ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች

ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች በአንድነት በሦስትነት ለሚመሰገን ለሥሉስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ይሁን ።

“ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ። ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ። አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀፀላ መንግሥቱ። አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ፡ ወለኪኒ ይሰግድ ውእ...
02/11/2025

“ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ። ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ። አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀፀላ መንግሥቱ። አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ፡ ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ።”

ትርጉም፦
ድንግል ሆይ የስሙ ምልክት እና የሞቱ መታሰቢያ የተጻፈብሽ ከሚያበራ ወርቅ ይልቅ እንደ እንቁ የጠራ ንፅህና ያለሽ የጊዮርጊስ የመንግሥቱ ሽልማት የአበባ አክሊል ማርያም ሆይ አንቺ ለእርሱ ሁሉን ታሰግጂለታለሽ እርሱም ላንቺ ይሰግዳል

(ማኅሌተ ጽጌ)

01/11/2025

“ጠላቶቼ ኹሉ ይፈሩ፥ እጅግም ይጐስቁሉ” (መዝ.6፥10)

ይህ ጸሎት ታላቅ የኾነ ጥቅም አለው - ጠላቶች ሲያፍሩና ወደ ኋላ ሲሉ! ምን ማለት ነው? በክፉዎች መንገድ የሚኼዱ ሰዎች ሲያፍሩና ወደ ኋላቸው ሲያፈገፍጉ ከክፋታቸው ይመለሳሉና፡፡

አንድ ሰው በፊቱ ወዳለው ገደል ለመውደቅ እየተንደረደረ እንደ ኾነ ስናየው፡- “ወንድሜ ሆይ! የምትሮጠው ወዴት ነው? በፊትህ ያለው’ኮ ገደል ነው” እንደምንለው ኹሉ፥ ክቡር ዳዊትም “ጠላቶቼ ኹሉ ይፈሩ፥ እጅግም ይጐስቁሉ” ሲልም እነዚህ ሰዎች ከክፉና እነርሱን ከሚያጠፋቸው መንገዳቸው እንዲመለሱ እየጸለየ ነው፡፡

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች መጽሐፍ)

 እስኪ ንገረኝ ! ሕፃናት ቤት እንሥራ ብለው የሚጫወቱት ጨዋታና እኛ በዚህ ዓለም የሚያማምሩ ቤቶችን ስንሠራ ልዩነታችን ምንድን ነው? ሕፃናት እራት እናሰናዳ ብለው በሚጫወቱት ጨዋታና እኛ በ...
01/11/2025



እስኪ ንገረኝ ! ሕፃናት ቤት እንሥራ ብለው የሚጫወቱት ጨዋታና እኛ በዚህ ዓለም የሚያማምሩ ቤቶችን ስንሠራ ልዩነታችን ምንድን ነው? ሕፃናት እራት እናሰናዳ ብለው በሚጫወቱት ጨዋታና እኛ በምናዘጋጀው ጣፋጭ ማዕድ ልዩነቱ ምንድን ነው? ምንም ምን ልዩነት የለውም፡፡ እንዲያውም እኛ እንደዚህ በማድረጋችን በእኛ ላይ የሚያመጣው ከፍ ያለ ቅጣት (ኵነኔ) አለው፤ [የሕፃናቱ ግን የለውም፡፡] ይህን የምናደርገው ነገር ፍጹም የጎስቋላነት ተግባር እንደ ኾነ ያልተገነዘብነው እንደ ኾነም ይህ ምንም አያስደንቅም፡፡ ገና እስከ አሁን ድረስ ዐዋቂ ሰዎች አልኾንንምና፡፡ ያን ጊዜ ግን ዐዋቂዎች ስንኾን ግን [ረብ ጥቅም የለውም እንጂ] አሁን የምናደርገው ተግባር ኹሉ የሕፃን ሥራ እንደ ኾነ እናውቃለንና፡፡

