Aleta Wondo Press

Aleta Wondo Press የአለታ ወንዶንና አጠቃላይ የሲዳማን ክልል የተመለከቱ የተለያዩ መረጃዎችን የሚሰጥ የፌስቡክ ገፅ!! https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

13/04/2026
በአለታ ወንዶ ከተማ የመሠረተ ልማት ውድቀትና የአመራር ብልሹ አሰራር ነዋሪዎችን ለአንገብጋቢ ቅሬታ ዳረገ********************//****************AWP 04/08/201018...
13/04/2026

በአለታ ወንዶ ከተማ የመሠረተ ልማት ውድቀትና የአመራር ብልሹ አሰራር ነዋሪዎችን ለአንገብጋቢ ቅሬታ ዳረገ
********************//****************

AWP 04/08/201018 ዓ.ም [አለታ ወንዶ - ሲዳማ]

በሲዳማ ክልል አንጋፋ ከሆኑ የንግድ ማዕከላት አንዷ የሆነችው የአለታ ወንዶ ከተማ፣ በአሁኑ ወቅት በአስተዳደራዊ ውድቀትና በመሠረተ ልማት መፈራረስ ምክንያት ነዋሪዎቿ መራር አቤቱታ እያሰሙ ይገኛሉ።

ከተማዋ ካላት የንግድና የኢኮኖሚ አቅም አንጻር ማደግ ሲገባት፣ በአመራሩ ቁርጠኝነት ማጣት ምክንያት ወደ ኋላ እየተጎተተች መሆኗን የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

በከተማዋ ዋነኛ ችግር ሆኖ የቀጠለው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት የህዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ ከባድ አድርጎታል።
ለቀናትና ለሳምንታት የሚጠፋው መብራት በከተማዋ በሚገኙ ጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሰ ሲሆን፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ ለማግኘት ደግሞ እናቶችና ህጻናት ረጅም ርቀት ለመጓዝ ተገድደዋል።
ይህ ችግር እየታወቀ ለአመታት መፍትሔ አለማግኘቱ የነዋሪዎችን ቁጣ ቀስቅሷል።

ሌላው በከተማዋ እየታየ ያለው አሳሳቢ ክስተት የወጣቱ ስራ አጥነት መባባስ ነው። ወጣቶች እንደሚገልጹት በከተማዋ የስራ ዕድልም ሆነ ማንኛውም አገልግሎት ለማግኘት ችሎታና እውቀት ሳይሆን "ገንዘብና የዘመድ አዝማድ ትስስር" የግድ አስፈላጊ እየሆነ መጥቷል።
"ገንዘብና ዘመድ ያለው ብቻ አገልግሎት የሚያገኝባት ከተማ ሆናለች" የሚሉት ወጣቶች፣ የፍትሃዊነት መጓደሉ ለስደትና ለተስፋ መቁረጥ እንደዳረጋቸው ይናገራሉ።

ነዋሪዎች ለዚህ ሁሉ ውድቀት ዋነኛ ተጠያቂ የሚያደርጉት የከተማዋን አመራር አካላት ነው። አመራሩ ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ከማገልገል ይልቅ፣ በሙስናና በግል ጥቅም ተሳስሮ ራሱን በማበልጸግ ላይ ተጠምዷል የሚል ሰፊ ወቀሳ እየቀረበበት ይገኛል። ከተማዋ ከመቼውም ጊዜ በላይ ወደ ኋላ እያዘገመች ባለችበት ወቅት፣ አመራሩ በቢሮ ተዘግቶ የመሬትና የሀብት ክፍፍል ላይ ማተኮሩ የከተማዋን እድገት ገድሎታል ተብሏል።

ከሁሉ በላይ የነዋሪዎችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ትኩረት የሳበው፣ አመራሩ ለህዝብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ ነው።
በከተማዋ ያለውን የመሠረተ ልማት ችግር፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር በመቃወም በማህበራዊ ሚዲያ (Facebook) ሀሳባቸውን የሚገልጹ ወጣቶች ከፍተኛ የማስፈራራትና የእስር ሰለባ እየሆኑ መሆናቸው ተጠቁሟል።
"ጥያቄያችንን ከመመለስ ይልቅ እጃችንን በማሰርና በማስፈራራት ዝም ለማሰኘት ይጥራሉ" የሚሉት ወጣቶች፣ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የመናገርና የመጠየቅ መብት አደጋ ላይ መውደቁን በምሬት ይገልጻሉ።

