Ever Light

Ever Light Updates on different situations You can get what you want,if you put here.

አስቸኳይ ስብሰባ ተጠርቷል‼️ገዥው ብልጽግና ፓርቲ፣ የሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በሙሉ "ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች" ላይ ለመምከር ለአስቸኳይ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ መጥራቱ...
01/08/2025

አስቸኳይ ስብሰባ ተጠርቷል‼️

ገዥው ብልጽግና ፓርቲ፣ የሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በሙሉ "ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች" ላይ ለመምከር ለአስቸኳይ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ መጥራቱ ታወቀ።

በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ላይ፣ በፀጥታው እንዲሁም በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ተሰምቷል።

ስብሰባው ከነገ ቅዳሜ ጀምሮ በ4 ኪሎ ቤተመንግስት የሚጀምር ሲሆን በስብሰባው ላይ ለመሳተፍ፣ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ከተለያዩ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር ያሉ ድርጅቶች ሀገሪቱን አረንጓዴ በማልበስ ሂደት ላይ የድርሻቸውን ተወጥተዋል፤ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ  ጀምበር የመት...
31/07/2025

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር ያሉ ድርጅቶች ሀገሪቱን አረንጓዴ በማልበስ ሂደት ላይ የድርሻቸውን ተወጥተዋል፤ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን ተቀላቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ ስፍራዎች አሻራቸውን ካኖሩ ድርጅቶች መካከል እነሆ እንልዎታለን፡፡
 የኢባትሎ አመራርና ሠራተኞች ዛሬ ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. የኢባትሎ ዋ/ሥ/አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) በተገኙበት በገላን ወደብና ተርሚናል አረንጓዴ አሻራ የማኖር ተግባር አከናውነዋል።
በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) መርሃ-ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለአካባቢ ጥበቃ እጅግ ወሳኝ ነው ያሉ ሲሆን ፣ የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ አካል በመሆናችን ታላቅ ደስታ እና ክብር ይሰማናል ብለዋል።

 የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የክረምት በጎፈቃድ ስራዎች የችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት፣ የተማሪዎች ቁሳቁስ እና መጣቶችን የማነቃቃት ስራ ተሰርቷል ለዚህም የክልሉ መስተዳድር ከፍተኛ እገዛ አድርገዋል።

 የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች ‹‹በመትከል ማንሰራራት›› በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ውን ሰባተኛውን ዙር ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሞጆ ከተማ በተዘጋጀው የችግኝ መትከያ ስፍራ በመገኘት አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

 የኢትዮጵያ ቤቶች ኮርፖሬሽን የዘንድሮውን የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል ምስራቅ ሀረርጌ ዞን ማያ ከተማ ተገኝተው አስጀምረውታል። በአንድ ጀምበር 7 መቶ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እየተከናወነ ባለው መርሐ ግብር የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች በተለያዩ ቦታዎች ሀገር በቀል ችግኞችን በጉለሌ እፅዋት ማዕከል፣ በቢሾፍቱ ኢባዩ ተራራ፣ በመኖሪያ አፓርትመንቶች፣ በማምረቻ ማዕከላት፣ በመኖሪያ ጊቢዎች ሀገር በቀል ችግኞች ተክለዋል።

 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 5,688 ሰራተኞች የተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ያከናወኑ ሲሆን በዚህ ክንውንም 64,640 ችግኞችን በአንድ ጀምበር መትከል ችለዋል፡፡

 የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ተሳተፈዋል፡፡ የግሩፕ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በተለያዩ ስፍራዎች በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞች የመትከል መርሐ ግብር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የግሩፑ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞቹ የተሳተፉት በምዕራብ አርሲ ዞን በወንዶ ወረዳ እና በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በተከናወኑ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብሮች ላይ ነው፡፡ በምዕራብ አርሲ ወንዶ ወረዳ በተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባን ጨምሮ የግሩፑ ከፍተኛ የማነጅመንት አባላት እና የፋብሪካዎቹ የሥራ መሪዎች እንዲሁም የመከላከያ ሠራዊት አባላትና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

 የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን(ኬ.ኢ.ኮ) በሀገር ደረጃ በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ኢ/ሆልዲንግ ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮች፣ ማኔጅመንት አባላት፣ ሠራተኞች እንዲሁም በሥሩ የሚገኙት ተቋማት ሥ/አስኪያጆችና ሠራተኞች (በኮርፖሬሽኑ ብቻ ከ140 በላይ ሠራተኞችን በማሳተፍ) በተገኙበት ቆቃ በተባለው አካባቢ በሚገኘው ረጅም ከ.ሜ በሚሸፍነው በፈጣን መንገድ ዳርቻ ላይ ከፍተኛ የሆነ የአረንጓዴ አሻራ መ/ግብር አከናውነዋል፡

