Hair loss regeneration

Hair loss regeneration all time GOD is good

15/04/2025

hdfhdj

‼  #የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰዓት እላፊ ይፋ አድረጓል ‼የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች...
17/11/2021

‼ #የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰዓት እላፊ ይፋ አድረጓል ‼

የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሰረት ፦

1ኛ. ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ከጎንና ጎን ያለበሱትን ሸራ በማንሳትና ሶስት ሰው ብቻ በመጫን እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት ፣ የህዝብ ትራንስፖርትና ታክሲዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 2 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።

2ኛ. መታወቂያን በተመለከተ ፦ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ሀላፊዎች መታወቂያ መስጠት የማይችሉና ማንነቱን የሚገልፅ መረጃ በመያዝ ግለሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ጊዜያዊ መታወቂያ ማግኘት ይችላሉ።

3ኛ. ከጦር መሳሪያ ጋር በተያያዘ፦ ከዚህ ቀደም ያስመዘገበም ያላስመዘገበም ከነገ ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያው በሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ማስመዝገብና የፈቃድ ወረቀት መያዝ ይኖርበታል።

ማሳሰቢያ፦
========
ይህን ያላደረገና ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ ይዞ የተገኘ ማንኛውም አካል እንደ ወንጀለኛ የሚጠየቅ ይሆናል።

- ፋብሪካዎች፣ ኢንደስትሪ ፖርኮች፣ ሪዞርቶችና አለም አቀፍ ሆቴሎች የሰራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከፖሊስ ኮሚሽኑ ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ።

- ከሲዳማ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ወደ ክልሉ የሚገቡ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መግባት አይችሉም። በእግረኞችና የቤት መኪኖች ላይ የሰዓት ገደብ ባይጣልም መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
#ህዳር 08/2014ዓ/ም
ሀዋሣ

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ "አሸባሪው የወያኔ ቡድን አይደለም ኢትዮጵያን ይዞ ሊያስተዳድር በቀጣይ ትግራይን እንኳን የማስተዳደር ዕድል የለውም"-  ‼ አሸባሪው እና ወራሪው የወያኔ ቡድን አይደለም ኢትዮጵያን ይዞ ሊ...
15/11/2021

‼ "አሸባሪው የወያኔ ቡድን አይደለም ኢትዮጵያን ይዞ ሊያስተዳድር በቀጣይ ትግራይን እንኳን የማስተዳደር ዕድል የለውም"- ‼

አሸባሪው እና ወራሪው የወያኔ ቡድን አይደለም ኢትዮጵያን ይዞ ሊያስተዳድር በቀጣይ ትግራይን እንኳን የማስተዳደር ዕድል የለውም ሲሉ የፋኖ ብርጌድ መሪ ሻለቃ ሰፈር መለሰ አስታውቀዋል።

ፋኖ ከወትሮው በተለየ በመንግስት ፈቃድና ድጋፍ በሻለቃና በብርጌድ እንደተደራጀ የገለፁት ሻለቃ ሰፈር መለሰ፣ የፋኖ አደረጃጀት በዚህ መንገድ መደራጀቱ የአማራን ህዝባዊ ሀይል የሚያጠናክር ከመሆኑም በተጨማሪ በፋኖ ስም የሚነግዱ አካላትን በማስቀረት ትክክለኛና የተደራጀ የህዝብ ሰራዊት እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል።

ይህ በሻለቃና በብርጌድ የተደራጀው የፋኖ ሀይል ከመከላከያ ሰራዊቱ፣ ከአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ ጋር በመቀናጀት ጠላትን እየተፋለመ እንደሚገኝም አዛዡ ገልፀዋል።

የፋኖ ብርጌድ መሪው፣ በግንባሩ የሚገኘው አጠቃላይ ሰራዊት እርስ በርሱ ተቀናጅቶና ተናቦ ጠላትን ለመቅበር እየታገለ ይገኛል ያሉ ሲሆን ፋኖ የራሱን ግንባር በመያዝ የጠላትን ምሽግ እየደረማመሰ በአሸባሪው ቡድን ላይ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ እንዲሁም የሞራል ኪሳራ እያደረሰ ይገኛል ብለዋል።

ጠላት የተለያዩ ጠንካራ ምሽጎችን በመስራት በተደጋጋሚ ጥቃት ለመሰንዘር ጥረት እያደረገ ቢገኝም የፋኖ ሀይል ፀረ ማጥቃት በማድረግ ሁለት የጠላት ምሽጎችን በመስበር ጀብዱ ፈፅሟል፤ በርካታ የጠላትን ሀይል በመደምሰስ ትጥቆችን ማርኮ ታጥቋል ሲሉ ሻለቃ ሰፈር መለሰ ገልፀዋል።

የህልውና ትግላችን ጠላትን ማሸነፍ እና ከወረራቸው አካባቢዎች ማስወጣት ብቻ ሳይሆን አሸባሪው ቡድን ዳግም ለአማራ ስጋት በማይሆንበት ደረጃ እስከ መቅበር ድረስ ነው ብለዋል። #መረጃውን ከአማራ ብልጽግና ፓርቲ አገኘነው