በአጠቃላይ የአለታ ወንዶ ከተማ ነዋሪዎችና ወጣቶች፣ ይህ አይነቱ አምባገነናዊና ሙስና የነገሰበት የአመራር ዘይቤ እንዲቆም በጥብቅ ይፈልጋሉ።
የሚመለከተው የክልልና የፌዴራል መንግሥት አካላት በከተማዋ ያለውን ሁኔታ በአካል ተገኝተው እንዲያዩ፣ የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄ እንዲመልሱና በህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ወከባና እስር በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ ጥሪ ቀርቧል።
Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

စာတို

በአለታ ወንዶ ከተማ የነዳጅ ምዝበራና የባለሥልጣናት እጅ  ህዝቡን በምሬት ላይ ጥሏል!================================AWP  ሚያዝያ 01 2018፣ዓ.ም ሐዋሳ በአለታ ወንዶ...
09/04/2026

በአለታ ወንዶ ከተማ የነዳጅ ምዝበራና የባለሥልጣናት እጅ ህዝቡን በምሬት ላይ ጥሏል!
================================
AWP ሚያዝያ 01 2018፣ዓ.ም
ሐዋሳ

በአለታ ወንዶ ከተማ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ሲገባቸው፣ ከከተማው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመመሳጠር ለህገ-ወጥ ንግድና ለምዝበራ መጋለጣቸውን አፊኒ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ካሰባሰበው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

እንደ መረጃ ምንጮቻችን ገለጻ፣ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት በከተማዋ በሚገኘው ቶታል ማደያ (ዘርዓብሩክ ሆቴል አጠገብ) እና ታች ሼል ማደያ አስገራሚ ድርጊት ተፈጽሟል።
የቀኑን ውክቢያ ተቋቁመው፣ ለሊቱን በሙሉ በሰልፍ ሲጠበቁ የነበሩ አሽከርካሪዎች ባሉበት ሁኔታ፣ በ"አይሱዙ" (Isuzu) ተሽከርካሪዎች በበርሜል የተሞላ ነዳጅ ጭነው ከማደያዎቹ ወጥተዋል።

ይህ ድርጊት የተፈጸመው አሽከርካሪዎች ለነዳጅ እጥረት ተዳርገው ስራ አቁመው ባለበትና ህዝቡ ለትራንስፖርት ችግር ተጋልጦ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ምሬቱን አክሮታል።

ከከተማ አስተዳደሩ ውስጥ የሚገኙ የመረጃ ምንጮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለአፊኒ ሚዲያ እንደገለጹት፣ ይህ ህገ-ወጥ ተግባር የሚከናወነው በከተማዋ አመራር አካላት ቀጥተኛ ድጋፍና መሪነት ነው። የማደያ ባለቤቶችና የአስተዳደር አካላት በፈጠሩት የጥቅም ትስስር፣ ነዳጅ ለህዝብ ከመቅረብ ይልቅ በጥቁር ገበያ እንዲሸጥ እየተደረገ ይገኛል።

"አመራሩ ህግ ከማስከበር ይልቅ ከባለሀብቶች ጋር በመመሳጠር የድሃውን ህዝብ እንጀራ እየነጠቀ ነው" ሲሉ አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የከተማዋ ነዋሪ በቁጭት ተናግረዋል።

የመረጃ ምንጮቻችን ጨምረው እንደሚያመለክቱት፣ እነዚህ አካላት አሁን ላይ በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተውን የጂኦ-ፖለቲካ ውጥረትና የነዳጅ ዋጋ መናር እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመውበታል። "ነዳጅ ከምንጩ ጠፍቷል" የሚል የሀሰት ሰበብ በማቅረብ፣ ያለውን ክምችት ለግል ጥቅማቸውና ለህገ-ወጥ ንግድ እያዋሉት መሆኑን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ይህ ስር የሰደደ የሙስና ሰንሰለት በአለታ ወንዶ ከተማ ነዋሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እየፈጠረ ይገኛል።

