Ever Light

Ever Light Updates on different situations You can get what you want,if you put here.

25/10/2025
እነሆ መልካም ዜና❶ በቀጣይ ወራቶች የብርን የመግዛት አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ሰፋፊ ተግባራት እንደሚከናወኑ የብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ ለብሉምበርግ መናገራቸውን ጠቅሶ birrmetric...
23/10/2025

እነሆ መልካም ዜና

❶ በቀጣይ ወራቶች የብርን የመግዛት አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ሰፋፊ ተግባራት እንደሚከናወኑ የብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ ለብሉምበርግ መናገራቸውን ጠቅሶ birrmetrics.com በትናንት እትሙ አስነብቧል። ሕገወጥ የገንዘብ አስተላላፊዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና እርምጃ እንደሚወስድ ይጠበቃል።

❷ ኢትዮጵያ በቢሾፍቱ ከተማ የባቡር ልህቀት ማዕከል ለመገንባት $98 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ ወደስራ መግባቷን africaviewfacts.com አስነብቧል። እንደዘገባው የልህቀት ማዕከል በመሆን እንዲያገለግል ታቅዶ ወደትግበራ የተገባው የስልጠናና የምርምር ማዕከል በ 62 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን በዓመት 1,000 ሰልጣኞችን ከኢትዮጵያና ከአፍሪካ ሃገራት በመመልመል ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስልጠና መስጠት የሚችል የአፍሪካ ሕብረት ያስቀመጠውን አጀንዳ 2063 እውን ለማድረግ የሚረዳ ቁልፍ ፕሮጀክት ነው።

❸ ሁለት የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ንግግር ላይ መሆናቸውን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርኪን መናገራቸውን ጠቅሶ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ዘግቧል። ኡልያኖቭስክ እና አውቶቫዝ የተሰኙ ሁለት የአውቶሞቢል ፋብሪካዎች የሀገሪቱን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ምህዳር እያጠኑ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን ላዳ ኤክስፖርት የተሰኘው ኩባንያ ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የአጋርነት ግንኙነት መመስረቱን አምባሳደሩ መግለጻቸውን ዘግቧል።

❹ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ከባድ ተሽከርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ሥምምነት ተፈረመ። የቻይናው ከባድ መኪና አምራች ሻክማን ኩባንያ ከቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በገቡት ውል መሰረት በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈሳሽ ጋዝ የሚሰሩ ከባድ የጭነት መኪኖች ለኢትዮጵያ ገበያ የሚቀርቡ ይሆናል። በተመሳሳይ ከቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ለመገጣጠም እቅድ መያዙን ጠቅሶ የዘገበው ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ነው።


መልካም ቀን ይሁንልን !🙏
ምንጭ ጌትነት አልማው

21/10/2025

Baaleekoo

ጦሩ ወደ አሰብ እርምጃ ጀመረወደ አሰብ ከፍተኛ የሆነ ሃይል ተንቀሳቅሷል። ሻብያን ለመገርሰስ በትጥቅ የሚንቀሳቀሰው የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ጦሩን ወደ አሰብ አቅጣጫ ማንቀሳቀሱ...
19/10/2025

ጦሩ ወደ አሰብ እርምጃ ጀመረ

ወደ አሰብ ከፍተኛ የሆነ ሃይል ተንቀሳቅሷል። ሻብያን ለመገርሰስ በትጥቅ የሚንቀሳቀሰው የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ጦሩን ወደ አሰብ አቅጣጫ ማንቀሳቀሱን አሳውቋል። የኢርትራ መንግስት በዚሁ አቅጣጫ አለ ብሎ ካሰበው የኢትዮጵያ ስጋት ጋር በተያያዘ ጠንከር ያለ የሃይል ክምችት እንዳደረገ ቀደም ብለው ሲወጡ የነበሩ ዘገባወች አመላክተዋል።

ይኸው ታጣቂ በዚሁ አቅጣጫ ከኢርትራ መንግስት ጋር ለአመታት ሲፋለም የቆየ ሲሆን በቀደመው የኢሕአዴግ መንግስት ወቅትም ጠንከር ያሉ ወታደራዊ ድጋፎችን ያገኝ ነበር። የቀይ ባህር ዳርቻን ተተርሶ የሚኖረው የአፋር ህዝብ በኢሳያስ አገዛዝ ከፍተኛ ጭቆና እየደረሰበት ነው በሚል ነፍጥ አንግቦ የተነሳው ቡድኑ፤ በአሁኑ ሰአትም ጦሩን ዳንኪላ ወደተባለ የኢርትራ አፋር ግዛት ፍሊሚያ ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በኤክስ ገጹ ባሰራቸው ተንቀሳቃሽ ምስል አመልክቷል። ተንቀሳቃሽ ምስሉ ታጣቂ ቡድኑ በሚገባ የተደራጀ ትጥቅ ያለው መሆኑን ያሳያል ።