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼   ︎‼ወራሪው የጁንታው ሃይል ለዲያስፖራውና ለሚዲያዎቻቸው የሚሆን ትንሽ ጠብታ ድል ለማስመዝገብ በየቀኑ ቢሞክርም በተለየ መልኩ በዛሬው እለት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሸኔዎች እንዲሁም ደሴ ኮ...
15/11/2021

‼ ︎‼

ወራሪው የጁንታው ሃይል ለዲያስፖራውና ለሚዲያዎቻቸው የሚሆን ትንሽ ጠብታ ድል ለማስመዝገብ በየቀኑ ቢሞክርም በተለየ መልኩ በዛሬው እለት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሸኔዎች እንዲሁም ደሴ ኮምቦልቻን ጨምሮ የተለያዩ እስር ቤቶች ታስረው የነበሩ ሃይሎችን መሳሪያ አስታጥቆ በግዳጅ በህዝባዊ ማዕበል የካሳጊታን ግምባር ለመስበር ሞክሯል።

እንዲሁም የሰማይ ያክል የራቀው በእውን የሚቃዥላት #ሚሌን ለመያዝ ከፍተኛና እልህ አስጨራሽ ውጊያ ቢያደርግም፥ በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን እና በጀግኖቹ የአፋር አናብስቶች የወራሪውን ሃይል አከርካሪ በመስበር ወደ መጣበት መልሰውታል።

በጣም የሚገርመው በዚህ ግምባር በየቀኑ ወራሪው ሃይል ለ24 ሰአት ያለረፍት ከፍተኛ ወጊያ ነው የሚያደርገው ሆኖም እስካሁን አልተሳካም። ለወደፊትም አይሳካም።


በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ " " - ግብፃዊ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ  ዘካሪያ (ሉጥፊ) ‼ "ጌታቸውን ማመን ቀብሮ ነው። ትናንት የነበረውን ጌታቸውን ዛሬ ማግኘት ከባድ ነው። የኛ ቴሌቪዥን ሳይቀር ሰውየውን ኢንተ...
13/11/2021

‼ " " - ግብፃዊ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ዘካሪያ (ሉጥፊ) ‼

"ጌታቸውን ማመን ቀብሮ ነው። ትናንት የነበረውን ጌታቸውን ዛሬ ማግኘት ከባድ ነው። የኛ ቴሌቪዥን ሳይቀር ሰውየውን ኢንተርቪው አድርጎታል። በወቅቱ ይሄ ለምን ይሆናል ብየ ስጠይቅ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው የሚል መልስ ተሰጠኝ። የነገሮች መቀያየርና የትግራይ ሊሂቅና የወደፊቱ የምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ የህወሓት ሚና የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ የኛ ህዝብ ማወቅ ያለበትን አላወቀም።

ትናንት ህወሓት ኢትዮጵያን ሲመራ ለግብፅ ሀዘኔታ የለውም ነበር። ሀዘኔታ አለው ከተባለም የግድቡን ፕሮጀክት በማንጓተት አጠቃላይ አርቴፊሻል ብረቶችን ሰርቶ እንደገና አሁን በአብይ አሕመድ በማስተካከል የተወሰነ እዝነት አድርጓል ሊባል ይችላል። ግድቡ የኢትዮጵያ የመጨረሻ እጣፈንታ የሚወሰንበት ግድብ ቢሆንም ከመለስ ዜናዊ ቀብር በውኋላ አቅጣጫውን ስቶ ነበር። ህወሓት ትኩረት የሰጠው በግድቡ ዙሪያ አልነበረም። ፕሮጀክቱ ለህወሓት የኢትዮጵያን ህዝቦች የልብ ትርታ ማዳመጫና ግብፅ አሸባሪዎችን እየረዳች ግድቡን ልታስተጓጉል እየሰራች ነው እያሉ የስልጣን ማራዘሚያ አድርገውት ነበር።

ኢትዮጵያ ላይ በተደረጉ ለውጦች ውስጥ ህወሓትን የሚታገሉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የግብፅ ተላላኪ ነበር ስማቸው። አጠቃላይ ግብፅ አፍራሽ ሆና እንድትታይ ህወሓት ትልቅ ፕሮጋንዳ ሰርቷል። ያኔ ደሞ ጌታቸው
ረዳ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ነበር። በዛን ጊዜ ስለግብፅ ምን እንደሚል እናውቃለን።

አሁን ጌታቸው ከኛ ጋር ትልቅ ወዳጅ ነው። የኛ ደህንነቶች እጅግ አፍቃሪው ናቸው። በህወሓት የተማመኑበት ነገር ሊኖር ይችላል ምናልባት አዎ ይኖር ይሆናል። ነገሩ ግን እስከመቼ ድረስ ነው ይሄ ነገር የሚቀጥለው የሚል ግብፃዊ ጠያቂ ጋዜጠኛና አዋቂ ፖለቲከኛ የለም። ህወሓት የሚገዛው ማንን ነው የነማን ወዳጅ ነው የነማን ጠላት ነው ብሎ የጠየቀ የለም።