የሚመለከተው የክልልና የፌዴራል አካል በከተማዋ አመራሮችና በማደያ ባለቤቶች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ምርመራ እንዲያደርግ ህብረተሰቡ ጥሪውን እያቀረበ ነው።

ዘገባው የአፊኒ ሚዲያና ኮሚዩንኬሽን ነው።

06/04/2026

በአለታ ወንዶ የንግድ ባንክ አገልግሎት መቆራረጥ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ እሮሮ ቀሰቀሰ

I በአለታ ወንዶ ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በየቀኑ በሚያጋጥሙ የ"ሲስተም" እና የ"መብራት" መቆራረጦች ሳቢያ ደንበኞች ለአላስፈላጊ እንግልትና ለኢኮኖሚ ኪሳራ እየተዳረጉ መሆኑ ተገለጸ።

በሲዳማ ክልል የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከልና የቡና ምርት መውጫ በሆነችው አለታ ወንዶ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎት አሰጣጥ ከከተማዋ የንግድ ፍሰት ጋር አለመመጣጠኑ ተገልጋዮችን እያስመረረ ይገኛል። ባንኩ "መብራት የለም" እና "ኔትወርክ ተቋርጧል" በሚሉ ምክንያቶች ስራ የሚያቆምባቸው ሰዓታት መብዛታቸው፣ በከተማዋ ያለውን የገንዘብ ዝውውር ሽባ እያደረገው መሆኑን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ጉዳዩን አስመልክቶ ያነጋገርናቸው የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ባንኩ እንደ አማራጭ ሊጠቀማቸው የሚገቡ የጄነሬተርና የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎቶች አለመኖራቸው ለችግሩ መባባስ ዋነኛ ምክንያት ነው። ይህ መጉላላት በደንበኞችና በባንኩ መካከል ያለውን የ"አገልግሎት ደረጃ ውል" የሚጥስ ከመሆኑም ባለፈ፣ በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት የፋይናንስ ተቋማት ሊያሟሏቸው የሚገቡ ዝቅተኛ የአገልግሎት መስፈርቶችን ያላሟላ መሆኑን ይጠቅሳሉ።

'ሀይ ባይ ያጣው የአለታ ወንዶ ንግድ ባንክ አገልግሎት አሰጣጥ!!'*****************//**************(በኢሳይያስ ጢሞቴዎስ)አለታ ወንዶ ዝም ብላ ከተማ አይደለችም! ከጂቡቲ ...
06/04/2026

'ሀይ ባይ ያጣው የአለታ ወንዶ ንግድ ባንክ አገልግሎት አሰጣጥ!!'
*****************//**************
(በኢሳይያስ ጢሞቴዎስ)

አለታ ወንዶ ዝም ብላ ከተማ አይደለችም! ከጂቡቲ እስከ ሞያለ፣ ከቦረና እስከ መካከለኛው የሀገራችን ክፍል ያሉ የንግድ መስመሮችን የምታስተሳስር፣ የቡናና የፍራፍሬ ምርት ለሀገር ኢኮኖሚ የምታበረክት የኢኮኖሚ ምሰሶ ናት።

ሆኖም በዚህች ስትራቴጂካዊ ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ የሚመጥን አገልግሎት መስጠት ተስኖታል።

"መብራት የለም፣ ሲስተም የለም" — እስከመቼ?

በየቀኑ "መብራት የለም" እና "ኮኔክሽን የለም" በሚሉ ምክንያቶች አገልግሎት ማቋረጥ የንግድ ማህበረሰቡን እያከሰረ፣ ተገልጋዩን ደግሞ ለከፍተኛ እንግልት እየዳረገ ይገኛል።

አንድ የንግድ ባንክ በእንዲህ ያለ ቁልፍ ከተማ ላይ ጄነሬተርና አማራጭ የኔትወርክ መስመር (Back-up system) ሳይኖረው መንቀሳቀሱ በራሱ ትልቅ ጉድለት ነው።

👉ባንኩ ያለበት ህጋዊና ሞራላዊ ግዴታ
የአገልግሎት ደረጃ (Service Level Agreement): ባንኩ ከደንበኞቹ ጋር ባለው ውል መሰረት፣ በማንኛውም ጊዜ ደንበኛው ገንዘቡን እንዲያገኝና ግብይት እንዲፈጽም ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ግዴታ አለበት።

