
14/07/2025
የሩሲያ ጦር በምስራቃዊ ዩክሬይን ዳኔስክ ግዛት በኩል ወደ ድኔፕሮ ፔትሮቭስክ ግዛት እየተጠጋሁ ነው አለ
ጦሩ በሁለቱ ግዛቶች ወሰን ላይ የሚገኘውን ማይረን የተባለ አካባቢ መያዙን እወቁልኝ ማለቱን AFP ፅፏል፡፡
ጦሩ የዩክሬይንን ሰራዊት መከላከያ ሰብሬበታለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡
ከቅርብ ወራት ወዲህ የሩሲያ ጦር ከሚፈፅመው የሚሳየል እና የድሮን ጥቃት በተጨማሪ በምስራቃዊ ዩክሬይን የተለያዩ ስፍራዎች ወደፊት እየገፋ ነው ተብሏል፡፡
አሜሪካ በዩክሬይን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አጠቃላይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ብትጠይቅም በሩሲያ በኩል ጥያቄው ተቀባይት እንዳላገኘ ይነገራል፡፡
የዩክይሬኑ ጦርነት ከ3 ዓመት ከ4 ወራት በላይ ሆኖታል፡፡
ተጨማሪ መረጃ👇
Telegram
https://t.me/+51TfVkc9GNI4NWU0
https://t.me/R51TfVkc9GNI4NWU0