በ2017 በጀት ዓመት ከ108 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል - የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስአዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስ...
28/07/2025

በ2017 በጀት ዓመት ከ108 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል - የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ በ2017 በጀት ዓመት ከ108 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር)፤ በ2017 በጀት ዓመት በተቋሙ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም የገቢ መጠን ማሳደግ፣ የመርከቦችንና የጭነት ተሽከርካሪዎችን የመጫን አቅም መጨመር፣ ፈጣንና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት መስጠትና በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ማጎልበት በበጀት ዓመቱ በትኩረት የተከናወኑ ተግባራት መሆናቸውን አንስተዋል።

ከዚህ አንጻር በ2017 በጀት ዓመት 101 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ከ108 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መግኘቱን ገልጸዋል።

ይህም ከእቅዱ አንፃር ሲታይ አፈፃፀሙ ከመቶ ፐርሰንት በላይ ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል።

ይህ ከፍተኛ ውጤት እንዲመዘገብ በቅርቡ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰቱ አለመረጋጋቶች በባህር ትራንስፖርት አገልግሎት እንቅስቃሴ ላይ የፈጠሩትን ጫና በመቋቋም ውጤታማ ስራ መከናወኑንም ገልጸዋል።

ምንጭ:- ኢዜአ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን 9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ገቢ አስመዘገበ***የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ግምገማ የ2018 በጀት...
24/07/2025

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን 9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ገቢ አስመዘገበ
***

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ግምገማ የ2018 በጀት ዓመትን እቅድና የአፈጻጸም አቅጣጫ በማስቀመጥ አጠናቋል፡፡

በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ረሻድ ከማል በተመራው በዚህ የማጠቃለያ ግምገማ ተቋማዊ ሪፎርሙ ከአገራዊ ሪፎርሙ እኩል ግለቱን ጠብቆ እንዲጓዝ ባማስቻል ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ያረጋገጡ ውጤቶች በሁሉም መስክ መገኘታቸው ተገምግሟል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ያገኘው የ9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ገቢ ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጀመር ከነበረበት ተመሳሳይ ወቅት የ2010 በጀት ዓመት (300 ሚሊየን ብር ገቢ ) ጋር ሲነጻጸር ከ 30 ጊዜ በላይ እጥፍ የገቢ አድገት ተመዝግቧል፡፡

ለገቢ እድገቱ ፡- የገቢ ማግኛ መሰረቱና ዓይነቱ በመስፋቱ ፣ ከአማካሪነት በተቋራጭነት የተገኘው ገቢ ፣ በሪኖቬሽንና ሥራ እና ከቤት ሽያጭ የተገኘው ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እድገት በማሳያታቸው እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ ከ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ተጨማሪ ሀብት (ASSET) መፍጠሩም ተችሏል፡፡

በኮርፖሬሽኑ እንዲሁም በደንበኞች ሙሉ በሙሉ ወጪ በርከታ ሱቆች በመገንባታቸው ከፍተኛ ገቢ ከማስገኘታቸው ባሻገር ኮርፖሬሽኑ ከ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ተችሏል፡፡

የተፈጠረው ሀብት በኮሪደር ልማት ስታንዳርድ መሰረት እንዲነሱ ከተደረጉት የኮርፖሬሽኑ ቤቶች በላይ ግምት ያለው ሀብት በአጭር ጊዜ መፍጠር መቻሉ በጥንካሬ ተገምግሟል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመት የተገኘው ንጹህ የኦዲት አስተያየት ፣ በሥራ ላይ ካለው የአልሙኒም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂ በተጨማሪ የ3ዲ ኮንስትራክሽን ፕሪንት ቴክኖሎጂ እና የፕሪካስት ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ለማስገባትና ለማላመድ በበጀት ዓመቱ የተከናወነው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይ በፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደር ፣ አዲዳስ ፕሮጀክትን ለመጀመረ እየተከናወኑ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ፣ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም ግንባታ ፣ በትብብር የሚከናወኑ አገራዊ ፋይዳ ያለቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ሥራዎች ላይም ትኩረት ያደረገ ግምገማ ተከናውኗል፡፡