የጌታቸው ቡድን ከትግራይ ውጭ ያለው ህዝብ የማይረባ አድርጎ የንቀት ምልከታን የያዘ በእብሪት የተወጠረ ነው። ትግሬዎች ብቻ ናቸው ሀይለኛ ፈላጭ ቆራጭ የሚል ግምት አለው። ለሌላው ኢትዮጵያዊ ትልቅ ንቀት አላቸው። ይህ አስተሳሰብ ምናልባት ወደኋላ ወስዶን 18ኛ ክፍለ ዘመን ላይ ሊመልሰን ይችላል። እውነታው ግን የህወሓት እይታ ይሄ ነው። ከዚህ እብሪት የሚወጡ አይደሉም።

አሁን እንኳን ጥምረት አለን የሚሉት የኦሮሞ ጦር ጋር ወደፊት የሚቀጥሉበት የጋራ አጀንዳ የላቸውም። አፋርን እንዲሁም በሀይማኖት በባህል በጣም በጂኦግራፊ የሚቀርበውና በናይል የወደፊት ፖለቲካ ላይ ትልቅ ሀይል ያላቸውን አማራና ቤንሻንጉል ክልልን አልፎ ከኦሮሞ ጋር ብቻ የሚያደርጉት ወዳጅነት መሰረት የለውም።
እጅህን በሾክ ውስጥ አሳልፈህ እራስን ለሰላምታ መጋበዝ ነው።

እነሱ እንደሚሉት አሁን ህወሓት ኢትዮጵያ ኖረች አልኖረች ትግራይ እውን ትሆናለች የሚል ግምት አላቸው። በኦሮሞ በኩል ግን 99⁰/⁰ ኢትዮጵያ ትቀጥላለች የሚል ሀይል አለ። እስር ላይ ያለው ጃዋር መሀመድ ነገ ከአብይ ጋር ተነጋግሮ ቢለቀቅ፣ ከእስር ወጥቶ ከህወሓት ጋር የሚያደርገው ድርድ በኢትዩጵያ የወደፊት እጣፈንታ ዙሪያ ቢወያዩ የነ ጃዋር አሰላለፍ ከጉምዙና ከአማራው ከአፋሩ ከሱማሌው አጠቃላይ ከሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች ተለይተው ለህወሓት እውቅናና ሀይል አይሰጡትም።

ከህወሓት ጋር ጥምር ጦር ለመመስረት የሚወያየው ጃል መሮ ራሱ በኦሮሞ ፖለቲካ ላይ ያለው ተቀባይነት አንድ አውራጃን እንኳን የሚወክል አይደለም። ሆነም ቀረም የጃዋር ሀይል ነው ተሰሚነት ያለው። የነሱ ሀይል ደሞ ኢትዮጵያ ትፍረስ በሚለው ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ የመስጠት ጉዳይ ላይ ለድርድር አይቀመጥም።

ለምሳሌ የግድቡ ድርድር ውጥረት በገጠመው ሰሞን የጃዋር ፁሁፍ አጠቃላይ አሁን ካለው ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አሕመድና ከሞተው መለስ ዜናዊ ያልተየ ነበር ጠንካራ አቋም ነበር ሲያሳይ የነበረው።
የናይል ጉዳይ የኢትዮጵያ የወደፊት እጣፈታን የሚወሰንበት ጉዳይ ነው ብሎ ቃል በቃል የተናገረ ሰው ነው። ይሄ ሰውየ ነገ ለኛ የተሻለ ሆኖ የነጌታቸውን ምክር ሰምቶ ለግብጽ የሚጠቅም ስራን ይሰራል ብሎ የሚመኝ ግብፃዊ ካሉ እሱ ሞኝ ነው ።

እዚህ ላይ ልታውቁት የሚገባው ነገር ኦሮሞ ተበሎ በሚነገረው ጉዳይ ላይ የኦሮሞ ችግር ከኢትዮጵያ ጋር አይደለም የኦሮሞ ጥያቄ የፖለቲካ ጥያቄ ነው።
ቀላልና በውይይት የሚፈታ ነው። እሱንም ከአማራ ሊሂቅ ጋር ከመከሩበት ነገሮች በቀላሉ የሚቀየሩ ናቸው። የፖለቲካ ጠላትና ወዳጅ ቢኖርም የሁለቱ ብሔሮች መናጋት ነው ኢትዮጵያን የሚጎዳው የሁለቱ ጥምረት ግን የሌሎቹን ሚዛን የመቀየር አቅም አለው። ዋናው ጉዳይ እዚህ ላይ ነው የሚወሰነው። ሁለቱ ካልተስማሙ አዎ ምናልባት ህወሓት አቅም ኖሮት ከኛ ጋር ያለውን ቃል ሊፈፅም ይችላል። ከተስማሙ ግን የጌታቸው ረዳን ውሸት እየተጋትን መኖራች ነው።