ሕፃናት እያለን ስናደርጋቸው የነበሩት ተግባራት ዐዋቂዎች ስንኾን እንንቃቸዋለንና፡፡ ሕፃናት እያለን ግን እነዚህን ልናገኛቸው ብለን አስበን የምንጨነቅባቸው የነበሩ ናቸው፡፡ ሕፃናት ኾነን ገልና ሸክላ ስንሰበስብና ካብ ስንከምር ረጃጅም አጥሮችን ከሚሠሩ ሰዎች እንደማንተናነስ አድርገን እናስብ ነበር፡፡ ነገር ግን እነዚያ ያቆምናቸው የድንጋይ ክምሮች ወዲያውና እዚያው ፈራርሰው የሚወድቁ ነበሩ፤ ጸንተው ቢቆሙም እንኳን የሚሰጡን ረብ አልነበረም፡፡ አሁንም እኛ በዚህ ዓለም የምንሠራቸው የሚያማምሩ ቤቶች ያው እንደ እነዚህ የሕፃንነታችን ጊዜ ካቦች ናቸው፡፡ አሁን የምንሠራቸው ቤቶች ሀገሩ በሰማይ የኾነውን ሰው ተቀብለው ማኖር የሚቻላቸው አይደሉምና፤ እነርሱ ተቀብለው ማኖር አለመቻላቸው ብቻም ሳይኾን በላይ በሰማይ ሀገሩ የኾነ ሰውም በእነዚህ ቤቶች መኖርን የሚሻ አይደለምና፡፡ ሕፃናት የከመሩአቸው ካቦች እኛ በእግራችን ነካ ብናደርጋቸው የሚፈራርሱ ናቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ በመንፈስ ልዑል የኾነ ሰውም እነዚህን እኛ የምንደነቅባቸው ቤቶች የሚመለከታቸው እንደዚህ ነው፡፡ ሕፃናቱ ቤት ብለው የከመሩአቸው ካቦች በእግራችን ነካ ብናደርግባቸውና ብናፈርስባቸው ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ ተመልክተን [የማያስለቅስ ያስለቅሳቸዋል ብለን] እኛ እንደምንስቅ ኹሉ፥ እነዚህ በመንፈስ ልዑላን የኾኑ ሰዎችም እኛ በእነዚህ ቤቶች መፍረስ ስንተክዝ ተመልክተው [በማያሳያዝን ያዝናሉ በማያስተክዝም ይተክዛሉ ብለው] ይስቃሉ፡፡ እንዲያውም መሳቅ ብቻም ሳይኾን ያለቅሳሉ፡፡ ምክንያቱም፡-

[አንደኛ] ርኅሩኀን ናቸው፤

[ኹለተኛ ደግሞ] እኛ ከእነዚህ ቤቶች ጋር ይህን ያህል በመጣበቃችን ምክንያት የሚመጣብን ጉዳት ብዙ የብዙም ብዙ እንደ ኾነ ያውቃሉና ያለቅሳሉ፡፡

ስለዚህ ዐዋቂዎች እንኹን፡፡ እስከ መቼ ድረስ ነው በምድር ላይ የምንንፏቀቀው? እስከ መቼ ድረስ ነው በድንጋዮችና በምድራዊ መኖሪያ ቤቶች ራሳችንን የምናስታብየው? እስከ መቼ ድረስ ነው ዕቃ ዕቃ የምንጫወተው?

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ የማቴዎስ ወንጌል፣ ድርሳን 23፥10)

መራራው እውነት➠ ጳጳሳቱ ብቻ ለምን ?በሰነ-ልቦናው ጦርነት ለተንበረከከው የሶሻል ሚዲያው አቀንቃኝ !ለአሩሲ ኦርቶዶክሳዊያን ሞት የሚመለከተው ጳጳሳቱ ብቻ ይሆኑ ?💔➠የታሉ የአድባራት አስተዳ...
31/10/2025

መራራው እውነት➠ ጳጳሳቱ ብቻ ለምን ?በሰነ-ልቦናው ጦርነት ለተንበረከከው የሶሻል ሚዲያው አቀንቃኝ !
ለአሩሲ ኦርቶዶክሳዊያን ሞት የሚመለከተው ጳጳሳቱ ብቻ ይሆኑ ?
💔➠የታሉ የአድባራት አስተዳዳሪዋች
💔➠የታሉ ሰንበት ት/ት ቤቶች
💔➠የታሉ ማህበራት
💔➠የታሉ መንፈሳዊ ኮሌጆች
💔➠የታሉ ኦርቶዶክሳዊያን ታዋቂ ሰዋች
➠የታሉ ➠የታሉ ➠የታሉ ይህች ቤተክርስቲያን የጳጳስ ብቻ ናት እንዴ ? ንገሩኝ የት ገብ? የሉም?
ውድቀቱ ሁሉም ጋር ነው ።ለመኳነን አንደኞች ነን።አባቶች ካዱን ሁሁ እኛ እራሱ ክደናት የለ ወይ ሟችን በሃይማኖቱ ሳይሆን በብሔሩ እየቦደን እኛ ምን ተቃወምን ምን አረግን መቃወምማ ማንም ይቃወማል ሳሻል ሚዲያ ላይ መፖሰት ቁምነገር አይደለም በአንድነት ቆመክ መታገል ቤተክርስቲያንክን መጠበቅ ካልቻልክ ።አንተ ግን እያረክ ያለከው ብሶት ነው ብሶት ወደ ድል አያመጣም ምክንያት እንጂ 😡😡😡😡

እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዛቱን በመጠበቅ ይገለጣል። ጽንስ ማስወረድ ትልቅ ኃጢአት ነው። ሥራየኛ ሟርተኛ አትሁን። ሙቶ የተገኘውን፣ ደምን፣ ጥሬ ሥጋን መብላት አይገባም። ሐሰተኛ፣ ነገረ ሠሪ...
31/10/2025

እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዛቱን በመጠበቅ ይገለጣል። ጽንስ ማስወረድ ትልቅ ኃጢአት ነው። ሥራየኛ ሟርተኛ አትሁን። ሙቶ የተገኘውን፣ ደምን፣ ጥሬ ሥጋን መብላት አይገባም። ሐሰተኛ፣ ነገረ ሠሪ፣ ሰነፍ አትሁን። ሰውን የማታፍር እግዚአብሔርን የማትፈራ አትሁን። ፊት አይተህ የምታዳላ አትሁን። አትሳደብ፣ አትማል። እውነቱን እውነት ሐሰቱን ሐሰት በል። የምትራቆትበት ምክንያት ሳያገኝህ በማንም ፊት ራቁትህን ከመሆን ተከልከል። በበዓል ሌላ እምነት ካላቸው ጋር አንድ አትሁን። በታመምክ ጊዜ ወደ ጠንቋይ ወደሟርተኛ ሄደህ ለመፈወስ አትሞክር። ሰውነትህን ከክፉ ነገር ሁሉ ከልክለው። አትታበይ፣ ሰውንም አትቀየም። ቂመኛ አትሁን። የቂመኛን ሰው ጸሎት እግዚአብሔር አይቀበለውምና። ከከሓድያን ጋር አንድ ላይ በአንድ ቦታ መጸለይ አይገባም። ከባድ ሕመም ሳያምህ እግዚአብሔር ያዘዘውን ጾም አትሻር። የፈቃድ ጾምን እየጾምክ ሳለ እንግዳ ቢመጣብህ አብረኸው በፍቅር ብላ። በአዋጅ አጽዋማት ግን እንዲህ ማድረግ አይቻልም። እሑድ ጠዋት ማልደህ ወደቤተክርስቲያን ሂድና አስቀድስ። በቅዳሴ ጊዜ ያለምክንያት እትው በሰላም ሳይባል አትውጣ። በዕለተ እሑድ፣ በበዓለ ኃምሳና ከቆረቡ በኋላ መስገድ አይገባም። ከቀዳም ሥዑር ውጭ ቅዳሜን መጾም አይገባም። ንስሓ ገብተህ ሥጋውን ደሙን ተቀበል። እንግዳ ሲመጣ እግሩን አጥበህ ተቀበለው።
❤ምዕራፍ ፳፩
መፍቀሬ ንዋይ አትሁን። ሰዎች ሁሉ በአንተ ዘንድ የከበሩ ይሁኑ። ከራስህ ይልቅ ሰውን ሁሉ አክብር። ከሰው ሁሉ ጋር ሰላማዊ ሁን። ለሰው ሁሉ ጸልይ። ገንዘብ ቢኖርህ ለሌለው ስጥ። አራጣ አትቀበል። ስለእግዚአብሔር ብለህ ትሑት ሁን። ጸብ ክርክርን አትውደድ። ከሰው ወገን ማንንም አትማታ። ሕፃናት ሲያጠፉ ግን ተግሣጽ እንዲሆናቸው አማትበህ ቀስ ብለህ ቅጣቸው። መልከ ክፉ ነው ብለህ ሰውን አትናቅ። ከንቱ ውዳሴን አትፈልግ። ወንድ ልጅ ጸጉሩን አያሳድግ። ጺሙንም አይላጭ። ወንድ ልጅ ጸጉሩን ሲላጭ ጋሜ ቁንጮ መተው የለበትም። ምድራዊውን ሳይሆን ሰማያዊውን ክብር ፈልግ። በመጠን ነው እንጂ አብዝተህ አትመገብ። ወይን በምትጠጣ ጊዜ አንድ ጽዋ ቢበዛ ሁለት ወይም ሦስት ጽዋ ይሁን። ከዚህ በላይ መጠጣትን ግን መጽሐፍ አይፈቅድም። ሰውነትህን አትከተብ፣ አትጠቆር። ወደ ባዕድ ሀገር ብትሄድ ራስህን አታስታውቅ ማለት መምህር ነኝ አባት ነኝ አትበል። ከመጠኑ አብዝተህ ጩኸኽ አትጸልይ።
❤ምዕራፍ ፳፪
ካህናት ሆይ ወደቤተክርስቲያን ከመሄድ ቸል አትበሉ። ካህናት ከሌባ፣ በሐሰት ከሚምል ሰው፣ ንስሓ ካልገባ ከነፍሰ ገዳይ፣ በዝሙት ከምትኖር ሴት፣ ጣዖት ከሚያመልክ፣ ከጠንቋይ፣ ከኮከብ ቆጣሪ፣ ከከሓድያን፣ ከሰካራሞች፣ ግብረ ሰዶምን ከሚፈጽሙ፣ ከሐሰተኞች፣ በጠቅላላው ንስሓ ካልገቡ ኃጢአተኞች መባዕ ሊቀበሉ አይገባም።