👉የንግድ ህግና መመሪያዎች፦ በኢትዮጵያ የንግድ ህግና በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት፣ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት እንዳይቋረጥ የማድረግና የቴክኒክ ብልሽቶች ሲያጋጥሙ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጠገን ሃላፊነት አለባቸው።

🔑የደንበኛን ጊዜ ማባከንና በቂ ዝግጅት ባለማድረግ አገልግሎት መከልከል ተጠያቂነትን የሚያስከትል ተግባር ነው።

👉ጥሪያችን ለሚመለከተው አካል፦

የአለታ ወንዶ ንግድ ባንክ አመራሮች የከተማዋን የንግድ ፍሰት የሚመጥን ዘመናዊ ጄነሬተርና አስተማማኝ ኔትወርክ በአስቸኳይ እንዲያደራጁ።

የባንኩ የክልል መምሪያ ይህንን ከፍተኛ የመጉላላት ችግር አይቶ ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ

የከተማዋ አስተዳደር የህዝቡን እንግልት ተረድቶ ከባንኩ ጋር በቁርጠኝነት እንዲነጋገር እንጠይቃለን!!

🫵ለዚህ ሁሉ ቁርጠኛና ከወቅቱ ጋር የሚሄድ አመራር ባለመኖሩ ምክንያት ስለሆነ፣ የአመራሩን ኋላ ላይ በዝርዝር በቅርቡ ይዤ እመለሳለሁ።

የአለታ ወንዶ ህዝብ የሚገባውን ክብርና ቀልጣፋ አገልግሎት ያግኝ መልሳችሁ አሻፈረኝ ከሆነ እስከ መጨረሻው ታግለን ህገ መንግሥቱ የሰጠንን መብት ተጠቅመን ህዝባችንን እናስከብራለን!💊
''ኢሶ ነኝ ፍትህ ለአለታ ወንዶ ህዝብ''🙏🏾

ፍቼ ጫምበላላ በዓል በሶሬሳ ጉዱማሌ በድምቀት እየተከበረ ነው!!**********************//********************  !_06/07/2018 የሲዳማ ሕዝብ ዘመን መለወጫ የሆነ...
15/03/2026

ፍቼ ጫምበላላ በዓል በሶሬሳ ጉዱማሌ በድምቀት እየተከበረ ነው!!
**********************//********************

!_06/07/2018

የሲዳማ ሕዝብ ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሐዋሳ ከተማ ሶሬሳ ጉዱማሌ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በበዓሉ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋን (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

እንዲሁም ከተለያዩ የሀገራችን ክፍል የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን የበዓሉ ባለቤት ከኾነው የሲዳማ ሕዝብ ጋር በዓሉን ለማክበር የተገኙ ሲሆን የውጭ ሀገራት ዜጎችም እየታደሙ ይገኛሉ።

ፍቼ ጫምባላላ የአብሮነት፣ የሰላም፣ የፍቅር እና የመረዳዳት እሴቶች ጎልተው የሚታዩበትም በዓል ነው።

በዓሉ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የማይዳሰሱ ቅርሶች ተብሎ ከተመዘገበ ዘንድሮ 11ኛ ዓመቱ ነው።
© etv

Join us our telegram channel :-👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የሐገራችን አውቅ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል ፊቼ ጫምባላላን  ለማክበር ሐዋሳ ከተማ ገቡ።አርቲስቶቹ ሀዋሳ  ከተማ ሲገቡ የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሀ...
12/03/2026

የሐገራችን አውቅ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል ፊቼ ጫምባላላን ለማክበር ሐዋሳ ከተማ ገቡ።

አርቲስቶቹ ሀዋሳ ከተማ ሲገቡ የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ እና የቢሮው ሥራ አመራሮች በ ሀዋሳ ሳውዝ ስታር ሆቴል ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በአቀባበል ሥነ-ስርዓቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጃጎ፤ በዓሉን ከክልሉ ህዝብ ጋር ለማክበር ሀዋሳ መገኘታቸውን አመስግነው በባህል ማስተዋወቅ፣ በኪነ-ጥበቡ እና በቱሪዝም ንቅናቄው ዘርፍ በሙያቸው ለሚያደርጉት አበርክቶ ቢሮው አስፈላጊውን ሁሉ እገዛ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