09/10/2025

#ይደመጥ

08/10/2025
 #የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የፕላቲኒየም አሸናፊ ሆነ። #ዋና ስራ አስፈጻሚው የልዩ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ተሸላሚ ሆነዋል።የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ለዓመታ...
08/10/2025

#የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የፕላቲኒየም አሸናፊ ሆነ።
#ዋና ስራ አስፈጻሚው የልዩ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ተሸላሚ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ለዓመታት የዘለቀውን ታማኝነቱን እና ለሀገር ኢኮኖሚ ያበረከተውን ጉልህ አስተዋፅዖ የሚያረጋግጥ ልዩ ዕውቅና ተቀዳጅቷል!

ድርጅቱ በትናንትናው ዕለት በተካሄደው “የግብር ለክብር” መርሃግብር ከፍተኛ ግብር ከፋይ በመሆን የፕላቲኒየም ደረጃ ሽልማትን አግኝቷል። ኢባትሎ ለተከታታይ ዓመታት ከፍተኛ ግብር በመክፈል የሀገሩን ልማት በታማኝነት ሲደግፍ ቆይቷል። በዘንድሮው "የግብር ለክብር" መርሃግብርም፣ ከ30 ልዩ ታማኝ ግብር ከፋዮች መካከል አንዱ በመሆንና በፕላቲኒየም ደረጃ ከፍተኛ ግብር ከፋይ በመሆን፣ሽልማቱን ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እጅ ተቀብሏል።

ከዚህ ታላቅ ሽልማት በተጨማሪ፣ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢባትሎ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) የድርጅቱን ስኬትና የእሳቸውን ታታሪነት መሰረት በማድረግ የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት እንዲሰጣቸው፣ “ምርጥ ዜጋ” በመባል በኢትዮጵያ አየር መንገድ ማንኛውም በረራዎች የቪአይፒ አገልግሎት እንዲያገኙ፣በተጨማሪም ድርጅቱ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዩ ድጋፍ እንደሚያደርግ እንዲሁም በሁሉም የአፍሪካ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች አስፈላጊ ትብብር እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት: ይህ ታላቅ ድል እና ስኬት መሠረቱ “ለጋራ ዓላማ በጋራ የመፅናት” መሆኑን ገልጸው፣ የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች የጋራ ቁርጠኝነትና ትጋት ውጤት መሆኑንም አጽንዖት ሰጥተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ደስታቸውን ከማናጅመንት አባላት ጋር የተጋሩ ሲሆን፣ ኢባትሎ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስን በማዘመን የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማቀላጠፍ ለሀገር ብልጽግና ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ይህ ሽልማት አንዱ መገለጫ መሆኑን በመግለፅ፣ በቀጣይም ድርጅቱ የተሻለ በመስራት ለሀገራችን ብልጽግና የበኩሉን አስተዋፅዖ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይፋዊ ደብዳቤ ልኳል፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እ.አ.አ ጥቅምት 2 2025 በላከው ዲፕሎማሲያዊ ያልሆነ ነገር ግን ይፋዊ ደብ...
07/10/2025

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይፋዊ ደብዳቤ ልኳል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እ.አ.አ ጥቅምት 2 2025 በላከው ዲፕሎማሲያዊ ያልሆነ ነገር ግን ይፋዊ ደብዳቤው የገለጸው ኢትዮጵያ ለጠባብ የፖለቲካ ትርፍ የቀጠናውን ሰላም የሚያደፈርሱ ሃይሎችን እንደማትታገስ ነው የገለጸው፡፡

ደብዳቤው የኤርትራ መንግስት ከህዝባዊ ሓርነት ትግራይ ታጣቂዎች እና የጦርነት ከበሮን ከሚደልቁ የክልል ታጣቂዎች ጋር በመመሳጠር የኢትዮጵያን ሰላም እና መረጋጋት ለማደፍረስ የገንዘብና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ ነው ሲል ይከሳል፡፡….