@መምህር @በትረማርያም

ቤተ ክርስቲያኗን ለማዳከም እና በሞቷ ትንፋሽ የለሽ እንድትሆን ለማድረግ በቅድሚያ መያዝ አለባቸው ተብለው ታርጌት የተደረጉ የቤተ ክርስቲያን መዋቅሮች እነዚህ ናቸው፦👉ገዳማት👉ማኅበራት👉ጉባኤያ...
30/10/2025

ቤተ ክርስቲያኗን ለማዳከም እና በሞቷ ትንፋሽ የለሽ እንድትሆን ለማድረግ በቅድሚያ መያዝ አለባቸው ተብለው ታርጌት የተደረጉ የቤተ ክርስቲያን መዋቅሮች እነዚህ ናቸው፦
👉ገዳማት
👉ማኅበራት
👉ጉባኤያት
👉የቤተ ክርስቲያን መዋቅር
👉ሰበካ ጉባኤያት
👉ሕዝባውያን የሆኑ ሰባክያን
👉ሰንበት ትምህርት ቤቶች
✍️ለእነዚህ ሁሉ በመጨረሻው ጽፈት ቤት ኮሚቴ ተቋቁሞላቸው በልዩ ደኅንነቶች እንዲታሠሰሱ እየተደረጉ ነው።
ቢያንስ በጋራ ሞታችን መግባባት እንዲያቅተን የሆነው ከምን የተነሣ ነው?ካልን ዋነኛው የእኛ ሰው ከመሰሉ ከተበተኑ ጠቃሽ የጥቅም እጆች የተነሣ ነው።
✍️በአበል እና ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅም አፋቸው እየሸበቡ በመንደር እያቧደኑ፣በተለያየ የማስፈራሪያ መረጃም ጭምር እያሳዩ አፋቸውን የለጎሟቸው ጠቃሽ አባቶች ብዙ ናቸው።
✍️ከክርስቶስ ይልቅ አጥፊውን፣ከወንጌል ቃል ይልቅ የመደመር መጽሐፍን ካልጠቀስን የሚሉ አስመሳይ አታላይ ጉሳንጉሶችም ቀላል አይደሉም።
✍️ጎበዝ ወደ አጎረሱት የሚዞር የቡሆ ዕቃ ብቻ ነው።በጣም ችግራችንን ያባባሱት እነዚህ የቡሆ(የቡኮ)ዕቃዎች ናቸው።
✍️ከሁሉም ሁኔታ በኋላ ማንንም ሳይምሩ ክርስቲያን በመሆኑ ብቻ ያጠፉታል።ዛሬ በእርጥቡ እንዲህ ካደረጉ ነገ በደረቁ የማያቃጥሉት እርጥብ አይኖርም።
✍️መፍትሄው እኛና እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ ሐቀኛ ተግባር ያስፈልገናል።
✍️ከሽማግሎች መፍትሄ ነበረ ግን ጉረሯቸውን የታነቁ ናቸው።ሲኖዶስ ምን እየሠራ ነው? የሚለውን እንተውና ሲኖዶሱ ራሱ የቤተ ክርስቲያን እንዲሆን መሥራት ይጠይቀናል።
✍️እንደ እኔ መረዳት የተፈጥሮ ሞትን እና ትንሣኤ ሙታንን የሚያምኑበት አይመስለኝም።የክርስቶስ ሞቱን እና ትንሣኤውን የሚያምን ሰው ለክርስቶስ መስቀል እንጂ ይህንን ያክል መስሎ ለመኖር አይሳሳም ነበረ።
✍️በሞታችን ከተግባባን በተለያየ አቅጣጫ ከመሳሳብ የጋራ የሆነ አንድ ኦርቶዶክሳዊ የመፍትሄ አቅጣጫ እንምረጥና እውን እናድርግ።