ዘመናዊ አፓርትመንት ሕንጻዎችን ወደ ሥራ ማሰገባት መቻሉና ግዙፉን የግብዓት ማምረቻ ማዕከል አጠናቆ በአጭር ጊዜ ወደ ምርት ሥራ ማስገባት መቻሉና አሁን ላይ በሙሊ አቅሙ ወደ ምርት እንዲገባ ለማስቻል እየተሰሩ ያሉት ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውም ተጠቁሟል፡፡

ከተለያዩ አካለት እየመጡ ያሉ አብረን እንሰራ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ሚያስችል የመፈጸምና የማስፈጻም አቅም ግንባታ ሥራዎችን የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል የአፈጻጸም አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡

በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ያስቀመጠውን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችለውን ሰፊ እቅድ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ከአፈጻጸም አቅጣጫ ጋር በማጽደቅ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ውጤታማና ታሪካዊ የማጠቃለያ ግምገማ በስኬት አጠናቋል፡፡
(ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን)

22/07/2025

መንግስት የአርሶ አደሩን የአፈር ማዳበሪያ በከፍተኛ የወጪ ድጎማ ግዥ ከመፈፀሙም ባሻገር ከምርት ቦታ እስከ አርሶ አደሩ በር ድረስ የማጓጓዙን ስራ በትጋትና በውጤታማነት እያከናወነ መሆኑ ደስ የሚያሰኝ ነው።

"የባህር በር ማግኘት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ መብት ነው" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ   ⚓️የባህር በር ማግኘት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ መብቷና ዓለም አቀፉ ህግ የሚፈቅደው መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ...
22/07/2025

"የባህር በር ማግኘት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ መብት ነው" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

⚓️

የባህር በር ማግኘት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ መብቷና ዓለም አቀፉ ህግ የሚፈቅደው መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ክቡር አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ።

ክቡር አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንደገለጹት፤ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያ የወጪና ገቢ ንግድ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ስለሆነ የባህር በር የግድ ያስፈልጋታል። የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ መሰረታዊ መብቷና ዓለም አቀፉ ህግ የሚፈቅደው መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በርን ማግኘት የምትፈልገው በሰላማዊ፣ በትብብርና በስጥቶ መቀበል መርህ መሆኑን አመላክተው በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ድጋፍ እያገኘ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የዲፕሎማሲ ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

© ጋዜጣ ፕላስ

ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ?አባዬ - አለው የገበሬው ልጅአቤት - አለ አባቱ።ይሄ የሚሰማው ድምጽ ምንድን ነው?የጃርቶች ድምጽ ነው ልጄ።ባለፈው ስታርስ ጮኹ። ስትዘራ ጮኹ። ስታጭድ ጮኹ- አለው ልጁ...
20/07/2025

ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ?
አባዬ - አለው የገበሬው ልጅ
አቤት - አለ አባቱ።
ይሄ የሚሰማው ድምጽ ምንድን ነው?
የጃርቶች ድምጽ ነው ልጄ።
ባለፈው ስታርስ ጮኹ። ስትዘራ ጮኹ። ስታጭድ ጮኹ- አለው ልጁ።
ልክ ነህ - መለሰለት አባቱ።
ለምን?- አለ ልጅ።
የጃርት ጠባዩ ነው። ጃርት ይጮኻል እንጂ አይሠራም። ጃርት አያርስም፤ ስታርስ ይጮሃል። ጃርት አይዘራም፤ ስትዘራ ይጮሃል። አያጭድም፤ ስታጭድ ይጮሃል - አለው አባቱ።
ለምን? - ደግሞ ጠየቀ ልጁ።
ጃርት ከጮኸ እየሠራህ ነው ማለት ነው። ፍሬ እያፈራህ ነው ማለት ነው። ጃርት ጠፍ መሬት ላይ አይጮህም። ምርት ያለበት ቦታ ነው የሚጮኸው። ጃርት የራሱ ጉዳይ የለውም፤ የራሱ ሥራ የለውም። የሚችለው በሰው ሥራ ላይ መጮህ፤ እሾህ መርጨት እና ሰብል ማጥፋት ብቻ ነው። ጃርቶች ሲጯጯሁ ከሰማህ ያ ገበሬ እየሠራ ነው ማለት ነው። መሬቱ እያፈራ ነው ማለት ነው። - አለው አባቱ።
እና ምን ይሻላል? አለ ልጅ።
ተዋቸው፧ እኛም እንሠራለን፤ ጃርቶችም ይጩኹ።
እስከ መቼ?
ወጥመድ እስኪገቡ።
ጃርቶች ከጮኹ - በዚያ አካባቢ ምርት አለ ማለት ነው።

ከግድባችን ላይ እጃችሁን አንሱ!
18/07/2025

ከግድባችን ላይ እጃችሁን አንሱ!

የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ሁሉም ሰው አምባሳደር ሆኖ ሊሰራበት ይገባል - ምሁራን*******ትልቋ ሀገር ኢትዮጵያ በባህር በር እጦት ምክንያት የሌሎች ሀገራት ጥገኛ ልትሆን ስለማይገባ የ...
18/07/2025

የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ሁሉም ሰው አምባሳደር ሆኖ ሊሰራበት ይገባል - ምሁራን
*******

ትልቋ ሀገር ኢትዮጵያ በባህር በር እጦት ምክንያት የሌሎች ሀገራት ጥገኛ ልትሆን ስለማይገባ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ሁሉም ሰው አምባሳደር ሆኖ ሊሰራበት ይገባል ሲሉ ምሁራን ገለጹ፡፡

የትውልድ ጥያቄ የሆነ ውየባህረ በር ጉዳይ በፖለቲካው ተዋንያኖች ብቻ የሚነሳ ጉዳይ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚመለከት መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ የሆኑት የእዮብዘር ዘውዴ ተናግረዋል፡፡

የባህር በር ጥያቄ ከታሪካዊ እና ከኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች ባሻገር ከዓለም አቀፍ ሕጎች አንፃር ሊቃኝ እንደሚገባውም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ጉዳዩ የሁላችንንም ጓዳ የሚነካ ብሔራዊ ሃብት መሆኑን በመገንዘብ አንድ አቋም ልንይዝ እና ልናስፈፅወው ይገባል ብለዋል።

“የዓለም አቀፍ ሕግን መሰረት ያደረገ ጥያቄ ጭብጡ ሰላማዊ እንደሆነ ይታወቃል” ያሉት ተመራማሪው፤ ይህን መሰረት በማድረግ ለባህር በር ባለቤትነት መሳካት ያልተቋረጠ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ነው የገለጹት።

እስካሁን የተሰሩ ሥራዎች ኢትዮጵያ ሰፊ የሕዝብ ቁጥር ይዛ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበትን ሁነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ያስረዱ ናቸው ያሉት ደግሞ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የታሪክና ቅርስ ጥበቃ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ሀበሻ ሽኮር (ዶ/ር) ናቸው፡፡

ቢሆንም ዲፕሎማሲያዊ አውታሮችን ማጠናከር፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የኢኮኖሚ መስተጋብርን ማጎልበት እንዲሁም የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ውይይቶችን ማድረግ እና መተግበር ጥያቄያችን መልስ እንዲያገኝ የሚያስችሉ አማራጮች ናቸው ይላሉ፡፡

የባህር በርን በተመለከተ ሁሉም ሰው አምባሳደር መሆን እንዳለበት የሚናገሩት ተመራማሪው፤ የዲያስፖራው ማህበረሰብ የውጭ ምንዛሬን በመላክ፣ በቀይ ባህር ዙሪያ ባሉ ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ ብሎም በገጽታ ግንባታ እና በሀገሩ ጉዳይ በጠበቃ በመሆን የሚጠበቅበትን የቤት ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላክተዋል።

በቀይ ባህር ቅርብ ርቀት ላይ የምትገነው ኢትዮጵያ ተጠቃሚ መሆን እንዳትችል የሚያደርጉ ሴራዎችን ሰብሮ መውጣት እና በሰላማዊ ጥረት የባህር በር ባለቤትነትን ማሳካት እንደሚገባ ምሁራኑ አስረድተዋል።

በአፎሚያ ክበበው

  አጀንዳ የገለጠው ሰላማዊው የባህር በር ጥያቄ‼️የባህር በር ጉዳይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ ዋና አጀንዳ ሆኖ መነሳት ጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ ላለፉት በርካታ ዓመታት የባህር...
16/07/2025

አጀንዳ የገለጠው ሰላማዊው የባህር በር ጥያቄ‼️

የባህር በር ጉዳይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ ዋና አጀንዳ ሆኖ መነሳት ጀምሯል፡፡

በኢትዮጵያ ላለፉት በርካታ ዓመታት የባህር በር ጉዳይ በተለይም በመንግስት ደረጃ እንደ ትልቅ ብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ ሆኖ ሳይነሳ የቆየ ጥያቄ ነው የሚሉት በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር የሆኑት አቶ ሙሉዓለም ሀ/ማርያም ናቸው፡፡