እነዚህ ከላይ ያልኳችሁ ናቸው የኢትዮጵያና የህወሓት ጉዳይ። ከዚህ አንፃር ጌታቸው ረዳን አምኖ እሱ ለግብፅ የተሻለ ስራ ይሰራል የሚል ካለ ራሱን ከተኛበት አልጋ ላይ ማንቃት አለበት። ጌታቸው ረዳም ይሁን ህወሓት የጊዜ ጉዳይ ይዟቸው እንጂ አጠቃላይ የትግራይ ፖለቲካ ለናይል ውሃና ለአረብ የውሃ ጥቅም መከበር ምንም አይነት ሚና አይኖረውም። የወደፊቱ የናይል ውሃ ቁልፍ ያለው ጣናን አቅፎ ከያዘው አማራ ጋር ሲሆን ወንዙን አቋራጦ ከሚሄደው ቤንሻንጉል ክልል ጋር ነው።
የወደፊቱም የኛ ጉዳይ የሚወሰነው በእነዚህ ክልሎች የፖለቲካ እጣፈንታ ጉዳይ ላይ ነው" ብሏል ግብፃዊ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ዘካሪያ (ሉጥፊ)።


በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ በሲዳማ ክልል ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ ‼በሲዳማ ክልል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚከለክላቸው ተግባራት በመሳተፍና ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ግንኙ...
13/11/2021

‼ በሲዳማ ክልል ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ ‼

በሲዳማ ክልል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚከለክላቸው ተግባራት በመሳተፍና ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ፈጥረው ለጠላት እገዛ በማድረግ የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያን ከተደቀነባት የህልውና አደጋ በአጭር ጊዜ ለማላቀቅ በሀገር ደረጃ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዜጎች ተፈጻሚ ሊያደርጉት ይገባል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣቱን ተከትሎ በሲዳማ ክልል በርዕሰ መስተዳድሩ ሰብሳቢነት የሚመራ ክልል አቀፍ የዕዝ መምሪያ ” ኮማንድ ፖስት ” ተቋቁሞ ለተፈጻሚነቱ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስከ ወረዳ ድረስ በተዘረጋው በዚህ አደረጃጀት በርካታ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም መልካም ውጤት እየታየ መምጣቱን አመልክተዋል።

እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሚከለክላቸው እኩይ ተግባራት ላይ በመሳተፍ የተጠረጠሩ ግለሰቡች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ነው ኃላፊው ያስታወቁት።

ከነዚህ መካከል የሀገር መከላከያ አመራር የነበሩና በሀገር ላይ ክህደት ፈፅመው ተሸሽገው የቆዩ እንዳሉበት አቶ አለማየሁ አስረድተዋል።

ከሰሞኑ አዲስ አበባ ላይ እየተካሄደ ያለውን አሰሳና ፍተሻ በመሽሽ ሀዋሳ ውስጥ ቤት ተከራይተው ተሸሸገው የነበሩና የተለያዩ የባንክ ሒሳብ ደብተሮች የያዙ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል ይገኙበታል ነው ያሉት።

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

︎  ። ሁለተኛ ሳምንቱ አጋማሽ ላይ የሚገኘው የሚሌ ፍልሚያ ላለፉት13ወራት ከተደረጉት ውጊያዎች ረጅም ጊዜ የወሰደ፣ በህወሀት ላይ አያሌ የሰው ዕልቂትና የመሳሪያ ውድመት ያደረሰበት እንደሆነ...
13/11/2021

︎ ። ሁለተኛ ሳምንቱ አጋማሽ ላይ የሚገኘው የሚሌ ፍልሚያ ላለፉት13ወራት ከተደረጉት ውጊያዎች ረጅም ጊዜ የወሰደ፣ በህወሀት ላይ አያሌ የሰው ዕልቂትና የመሳሪያ ውድመት ያደረሰበት እንደሆነ ይነገራል። ህወሀት ሚሌን መያዝ የዓለም መጨረሻ አድርጎ የትግራይ ወጣቶችን ህይወት እየገበረበት ነው። ዕልቂቱ አሰቃቂ ነው። በሜዳማ የተፈጥሮ አቀማመጥ ውጊያ ማድረግ የማይችለው የህወሀት ሃይል የአፋር በረሃ አቅልጦ እያስቀረው ነው። በነገራችን ላይ ሚሌ ሲባል ውጊያው የሚካሄድበትን አከባቢ የሚገልጽ አይደለም። ሚሌ ሩቅ ናት። ከ100 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት ባሉ እንደካሳጊታ ቦታዎች ነው አሁን ጦርነቱ እየተካሄደ የሚገኘው።

ረቡዕ ዕለት ሄሊኮፕተር ጣልን ብሎ ጌታቸው ረዳ የህወሀትን መንደር ለሰዓታት ካስፈነደቀ በኋላ እሱን ተከትሎ ቴሌቪዥን መስኮት ላይ ጉብ እያለ ኮሚዲ ዜናዎችን የሚያስኮመኩመን ገራገሩና ጅላጅሉ ስታሊንም ሚሌ ጭብጣችን ውስጥ ገባች ሲል መንጋውን በባዶ ሜዳ ለማስደሰት ሞክሯል። በእርግጥም ሚሌ የሰማይን ያህል ርቃለች። ለህወሀቶች በአካል የሚጠጓት ይቅርና በምኞት ፈረስ የምትጋለብ ልትሆን አልቻለችም። ህልም ሆና ቀርታለች። ለፈረንጆቹ በሁለት ሳምንት ጮማ የድል ዜና እናደርሳችኋለን ብሎ ቃል የገባው ጻድቃን ገ/ትንሳይ ከአንድ ወር በኋላ ትንፋሹን እንኳን ደብቋል።