ለክልሉ ቱሪዝም መነቃቃት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ በታመነው በዚህ " ኑ ወደ ሲዳማ እንሂድ" በተሰኘው የጉዞ እና የጉብኝት መርሐግብር ላይ አንጋፋውን አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬን ጨምሮ አርቲስት ሚካኤል ሚሊዮን፣ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ፣ አርቲስት ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ) አርቲስት መዓዛ ታከለ፣ አርቲስት ካሳሁን ፍሰሃ (ማንዴላ) ፣ አርቲስት እንግዳሰው ሀብቴ (ቴዲ) አርቲስት ማክዳ አፈወርቅ፣ አርቲስት ምህረት ታደሰ (ፒፒሎ) አርቲስት ሶኒያ ኖኦል (ሶሊያና) ተሳታፊዎች ናቸው።

​በዓለም የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ የተመዘገበው የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ "ፊቼ ጫምባላላ" ​ በዓል የሲዳማ አባቶች ዘመንን የመቁጠር ጥበባቸውንና ሀገር በቀል ዕውቀታቸውን ለትውልድ ያስተላለፉበት የሰላም፣ የዕርቅና የአንድነት ተምሳሌት ነው።

ፊቼ ጫምበላላ​ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ ይቅርታ የሚደረግበትና የአብሮነት እሴት የሚጎለብትበት ታላቅ ዕለት ነው።

ተጓዥ ቡድኑ ከዛሬው እለት ጀምሮ በሀዋሳ፣ በይርጋአለም፣ በወንዶገነትና በሌሎችም የክልሉ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እንደሚንቀሳቀስና ጉብኝት እንደሚያደርግ ከክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

© Dire Tube

በዚያን ዘመን ለፎቶ የቀረ ማስታወሻ 💥(በወገኔ ዮሐንስ )ከሲዳማ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና እስከ ብሄራዊ ሊግ ከብሄራዊ ሊግ እስከ ታላቁ የሀገሪቱ ሊግ በሆነው እስከ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር...
06/03/2026

በዚያን ዘመን ለፎቶ የቀረ ማስታወሻ 💥
(በወገኔ ዮሐንስ )

ከሲዳማ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና እስከ ብሄራዊ ሊግ ከብሄራዊ ሊግ እስከ ታላቁ የሀገሪቱ ሊግ በሆነው እስከ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዚያም አልፎ እስከ ዋሊያዎቹ ድረስ ተጫዋቾችን በማፍራት የራሱን የታሪክ አሻራ ፅፎ አልፏል ✌️

በዚያን ዘመን አለታ ከነማን ጨምሮ ይርጋዓለም ከነማን ወንዶ ገነትን ጩኮ ከነማን ዳራ ወረዳን የመሳሰሉ ለእግርኳስ የተፈጠሩ በዘመኑ ግናና ስም የገነቡ ምርጦችን አሳይቶን ያሳለፈ ስታዲየም ነው።

የገናናው የአለታ ወንዶ ከነማ ድንቅ ዘመን ስታዲየም የአለታ ወንዶ ሁለገብ ስታዲየም።

27/06/2016 ዓ.ም

‎አለታ ወንዶ ከተማ አሰተዳደር  ባካኼደው 2ኛ ዙር 48ኛ መደበኛ ጉባኤ ለወደፊት ከተማዋ የምትመራበትን የ10 ዓመት  መዋቅራዊ ፕላን  በማጽደቅ አጠናቀቀ።**********************...
05/03/2026

‎አለታ ወንዶ ከተማ አሰተዳደር ባካኼደው 2ኛ ዙር 48ኛ መደበኛ ጉባኤ ለወደፊት ከተማዋ የምትመራበትን የ10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን በማጽደቅ አጠናቀቀ።
**********************//**********************

‎ 26/2018 ዓ.ም አለታ ወንዶ

የአለታ ወንዶ ከተማ አሰተዳደር ባካኼደው 2ኛ ዙር 48ኛ መደበኛ ጉባኤ ለወደፊት ከተማው የምመራበትን የ10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን በማጽደቅ መጠናቀቁ ተገልጿል።