አቶ ሙሉዓለም ሀ/ማርያም ከኢቢሲ ኤፍኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ የባህር በር ጉዳይ ለበርካታ ዓመታት ሳይነሳ የቆየ ከመሆኑ ባለፈ ጉዳዩን የሚያነሱ አካላትን በአሉታዊ መልኩ የመመልከት ችግርም እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ አሁን ያነሳችው የባህር በር ጥያቄ ተሸፍኖ ካለበት እና እንደጥያቄ በማታይነሳበት ሁኔታ ውስጥ ሆነን ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የባህር በር ጉዳይ ትልቁ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳችን መሆን አለበት ብለው ማንሳትታቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ የባህር በር እንደነበራት ሀገር ይህን ጥያቄ ማንሳቷ ተገቢ ነው የሚሉት መምህሩ፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እያደገ በመምጣቱ እንዲሁም በቀጠናው በርካታ ሕዝብ ካላቸው ሀገራት ኢትዮጵያ ዋነኛዋ ስለሆነች የባህር በር ጥያቄው መሰረታዊ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ 95 በመቶ የሚሆነው የገቢና ወጪ ንግድ በጅቡቲ በኩል እንደሚከናወን የጠቆሙት አቶ ሙሉዓለም፤ ከጥቂት ዓመታት ጀምሮ ደግሞ አማራጭ ወደቦችን ለማግኘት እየተሰራም ነው ብለዋል፡፡

አማራጭ ወደቦችን መፈለግ አንዱ መንገድ ቢሆንም ከዘላቂነት አንፃር የራስ የባህር በር ወደብ ያስፈልጋል የሚለው ወሳኝ ነገር ነውም ብለዋል፡፡

ይህንን የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የተጀመረውን ጥረት በማስቀጠል በሰጥቶ መቀበል መርህ እና በዲፕሎማሲ መንገድ ከግብ ማድረስ እንደሚገባም አመላክተዋል።

የዓለም አቀፉ ሕግ የባህር በር ጥያቄውን እንደሚደግፈው ያነሱት መምህሩ፤ ዲፕሎማሲን የመጨረሻው አማራጭ አድርጎ መውሰድ ይቻላል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ የባህር በር ባለቤት ባንሆንም ከሶማሌ ላንድና እና ከሶማሌ ጋር የተደረሱት ስምምነቶች ወሳኝ ምዕራፍ መሆናቸው መናገር እንደሚቻልም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል የሚለው ሃሳብ ዓለማቀፉ ማህበረሰብም እውቅና እየሰጠው መሆኑን አንስተው፤ የአሜሪካ፣ የሩሲያ፣ የፈረንሳይ መንግስታት ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ እየሰጡ ይገኛልም ብለዋል፡፡

በቀጣይም የሌሎችንም አገራት ድጋፍ በማግኘት ከጎረቤት አገራት ጋር መተማማን እስከሚፈጠር ድረስ በርካታ የዲፕሎማሲ ስራዎችን በመስራት የባህር በር ባለቤትነትን ዕድል መፍጠር እንደሚገባ አመላክተዋል።

#አባይ ሚዲያ‼️‼️

የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ በአፍሪካ ቀዳሚ የሚያደርገውን ሰው አልባ የፖሊስ ጣቢያ (Smart Police Station) ለማደራጀት ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ተፈራረመ።...
15/07/2025

የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ በአፍሪካ ቀዳሚ የሚያደርገውን ሰው አልባ የፖሊስ ጣቢያ (Smart Police Station) ለማደራጀት ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ 24/7 አገልግሎት የሚሰጥ ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ ለማደራጀት ሶፍትዌር የማበልጸጉን ስራ ኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰጠ ሲሆን ተቋሙ በበኩሉ የተገልጋዩን ደህንነት ጠብቀው ከ30 በላይ አገልግሎት የሚሰጡ ሶፍትዌሮችን (የፖሊስ ቀጠሮ፣ ወንጀል ሪፖርት ማድረግ፣ የትራፊክ አደጋ ማመልከት፣ የጠፋ ሰው ማመልከቻ፣ የቤት ውስጥ ወንጀሎችን መጠቀም፣ ስርቆትን ማመልከት፣...) የሚያበለጽግ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ በኩል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ሥምምነቱን ተፈራርመዋል።

Address

Bole

1000

Telephone

+251924542559

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ever Light posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share