በየግንባሩ ያለው ወቅታዊ ሁኔታም ተመሳሳይ ነው። ሰሜን ሸዋ በትንንሽ ቁጥር እየተሽሎኮለከ ለመግባት የሚጋጋጠው የህወሀት ጀሌ እየተለቀመ በመያዝ ላይ ነው። አምልጦ የገባና የሆነች ቦታ ፎቶ ተነስቶ ከተማ ያዝን፣ ተቆጣጠርን የሚል የድል ወሬ ለማስተላለፍ የሚሞክር አሁንም አይጠፋም። እንዲህ ዓይነቱን ትርጉም የሌለው ጀብደኝነት እስከአዲስ አበባ ጫፍ ድረስ ከሸኔ ትርፍራፊ ታጣቂ ጋር ሆኖ ለማድረግ እቅዱ እንዳለ ተሰምቷል። ለዚህም የየአከባቢው ማህበረሰብ ነቅቶና የጸጉረ ልውጦችን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ተከታትሎ ከንቱ ህልማቸውን መቅጨት የወቅቱ ትልቅ ሃላፊነት መሆን ይገባዋል። የፌደራልና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተናበው እየሰሩበት እንዳለ መረጃውን አግኝቼአለሁ።

እዚህ ላይ ወዳጄ ጌታቸው ሽፈራው ያነሳውን ቁልፍ ጉዳይ ደግሜ ብጠቅሰው ደስ ይለኛል። ጌታቸው ስለህወሀት ጀሌ የእስከአሁን ግስጋሴ ሲያነሳ እነሱ ድላቸውን የሚለኩት በገደሉት ሰው ቁጥር ሳይሆን በያዙት መሬት ርቀት ልክ ነው በማለት ነው። ከእኛ ሃይሎች ጋር ሲያነጻጽርም እኛ ከእነሱ በብዙ እጥፍ የሚልቅ ታጣቂዎቻቸውን እንገላለን፣ ነገር ግን መሬት በመያዝም ሆነ በማስለቀቅ ረገድ የምንመነዝረው ድል እጅግም አናሳ ነው ሲል ጌታቸው ወሳኝ ነጥብ አንስቷል። ድልን በምንይዘው አንድ ኢንች ጋት መሬት እየለካን ወደፊት መሄድ ካልቻልን የሰው ህይወት የትንኝ ነፍስን ያህል ዋጋ ያጣበትን ህወሀት በምንገለውና በምንማርከው ታጣቂዎቹ ብዛት ድላችንን እየመነዘርን ብቻ እናጠፋዋለን የሚለው ስሌት የጦርነትቱን ጊዜ ከማራዘም በሂደትም እንደሀገር ትልቅ ኪሳራና ውድቀት ላይ ከመጣል ያለፈ ምንም ዓይነት ውጤት የለውም።

የድል ምሶሶውና ማገሩ መሬት መቆጣጠር፣ ስትራቴጂክ ቦታዎች ነጥቆ መያዝ ነው። ከዚህ አንጻር አሁን ለውጥ እያየን ይመስለኛል። ድላችን የህወሀትን ወራሪ ሃይል ከመደምሰስ ባሻገር፣ መሬት በመቆጣጠር፣ በህወሀት የተያዙትን አከባቢዎች በማስለቀቅ ጭምር የሚለካበት የመልሶ ማጥቃት መጠነ ሰፊ ዘመቻ የመጀመሩ ፍንጭ ከፊታችን ልብ የሚያሞቁ ዜናዎች እንደሚኖሩ እንድገምት አድርጎኛል። እንበርታ!


በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼  #የአሜሪካኖች ጩኸትና ጫና መሠረታዊ ዓላማው  #በጅቡቲ ያለውን  #የቻይና የጦር ሰፈር እንዲዘጋ ማድረግ ነው...... #በቻይና እና  #አሜሪካ መካከል የሚካሄደው   ማሳያ  አሁን  #በ...
13/11/2021

‼ #የአሜሪካኖች ጩኸትና ጫና መሠረታዊ ዓላማው #በጅቡቲ ያለውን #የቻይና የጦር ሰፈር እንዲዘጋ ማድረግ ነው......
#በቻይና እና #አሜሪካ መካከል የሚካሄደው ማሳያ አሁን #በኢትዮጵያ እያካሄዱት ያለው የተልዕኮ ጦርነት ነው ‼

