
13/06/2025
የሕይወት ተስፋችን የተቀመጠው በሃይማኖት መዝገብ ላይ ነው።
"ሃይማኖት እራሱን ለፍጥረቱ በገለጠ በእግዚአብሔር ተስፋ ለምናደርገው ማናቸውንም ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር ሁሉ የሚያስረዳና የሚያስገነዝብ እውነታ ነው፡፡
(በተስፋችን የተቀመጠው በዚህ እውነታ ነው።)
ይኸውም ከሁሉ በፊት የነበረ ሁሉን አሳልፎ የሚኖር ፍጠረትን ሁሉ የፈጠረ ማንኛውም ነገር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ለእርሱ ግን አስገኝ አሳላፊ የሌለበት በአድነት በሦስትነት ያለ ሁሉን ቻይ የማይለወጥ አምላክ መኖሩን ማመን ነው፡፡ሃይ.መቅ.
በዚህ ማመን ስንጸና ምሥክርነታችን ይገለጻል ተስፋችንም ይጸናል።