሓባራዊ ታሪኽና ዝኾኑ ኣገረምቲ ዓወታት ምህንድስና፣ እምነት፣ ትምህርትን ፍልስፍናን ብዓይንኹም ርኣዩ። ድንቂ ስነ ህንጻ፡ ስነ-ጥበብ፡ ስነ-ጥበብን ቅብኣን ውርሻታት ስልጣነ ኣቦታትና ይስመዓኩም።

ሎሚ ዓመት ኣብ መላእ ዓለም ዘለኹም ደቂ ዓደይ
ጥምቀት ኣብ ከተማ ጠበቓ ብምሕላፍ
ቀገንት ኣቡነኣረጋዊና፡ ጊልዓድ፡ ቀራንዮ፡ ወንፊት፡ ኣኽራን፡ ነብስ፡ ንጹህ ኣየር፡ ታሪኽን ባህልን እናስተማቐርካ።

ስልጣነ ንምድህሳስን ብጽባቐኡ ንምግረምን። ንመንፈስካ ብሓጐስ ምምላእ ተማሃር ነቶም ተቐበልቲ ኣጋይሽ ካብ ኣአንገድታ ዝመጽእ በረኸት ጸባን ወይንን መዓርን ክካፈሉ እዕድም ኣለኹ።

Via- ታዴ የማመይ ልጅ

10/01/2026

''መሬት ላይ መቆም የአውሮፕላን ተፈጥሮ አይደለም'' ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በቢሾፍቱ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ያስተላለፉት መልዕክት መነጋገሪያ ሆኗል ያድምጡት

''የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የትውልዱ ወሳኝ የቤት ሥራ ነው !'' ፕሮፌሰር አደም ካሚልየኢትዮጵያን ከፍተኛ እና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ አስተማማኝ የባሕር በር...
10/01/2026

''የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የትውልዱ ወሳኝ የቤት ሥራ ነው !'' ፕሮፌሰር አደም ካሚል

የኢትዮጵያን ከፍተኛ እና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ የአሁኑ ትውልድ ወሳኝ የቤት ሥራ መሆኑን ተናግረዋል። በቀይ ባሕር ነባራዊ እውነታ ውስጥ ኢትዮጵያ የነበራትን ከፍተኛ ቦታ ያጣችው የህዝብ ውክልናን ችላ በማለት በተሰጠ የተሳሳተ ውሳኔ እና ሸፍጥ መሆኑ ይታወቃል።

ኢትዮጵያ በተሸረበባት ታሪካዊ ሸፍጥ የባሕር በሯን በማጣቷ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በሌሎች ሀገራት ወደብ ላይ ጥገኛ እንድትሆን ተገዳለች፣ ይህ ደግሞ በኢኮኖሚ ዕድገቷና በሉዓላዊነቷ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል።

የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የስልጣኔ ኃያልነት ከቀይ ባሕርና ዓባይ ወንዝ ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው። የውስጥ ባንዳዎችና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች በሸረቡት ሴራ ኢትዮጵያ ከስልጣኔዋ ጋር ጥብቅ ቁርኝት ካለው አስተማማኝ የባሕር በሯ እንድትገለል መደረጉን አስታውሰዋል።

የኢትዮጵያን ከፍተኛ የህዝብ ቁጥርና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የአሁኑ ትውልድ ወሳኝ የቤት ሥራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይና ትራንዚት ከምታወጣው ገንዘብ ባለፈ በወጪና ገቢ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ በማድረግ ዓለም አቀፍ የንግድ ተወዳዳሪነትን እያቀጨጨ መሆኑን ገልጸዋል።

የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ የሎጀስቲክስ ዘርፍ የኢኮኖሚ ስብራትን በዘላቂነት የሚጠግን ወሳኝ የዲፕሎማሲ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ጉዳይ ለዚህ ትውልድ ብቻ የሰጡት ይመስላል!

ሀሳብዎን ያካፍሉን?

ይህን ያዉቃሉ ''ማን ስለሆነ ነዉ መኪና የሚገባዉ ለምትሉ!'' ሀገሩን በአለም አደባባይ ያስጠራና ያላከበርነዉ አርቲስት ሱራፌል ተካ አንድ አርቲስት ማሳካት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ ሽልማቶች መካ...
09/01/2026

ይህን ያዉቃሉ ''ማን ስለሆነ ነዉ መኪና የሚገባዉ ለምትሉ!'' ሀገሩን በአለም አደባባይ ያስጠራና ያላከበርነዉ አርቲስት ሱራፌል ተካ

አንድ አርቲስት ማሳካት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ ሽልማቶች መካከል ከኦስካር በመቀጠል የገነነ ስምና ዝና ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃ የፊልም ፌስቲቫል ነዉ በ1972 የተጀመረው የካንስ የፊልም ፌስቲቫል