በአፍሪካ ቀንድ የሰይጣን መልዕክተኛ የሆነው ሰውዬ ጠዋት ማታ ወደ ኢትዮጵያ የሚመላለሰው፤ የኢትዮጵያ ወዳጆች የሆኑትን ቱርክ እና የተባበሩት የአረብ ኤምሬትስን አቋም ለማስቀየር የሚታትረው፣ የአሜሪካ ተላላኪ የሆኑት ሳውዲ አረቢያ እና ግብፅ፣ እንዲሁም የእነሱ ተላላኪ የሆኑት ሱዳን እና ኬኒያ የሚሯሯጠው ለምንድነው? መልሱን ትላንት በጅቡቲ የአሜሪካን የጦር አዛዥ ስለ ኢትዮጵያ በሰጠው አስተያየት ላይ ታገኙታላችሁ።

የአሜሪካኖች ጩኸትና ጫና መሠረታዊ ዓላማው በጅቡቲ ያለውን የቻይና የጦር ሰፈር እንዲዘጋ ማድረግ ነው። የአሜሪካው የጦር አዛዥ ትላንት የተናገረው ነገር ሙሉ በሙሉ ባዶ ቀረርቶ መሆኑን የምታውቁት ከጎናቸው የሚገኘው የቻይና የጦር ሰፈር 10,000 ወታደሮችን መያዝ የሚችል ሲሆን የራሱ ሆነ ወደብ እና Naval Base አለው። በአንፃሩ የአሜሪካ የጦር ሰፈር 4,000 ወታደሮችን የመያዝ አቅም አለው። ይህም ሆኖ አሜሪካኖቹ የሚፈሩት ከጎናቸው ካለው የቻይና የጦር ሰፈር ይልቅ በምዕራባዊ ቻይና ከሚገኙት 100 የሚጠጉ የሮኬት ማስወንጨፊያዎች የሚተኮሰውን "Hypersonic Missile" ነው።

የቻይና Hypersonic ሚሳኤል በሰዓት 4ሺህ ማይል የሚመዝገዘግ ሲሆን ከቻይና ቤጂንግ ተነስቶ አሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ለመድረስ 100 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ40 ደቂቃ) ብቻ ነው። በቅርቡ ቻይና ይህን እጅግ ዘመናዊ የሆነ የጦር መሣሪያ ሙከራ አድርጋለች። ሚሳኤሉ የምድርን ወገብ በሚገርም ፍጥነት ከዞረ በኋላ ኢላማውን መምታቱን በከባድ ድንጋጤ ውስጥ ሆነው የነገሩን የአሜሪካ ኢታማዦር ሹም ናቸው። ቻይና Hypersonic Missile ሙከራን በተሳካ ሁኔታ ያደረገችው የአሜሪካ ጦር በተመሳሳይ መንገድ ያደረገው ሙከራ በከሸፈ ማግስት ነው።

የአሜሪካው የጦር ጄኔራል እንደተናገሩት አዲሱ የቻይና Hypersonic Missile በዓለም ላይ የመጀመሪያው ከመሆኑም በተጨማሪ በምድር ወደብ ላይ ሲሽከረከር ከላይ ወደታች ገላምጧቸው ካለፉት ሀገራት አንዷ አሜሪካ መሆኗ በ1957 ሩሲያ የመጀመሪያውን ሳተላይት ወደ ህዋ ስታመጥቅ የተፈጠረውን አይነት ድባብ በአሜሪካ ነጩ ቤተመንግሥት እና ፔንታጐን ውስጥ ዳግም መፈጠሩን የራሳቸው ሚዲያዎች ሳይቀሩ በስፋት ዘግበውበታል።

ዋናው ቁምነገር ከ60 አመት በፊት ለቀዝቃዛው ጦርነት መነሻ የሆነው በአሜሪካ እና ሩሲያ መካከል የነበረው የጦር መሣሪያ እሽቅድድም ዛሬ በአሜሪካ እና ቻይና መካከል ተከስቷል። ሩሲያ እና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ሲያካሂዱት የነበረውን "Proxy war" ዳግም በኢትዮጵያ እያካሄዱት ይገኛሉ። በቅርቡ ጠ/ሚ አብይ አህመድ እንደተናገሩት 2ኛው የዓለም ጦርነት የተጀመረው ናዚ ፖላንድን ከመውረሩ የተወሰኑ አመታት ቀደም ብሎ ነው። በተመሣሣይ 2ኛው ቀዝቃዛ ጦርነት የተጀመረው ከስድስት አመት በፊት በፈረንጆች አቆጣጠር በ2015 ነው።

ይህ በቻይና አሜሪካ መካከል የሚካሄደው ቀዝቃዛ ጦርነት ማሳያ ደግሞ አሁን በኢትዮጵያ እያካሄዱት ያለው የተልዕኮ ጦርነት ነው። ችግሩ የዶ/ር አብይ ከቻይና መንግስት ይልቅ ፊቱን ወደ ሩሲያ እና ቱርክ ማዞሩ ላይ ነው። አሜሪካኖች በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ጫና እና ግፊት የሚያቆሙት እኛ ስንሸነፍ ወይም የእነሱ ተላላኪዎች ስንሆን ብቻ ነው። ዳግም የኢምፔሪያሊስቶች ተላላኪ ከመሆን ይልቅ ጓዛችንን ጠቅልለን ከቻይናዎቹ ጋር መጣመር እና አይቀሬውን 3ኛው የዓለም ጦርነትን ቀድመን እንጀምረው።

https://youtu.be/xyaq7S05HQs

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ ሀገራት የአሜሪካንን ህገወጥነት በመቃወም ከኤርትራ ጎን እንዲቆሙ  #ኤርትራ ጥሪ አቀረበች ‼ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የምትወስደውን ህገወጥ ማዕ...
13/11/2021