ባለፈው ሰኔ ወር ላይ የተላከውን ጨምሮ ለሁለተኛ ጊዜ ለተመድ በተላከው ደብዳቤ የኢትዮጵያ ቀጠናዊ ዲፕሎማሲ በውጥረቶች እየተፈተነ መሆኑን ነው የሚያብራራው፡፡

ከ1998-2000 አውዳሚው የድንበር ጦርነት በኋላ ኢትዮጵያና ኤርትራ ለረጅም ጊዜ “ሰላም እና ጦርነት የለሽ” በሆነ ከባቢ ውስጥ ቆይተዋል።

እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን የመጣው የለውጥ አመራር ያንን ውጥረት በመቅረፍ ፖለቲካዊ እርቅ እንዲመጣ የሞራል ሚናን ኢትዮጵያ እንድትጫወት አድርጓል፡፡

በዚህም ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰላም የኖቤል ሽልማትን ያስገኘ ቆራጥ ውሳኔን በመወሰን በሁለቱ ሀገራት መካከል ለረጅም ዓመታት የተዘጋውን ድንበር እስከመክፈት የደረሰ የሰላም መንገድን ተከትለዋል፡፡

ለተመድ የተላከው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደብዳቤ የወቅቱ የሰላም ተነሳሽነት ከኢትዮጵያ ወገን ብቻ የነበረ እና የኤርትራን በጎ ፈቃድ ሙሉ ለሙሉ ያላገኘ ሲል ጠቅሶታል፡፡

ደብዳቤው አስመራ ከህወሀት ታጋዮች ጋር በመተባበር እና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎችን በማስታጠቅ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጣረስ ተግባር እየፈጸመች መሆኑ ነው የሚጠቅሰው፡፡

ኢትዮጵያ ለሰላም ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያረጋግጥ እና ትዕግስት ገደብ እንዳለው በማስጠንቀቅ ላይ ያተኮረ መልእክትንም አያዘ ነው፡፡

ኢትዮጵያ የምታቀርበው የባህር በር ይገባኛል ጥያቄን ኤርትራ እና አጋሮቿ የግዛት ፍላጎት ያለበት አስመስለው አቅርበውታል፡፡

ሆኖም ኢትዮጵያ የባህር መዳረሻ ፍላጎቷ በትብብር እና በኢኮኖሚያዊ ሰቶ መቀበል መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አሳስቧል፡፡

ካይሮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ያጋጠማት አለመረጋጋት ባገኘችው አጋጣሚ ተጠቂነቷን እንድትገልጽ አድርጓት መቆየቱን የሚጠቅሰው ደብዳቤው፣በቀይ ባህር ላይ ስትራተጂያዊ አቀማመጥ ያላትን አምባገነን ኤርትራን አጋር ስለማድረጓ ያትታል፡፡

አዲስ አበባ ለተመድ በላከችው ደብዳቤ ኢትዮጵያ ግልጽ ዲፕሎማሲያዊ መርህን እንደምትከተል አስፍሯል፡፡

ሉዓላዊነት ለድርድር የማይቀርብ መሆኑን በመጥቀስም የኢትዮጵያን ትዕግስት እንደ ፍርሃት የሚያዩ ታሪኳን ያልተረዱ ሲል የሀገሪቱ ጽናት አላማ እንዳለው በመጥቀስ ይቋጫል፡፡

ኢትዮጵያ የኬንያን የመብራት ፈረቃ ማስቀረቷ ተዘገበ፡፡ የኬንያው ካፒታል ኤፍኤም እንደዘገበው ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው የኤሌክትሪክ ሀይል ውስጥ ቀዳሚዋ አቅራቢ አገር ኢትዮጵያ ሆናለች፡፡ በጁን...
04/10/2025

ኢትዮጵያ የኬንያን የመብራት ፈረቃ ማስቀረቷ ተዘገበ፡፡ የኬንያው ካፒታል ኤፍኤም እንደዘገበው ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው የኤሌክትሪክ ሀይል ውስጥ ቀዳሚዋ አቅራቢ አገር ኢትዮጵያ ሆናለች፡፡ በጁን ወር 2025 ባለው መረጃ መሰረት አገሪቱ ከውጭ ከገዛችው የኤሌክትሪክ ሀይል 83 ፐርሰንቱ ከኢትዮጵያ መሆኑን ያስረዳው ዘገባው፣ በዚህ አመት ከኢትዮጵያ የተገዛው ሀይል 1274 ጊጋ ዋት ሀወር መሆኑን ጠቅሷል፡፡ በዚሁ ጊዜ ከኡጋንዳ 225 ጊጋ ዋት ሀወርና ከታንዛኒያ ደግሞ 33 ጊጋ ዋት ሀወር መብራት መግዛቷን ያስታወቀው ዘገባው ጨምሮም በዚህ አመት ኬንያ ከውጭ የገዛችው የኤሌክትሪክ ሀይል በ27 ፐርሰንት መጨመሩን አስታውቋል፡፡