30/10/2025
30/10/2025

ተሳስተው ከሚያሳስቱን ክፍ ሰዎች አቤቱ አድነን😭 #

30/10/2025

ለምን ግን እኛ መፍትሄ አጣን?😭🤔

ማሳሰቢያ፦ስለ ቤተ ክርስቲያን ህልውና የማያሳስበው አባት የምትቀልቡ ምእመናን አስቡበት።
30/10/2025

ማሳሰቢያ፦ስለ ቤተ ክርስቲያን ህልውና የማያሳስበው አባት የምትቀልቡ ምእመናን አስቡበት።

👉መፍትሄው ምንድን ነው?✍️ከምንም በፊት የእውነት ኦርቶዶክስ መሆን፤✍️ኦርቶዶክሳዊ አንድነታችንን ማጥበቅ፤✍️ከዚህ ቀጥሎ ማንንም ሳይጠብቁ በእያሉበት መፈላለግ፤✍️በተለያየ ዘዴ ጥንቃቄን ተላ...
30/10/2025

👉መፍትሄው ምንድን ነው?
✍️ከምንም በፊት የእውነት ኦርቶዶክስ መሆን፤
✍️ኦርቶዶክሳዊ አንድነታችንን ማጥበቅ፤
✍️ከዚህ ቀጥሎ ማንንም ሳይጠብቁ በእያሉበት መፈላለግ፤
✍️በተለያየ ዘዴ ጥንቃቄን ተላብሶ መሰባሰብ፤
✍️አንድ የአረዳድ ቁመና ላይ መድረስ፤
✍️ከአጥፊዎቻችን እና ካለንበት አንጻር ቁመናችንን በያለንበት በደንብ መገምገም፤
✍️የመፍትሄ መንገዶችን መትለም እና የትኩረት አቅጣጫ ማስቀመጥ፤
✍️በዘላቂነት ችግሩ የሚፈታው ምን አይነት ዘዴን ብንጠቀም ነው?ብሎ መለየት፤
✍️በእያለንበት አጭር፣መካከለኛና ረጂም ዕቅዶችን ማቀድ፤
✍️ባለችን አጋጣሚ ወደ ትግበራው መግባት፤
✍️በየትኛው ቦታ ያለን ኦርቶዶክሳውያን የመረጃ ልውውጥ ማድረግ፤
✍️በበቂ ሁኔታ እውነታውን መሠረት ያደረገ የሚድያ ሥራን መሥራት፤
✍️ለድንቡልቡል ደናቁርት ቦታ አለመስጠት፤
ዓለም ሁሉ አንድ ሁኖ እስኪነቃ ምጽአት ይደርሳል።
✍️ከገባቸው እና ከተረዱት ከትቂቶቹ ጋራ መሥራት፤
✍️ነገ ከዛሬ በከፋ መልኩ የእኛ እንዳልሆነ ፍትህ እንደማናገኝ አለመርሳት፤
እንኳን መሞታችን ይቅርና ክርስቲያኖች ፍትህ አጥተው እየሞቱ ነው ብሎ መናገር በሞት የሚያስቀጣ ወንጀል ይሆናል።
✍️ዝም ብሎ ቁጭ ብሎ ከመሞት ለመፍትሄ እየሠሩ ዋጋ መክፈል፤
✍️ቀጠና ከቀጠና፣ክፍለ ሀገር ከክፍለ ሀገር፣ክልል ከክልል መተሳሰር፤
✍️ከዚህ ሥርዓት የኦርቶዶክሳውያንን ፍትህ መጠበቅ ግን ጅልነት ነው።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች:

Share