‼ ሀገራት የአሜሪካንን ህገወጥነት በመቃወም ከኤርትራ ጎን እንዲቆሙ #ኤርትራ ጥሪ አቀረበች ‼

ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የምትወስደውን ህገወጥ ማዕቀብ በማውገዝ ከጎኗ እንዲቆም ኤርትራ ጥሪ አቀረበች።

ኤርትራ ትላንት አሜሪካ የጣለችባትን ማዕቀብ ህገወጥ እና ኢሞራላዊ ስትል አውግዛለች። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት ያወጣው መግለጫ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል።

የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር በኤርትራ ላይ የተሳሳተ እና የጥላቻ ፖሊሲውን በማስቀጠል አዲስ የሚመስለውን “ማዕቀብ” አውጇል። ይህ ኤርትራን ተወቃሽ የሚያደርግ እና በተንኮል ውንጀላ ላይ የተመሰረተ የአንድ ወገን ማዕቀብ፣ ከዓለም አቀፍ ህግጋቶች ጋር የሚጋጭ እና የሀገራትን ሉዓላዊነት ብሎም ነጻነትን የሚጻረር ነው።

የማዕቀቡ ግልፅ አላማ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያ ዘላቂ መረጋጋትን የሚያመጡ መፍትሄዎችን ማደናቀፍ እና የድሮውን የትርምስ አዙሪት በመቀስቀስ ዳግም ማስቀጠል ነው። በዚህ ሂደት ዓለምአቀፍ ሚዲያዎች መሰረተ ቢስ ውንጀላዎችን በማቀነባበር ያለማቋረጥ መስራታቸው እሙን ነው። ይህን ሕገወጥ ማዕቀብ ለመጣል በሚያሳዝን ሁኔታ ውሸትን እና የአንድ ወገን ውንጀላዎችን ምክንያታዊ ለማድረግ የሚሰሩ ተከፈይ የሀሰት ምሥክሮችን ተጠቅመዋል።

የዚህ ሕገወጥ እና ሥነ ምግባር የጎደለው ማዕቀብ ዋና ዓላማ በሕዝብ ላይ መከራና ረሃብ እንዲፈጠር በማድረግ የፖለቲካ አለመረጋጋት እንዲፈጠር ማድረግ እንደሆነ ኤርትራ ትገነዘባለች። ስድብ በሚመስል መልኩም ያለምንም ማፈር “ማዕቀቡ የኤርትራን ሕዝብ ለመጉዳት ያለመ አይደለም” በማለት ተናግረዋል። ነገር ግን በእነሱ የአዞ እንባ ሊታለል የሚችል ማንም የለም።

የኤርትራ ህዝብና መንግስት ይህንን ህገ-ወጥ የአንድ ወገን ማዕቀብ በጽኑ ያወግዛሉ። በዚህ አጋጣሚ በመላው ዓለም ላይ የምትገኙ ማንኛውም ሰላምና ፍትህ ወዳድ፣ ሉዓላዊ እና ገለልተኛ ሀገራት ይሄንን ማዕቀብ በመቃወም ከኤርትራ ህዝብ እና መንግስት ጎን በመቆም ድጋፋቹን እንድትገልፁ ጥሪ እናቀርባለን።

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር
አስመራ
ህዳር 13 ቀን 2021

https://shabait.com/2021/11/13/eritrea-deplores-illicit-and-immoral-us-sanctions/

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ አክቲቪስት ታማኝ በየነ ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ ኢትዮጵያዊነቴ ትርጉም የለውም አለ ‼  ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ የእኔ ኢትዮጵያዊነት ትርጉም የለውም ሲል ...
13/11/2021

‼ አክቲቪስት ታማኝ በየነ ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ ኢትዮጵያዊነቴ ትርጉም የለውም አለ ‼

ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ የእኔ ኢትዮጵያዊነት ትርጉም የለውም ሲል የሰብኣዊ መብት ተሟጋችና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ተናገረ።

አክቲቪስቱ ወደ አገሩ መመለሱን በማስመልከት ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጠ ነው።

በመግለጫው አገሬን በክፉ ቀኗ አብሬያት ካልሆንኩ ደግሜ አገሬን ለመመልከት የሚያስችል ሞራል ሊኖረኝ አይችልም ብሏል።

አሸባሪውን ሕወሓትን ሴራ ያልተናገርኩበት ወቅት የለም ያለው ታማኝ አሁን ግን ርህራሄ የማያውቅ ክፉ መሆኑን ማረጋገጫ ሰጥቷል ሲል ተናግሯል።