ይህ የሆነው ደግሞ በኢትዮጵያና ኬንያ መካከል የኤሌክትሪክ ግዢ ስምምነት ተግባራዊ መሆን በመጀመሩ ነው ብሏል፡፡ የኬንያ የሀይልና ፔትሮሊየም ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለዜና አውታሩ በሰጠው መግለጫ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል መግዛት መቻሉ ወጪ ለመቆጠብም እንደረዳው አስረድቷል፡፡ በዚህም በአመት 10 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወጪ እንደሚያድንም ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ የተሰኘው የኬንያ ጋዜጣ እንደዘገበው አገሪቱ በሀይል እጥረት ከፍተኛ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅት ከኢትዮጵያ መፍትሄ አግኝታለች፡፡ በዘገባው በኬንያ ውስጥ የመብራት ፈረቃ የነበረ ከመሆኑም በላይ በአንዳንድ አካባቢዎች ለተወሰኑ ቀናት ጨለማ ለመሆን የሚገደዱበት ጊዜም ነበረ፡፡ ‹‹የኬንያን የመብራት ፈረቃ ኢትዮጵያ አስቀርታለች›› ያለው ዘገባው በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ የኬንያው ፕሬዝደንት ዊልያም ሩቶ የክብር እንግዳ በመሆን መገኘታቸውን አውስቷል፡፡

ባለፈው ሰኔ ወር ኬንያ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ ለመግዛት በምትችልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ማድረጓን ጠቅሶም ከህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ በኋላ ተጨማሪ 200 ሜጋ ዋት ለመግዛት ጥያቄ ማቅረቧንም አስታውቋል፡፡
ምንጭ:- ዘሀበሻ

03/10/2025

is it.

ተስፈኞች ከኬንያ ወደ ኔፓል፥ ከኔፓል ወደ ማዳጋስካር፥ ከማዳጋስካር ወደ ሞሮኮ፥ ከሞሮኮ ምንአልባት ወደሆነ አመጽ ወዳለበት ሃገር በጎግል ጫካ አመጽ ሲያስሱ ውለው አመጽ ሲያስሱ ሲያነጉ ብርቱ...
02/10/2025

ተስፈኞች ከኬንያ ወደ ኔፓል፥ ከኔፓል ወደ ማዳጋስካር፥ ከማዳጋስካር ወደ ሞሮኮ፥ ከሞሮኮ ምንአልባት ወደሆነ አመጽ ወዳለበት ሃገር በጎግል ጫካ አመጽ ሲያስሱ ውለው አመጽ ሲያስሱ ሲያነጉ ብርቱው መሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየእለቱ በሚባል ደረጃ ማርሽ ቀያሪ የሆኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን ያደርጋል።

በአንድ ወር ብቻ እውን ከሆኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ውስጥ፦

❶ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ፣
❷ የግዙፉ ኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ ፕሮጀክት ማስጀመር፣
❸ የጎዴ አፈር ማዳበሪያ ግንባታ ሥምምነት እንዲሁም የፕሮጀክት ማስጀመር ሥነሥርዓት (ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር)፣
❹ የኢትዮጵያ አየርመንገድ በቢሾፍቱ ከተማ አቅራቢያ ለሚያስገነባው ግዙፍ አውሮፕላን ጣቢያ የፋይናንስ አቅርቦት ሥምምነት (AfDB)፣
❺ የኑክሌር ማብላያ የፋይናንስ አቅርቦትና የግንባታ ሥምምነት (ከሩሲያው Rosatom ጋር) ፣
❻ የግዙፍ ቤቶች ግንባታ ግብዓት ማምረቻ ሥምምነት (ከቤላሩስ መንግስት ጋር በቅርቡ የሚፈረም ይሆናል)
❼ ግዙፍ የእርሻ ትራክተር ፋብሪካ ግንባታ (ከቤላሩስ መንግስት ጋር በቅርቡ የሚፈረም ይሆናል)
❽ የባቡር መስመር ዝርጋታ ጥናት ሥምምነት (ከጣሊያን ኩባንያ ጋር)
❾ የነዳጅ ማጣሪያ ፕሮጀክት ማስጀመር (ከቻይናው GCL ኩባንያ ጋር)፣
❿ አንደኛ ዙር የጋዝ ምርት የማስመረቅ ሥነሥርዓት፣
⓫ ሁለተኛ ዙር የጋዝ ምርት ፕሮጀክት ማስጀመር፣.......
________________________________________

ተቃዋሚዎች ነን የሚሉት ወንበራቸው ላይ ተወ'ዝፈው አመጽ የተደረገባቸውን ሃገራት እየዘረዘሩ ‟የበሬ ቆለ*ጥ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ዋለች” እንደተባለችው እንስሳ እነሱም የሌሎች ሃገር አመጽ ኢትዮጵያ ውስጥ ይሆናል ብለው ይቃዣሉ ።
ጌትነት አልማው

Address

Bole

1000

Telephone

+251924542559

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ever Light posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share