‎የከተማው ምክት ከንቲባ እና የከተማ ልማትና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ የከተማውን መዋቅራዊ ፕላን ለምክር ቤቱ በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል ።

‎ከተማው ባለፉት ዓመታት መዋቅራዊ ፕላን በጠበቀ መልኩ አለመመራት የከተማውን እድገት እንዳይፋጠን ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረው የማይካድ እውነት ነው

‎ከተማው ለወደፍት የመልማትና ለማደግ ይህ መዋቅራዊ ፕላን መዘጋጀቱ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የምክር ቤቱ አባሌት አፅንኦት ሰጥተው አሰተዋል።

‎በቀጣይነት ይህ ኘላን እሰከ ታች ቀበለ ድረሰ በማውረድ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ተደርገው የጋራ መግባባት እንደምፈጠርም ተብራርቷል ።

‎ምክር ቤቱ በዛሬው ቀን እንድወያይበት በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ተችሏል ።

‎ምክር ቤቱ በቀረበው ሰነድ መነሻ በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረገ ቦኃላ የከተማው ለወደፍቱ የምመራበትን የ10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን በማጽደቅ ጉባኤው ተጠናቋል።

ዘገባው የአለታ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ገፅ ነው።

Join us our telegram channel :-👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

 (በአበበ የሺጥላ) ሰባዎቹ ...ሰማንያዎቹ.... ዘጠናዎቹ....አጅፕ ሰፈር... ማርያም ሰፈር... አለታ ሞላዋሀኪም  ቢባል .... የሱን ያህል ማን ይታወሳል?እጁ መድሀኒት  ነው!እናቶች ...
02/03/2026


(በአበበ የሺጥላ)

ሰባዎቹ ...ሰማንያዎቹ.... ዘጠናዎቹ....

አጅፕ ሰፈር... ማርያም ሰፈር... አለታ ሞላዋ

ሀኪም ቢባል .... የሱን ያህል ማን ይታወሳል?

እጁ መድሀኒት ነው!

እናቶች ቢያምጡ

ጥርስ ቢቦረቦር.... ቢነቃነቅ

ልጅ ቢታመም .... ቢገረዝ

አደጋ ቢደርስ ወረርሽኝ ....

ሀኪሙ ጋሽ አስፋው ነው...ጋሼ!!

እንዲህ እንደዛሬው አለታ ሆስፒታል ሳይኖራት በፊት ፣ የጤና ባለሞያውም ቁጥር በርከት ሳይል አስቀድሞ፣ በትንሿ ጤና ጣብያ (የአሁኑ ፖሊስ ጣብያ) ከነበሩት በጣም ጥቂት የጤና ባለሞያዎች መሀል በቀዳሚነት ምናነሳው ነው ... ጋሼ አስፋው!

የበርካቶቻችን እትብት በሱ እጅ ታብቷል

ያብዛኞቻችን መቀመጫ የሱ መርፌ ማህተም አያጣትም

የብዙዎችንን የልጅነት ክንዶችን በክትባት ዳብሷቸዋል

ፍንክቶቻችንን እያባበለ እንደ ጨርቅ ቀምቅሟል...

የህመማችንም የመዳናችንም ትውስታ ነው ጋሼ አስፋው!

እንዲያው በጥቅሉ... ጋሼ is pure childhood nostalgia! 😘

ታድያ ... ምንስ ሀኪም ቢሆን ሰውም አይደል? ምንስ ብርቱ ቢሆን ሰውም ነውና ደካሚ አይደል?... ቀሪ?

ሁሉም ሊያበቃ... ትርፉ ትዝታ ብቻ ሊሆን ግድ ሆነና

ይሄው .....

ተግባቢውን

ሽቅርቅሩን

እጀ መድሀኒቱን

የነ ተስፉን፣ አበባየሁን፣ህይወትን ፣ሲሳይን ... መንታዎቹን... ትንንሾቹን እና ደግሞ የኛና የብዙዎቹን አባት .....

ሀኪሙን... ጋሼ አርብ እለት ቀበርነው 😢😢

ነፍስህ በሰላም ትረፍ!😢

አስፋው ደንጊሶ ገመዳ (ከ 1946 - 2018)

Address

Aleta Wondo, Sidama
Wendo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aleta Wondo Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share