አክቲቪስት ታማኝ ሁሉም ሕዝብ አብሮ በመሆን አሸባሪውን ቡድን ማጥፋት እንደሚገባውም ጥሪ አቅርቧል።

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በፅኑ አወገዘች ‼ አሜሪካ በትናንትናው ዕለት በኤርትራ መንግስት ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ኢትዮጵያ አውግዛለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግ...
13/11/2021

‼ ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በፅኑ አወገዘች ‼

አሜሪካ በትናንትናው ዕለት በኤርትራ መንግስት ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ኢትዮጵያ አውግዛለች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ውሳኔ በግልጽ የሚታወቁ እውነታዎችን ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነበር ብሏል።

የአሜሪካ መንግስት የሚከተሉትን እውነታዎች ከግምት ውስጥ እንዲያስገባ መንግስት ጠይቋል፦

1. ህወሓት በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ያደረሰውን ያልተጠበቀ ጥቃት ተከትሎ ሉዓላዊት ሀገር በሆነችው ኤርትራ ላይ ሮኬቶችን ተኩሷል።

2. የኤርትራ መንግስት በግዛቱ አንድነት እና ደህንነት ላይ ለተቋጣው ጥቃት ምላሽ የመስጠት ሉዓላዊ መብት አለው።

3. የኢትዮጵያ መንግስት የኤርትራ ጦር ግዛቱን አልፎ መገኘቱን አስመልክቶ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ቅሬታ አለማቅረቡንም መግለጫው አስታውሷል።

እንዲህ ዓይነት ቅሬታ የማቅረብ መብት ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ እንጂ ሌላ አካል አይደለም።

4. የኤርትራ መንግስት የኢትዮጵያ መንግስት ያወጀውን የተናጥል የሰብአዊ መብት ተኩስ አቁም ተከትሎ ወታደራዊ ሀይሉን ከኢትዮጵያ ማስወጣቱም ይታወቃል።

5. የኢትዮጵያ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዳይሰፍን የኤርትራ መንግስት እንቅፋት ነው ብሎ አያምንም። በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለው የሰላም ስጋት የህወሓት ጠብ አጫሪነት እና ወረራ ነው።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የህወሓትን የማተራመስ ሚና አጥብቆ ለማውገዝ አለመፈለጉም የሽብር ቡድኑን አበረታቶታል ብሎ መንግስት ያምናል።


በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

‼ አሜሪካ ዳግም በክፋት የቆሸሸ እጇን በኤርትራ ላይ አንስታለች‼‼ አሜሪካ በኤርትራውያን ባለስልጣናት እና ተቋማት ላይ ማዕቀብ ጥላለች ‼ አሜሪካ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያ...
12/11/2021

‼ አሜሪካ ዳግም በክፋት የቆሸሸ እጇን በኤርትራ ላይ አንስታለች‼
‼ አሜሪካ በኤርትራውያን ባለስልጣናት እና ተቋማት ላይ ማዕቀብ ጥላለች ‼

አሜሪካ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት፤ በኤርትራ አራት ተቋማት እና ሁለት ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ዛሬ አርብ የወሰደው ይህ እርምጃ፤ “የኢትዮጵያን መረጋጋት እና አንድነትን ላናጋው ቀውስ እና ግጭት አስተዋጽኦ ያበረከቱ ኤርትራውያን ተዋናዮች ላይ ያነጣጠረ“ መሆኑን ይፋ አድርጓል።

በማዕቀቡ ከተካተቱት መካከል የኤርትራ ገዢ ፓርቲ ህዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ (PFDJ) እንዲሁም የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት ይገኙበታል።

የኤርትራ ብሔራዊ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አብርሃ ካሳ ነማርያም እና የገዢው ፓርቲ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ ሐጎስ ገብረሕይወት ወልደኪዳንም ማዕቀብ የተጣለባቸው ባለሥልጣናት ሆነዋል።

በአሜሪካ ግምጃ ቤት የውጭ ሃብት ቁጥጥር ቢሮ (OFAC) ዛሬ ይፋ በተደረገው መግለጫ መሠረት፤ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪው አቶ ሐጎስ በዋና ስራ አስፈጻሚነት በሚመሩት “ሬድ ሲ ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን” ላይም የአሜሪካ መንግስት ማዕቀብ ጥሏል።

ከ27 አመታት ገደማ በፊት የተመሠረተው እና የገዢው ፓርቲ የንግድ ተቋማትን በበላይነት የሚያስተዳድረው “ህድሪ ትረስት” የተባለው ድርጅትም የማዕቀቡ ሰለባ ሆኗል።

ሁለቱ ተቋማት በአሜሪካ የሚገኝ ጥሪታቸውን ከማንቀሳቀስ እንደታገዱ የውጭ ሃብት ቁጥጥር ቢሮ ማስታወቁን በኢትዬጲያ የአሜሪካ ኤንባሲ ገልጿል።

በፌስቡክ የማይለቀቁ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በዚህ የቴሌግራም ቻናል በመግባት ይመልከቱቨ
https://t.me/joinchat/g9j2Vfso_XhiNWZk

Address

Addis Ababa

Telephone

+251924652539

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hair loss regeneration posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hair loss regeneration:

Share