በዚህ የፊልም ፌስቲቫል ላይ እንደ ሰርጂዮ ሊዮን፣ ቴዎ አንጀሎፖሎስ፣ በርትራንድ ታቨርኒየር፣ ፒተር ግሪንዌይ፣ ኤቶሬ ስኮላ፣ የታቪያኒ ወንድሞች፣ ኒኪታ ሚካልኮቭ፣ ዉዲ አለን፣ ዣን-ሉክ ጎዳርድ፣ በርናርዶ ቤርቶሉቺ፣ ሚሎስ ፎርማን፣ ፍራንቼስኮ ሮሲ፣ ጆን ሁስተን፣ አንድሬጅ ዋጅዳ፣ ጄምስ አይቮሪ፣ አንድሬይ ታርኮቭስኪ፣ ኬን ሎአች፣ አንድሬጅ ዙላውስኪ፣ አንድሬጅ ዋጅዳ እና ካጌሙሻ አላይን ኮርኖ፣ አንድሬ ቴቺኔ፣ እስጢፋኖስ ፍሬርስ፣ ሊዮስ ካራክስ፣ ላርስ ቮን ትሪየር፣ ስፓይክ ሊ፣ ጂም ጃርሙሽ እና ኤሚር ኩስቱሪካ ያሉ ግዙፍ የጥበብ ሰዎችን በክብር የሸለመ ነዉ።

በዚህ ከአራቱም የዓለም ማዕዘኖች የተውጣጡ ፊልሞች ባለሙያዎች ተዋናዮችን በማወዳደር ለሽልማት የሚያበቃ የምድሪቱ ቁጥር ሁለት የሽልማት መድረክ ኢትዮጵያ ሁለት ጊዜ በእጩነት የቀረበች ሲሆን ላምብ እና አላዛር የተባሉ ፊልሞች በእጩነት ቀርበዋል ።

በእነዚህ ሁለት እጩ የሆኑ ፊልሞችን በተዋናይነት የተሳተፈ ሰዉ ማን ነዉ ካላችሁ አርቲስት ሱራፌል ተካ ብቻና ብቻ ነዉ ።

በ21ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በዓለም ላይ ቀዳሚ የሲኒማ ዝግጅት የሆነዉ ፌስቲቫሉ እንደ ፊሊፒንስ፣ ቻይና፣ ኩባ፣ አውስትራሊያ፣ ህንድ፣ ኒውዚላንድ እና አርጀንቲና ፌልሞች ጋር ለመወዳደር ከአፍሪካ ከተመረጡ መካከል የ35 ደቂቃ ቆይታ ያለዉ በሰሜኑ ኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍል የተሰራው ላምብ የተባለ ዶክመንተሪ ፊልምና በ2025 ከሁለት ሽህ በአለምአቀፋ ከተሰሩ ፌልሞች መካከል ተወዳድሮ ለእጩነት የቀረበው አላዛር ፊልም ይጠቀሳሉ ።

በእነዚህ ሁለቱ ፊልሞች ላይም አርቲስት ሱራፌል ተካ በመሪ ተዋናይነት የተወነ ሲሆን
ፊልሙ ‘የዳካር ኮርት’ የ2025 ዓለም አቀፍ የአጭር ፊልም ፌስቲቫልግራንድ ፕሪ ሽልማት አሸናፊ መሆን ችሏል ።

ለ36 ደቂቃዎች የሚዘልቀው “አላዛር” ፊልም፣ ለምርጥ ዳይሬክተር የሚሰጠውን “አባባካር ሳም ማክሃራም” የተሰኘውን አለምአቀፋዊ ሽልማት ያሸነፈ የኢትዮጵያን ስም በአለም አደባባይ ያስጠራ ቢሆንም አትሌት አይደለምና አርቲስት ሱራፌል የሚገባውን ክብር በሀገርአቀፍ ደረጃ ሳይሰጠዉ ታክሲ ለመያዝ ሲጋፋ ሞልቷል ተብሎ ሲመለስ መታየቱ በሀገሪቱ ገፅ ላይ የታየ አሳዛኝ ክስተት ነበር ።

ከታዴ የማመይ ልጅ የተወሰደ

ተሳክቷል የተሳተፋችሁ በሙሉ ክብር ይገባችሗልPopular Electronics 1M Followers ገብቷል
09/01/2026

ተሳክቷል የተሳተፋችሁ በሙሉ ክብር ይገባችሗል
Popular Electronics 1M Followers ገብቷል

 #እባካችሁ  #ሸር ''ሰው አክባሪው አርቲስት ሱራፌል ተካ መኪናው ይገባዋል!'' ቻሌንጁን ተቀላቀሉ በአሁኑ ሰአት Popular Electronics ከ982ሽህ Followers በላይ ተሻግረዋል...
09/01/2026

#እባካችሁ #ሸር ''ሰው አክባሪው አርቲስት ሱራፌል ተካ መኪናው ይገባዋል!'' ቻሌንጁን ተቀላቀሉ በአሁኑ ሰአት Popular Electronics ከ982ሽህ Followers በላይ ተሻግረዋል

ጉዞ 1ሚሊዮን የPopular Electronics ቲክቶክ ሊንክ ተያይዟል'' ተጭነው Follow ያድርጉ https://www.tiktok.com/.electronics?_r=1&_t=ZS-92qoYhltmSd

Full Time ''Arsenal 0-0 Liverpool'' ተጠናቋልየአርሰናል የዋንጫ ግስጋሴ ሊቨርፑል አሰናክሎታል
08/01/2026

Full Time ''Arsenal 0-0 Liverpool'' ተጠናቋል
የአርሰናል የዋንጫ ግስጋሴ ሊቨርፑል አሰናክሎታል

የመጀመሪያ አጋማሽ Arsenal 0-0 Liverpool
08/01/2026

የመጀመሪያ አጋማሽ Arsenal 0-0 Liverpool

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo Addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wollo Addis:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share