Aleta Wondo Press

Aleta Wondo Press የአለታ ወንዶንና አጠቃላይ የሲዳማን ክልል የተመለከቱ የተለያዩ መረጃዎችን የሚሰጥ የፌስቡክ ገፅ!!

የችሎት ዜና!********  08/08/2018 ዓ.ም| አለታ ወንዶበአለታ ወንዶ ከተማ ዴላ ቀበሌ፡አንደኛ ተከሳሽ ኤፍሬም ብርሃኑ ዕድሜው 24ሁለተኛ ተከሳሽ የአብሥራ ተስፋዬ ዕድሜው 23ሶስተኛ...
17/04/2025

የችሎት ዜና!
********
08/08/2018 ዓ.ም| አለታ ወንዶ

በአለታ ወንዶ ከተማ ዴላ ቀበሌ፡
አንደኛ ተከሳሽ ኤፍሬም ብርሃኑ ዕድሜው 24
ሁለተኛ ተከሳሽ የአብሥራ ተስፋዬ ዕድሜው 23
ሶስተኛ ተከሳሽ አዜብ አሰፋ ዕድሜዋ 22
አራተኛ ተከሳሽ ፍርደዎስ ገበየሁ ዕድሜዋ 20 ሲሆን

በቀን 17/05/2017 ዓ.ም የግል ተበዳይ አቤል አባይ የተባለ ግለሰብ፤ ከምሽቱ 7:30 ገደማ “ሀበሻ ሆተል” በመባል በሚታወቀው ሆቴል ከለበት፤ ሶስተኛ ተከሳሽ አባብላው ከሆቴሉ አቅፋ አስወጥታ እየኼደች፤ አራተኛ ተከሳሽ ከኃላ በመከተል እያለች፥ አንደኛ ተከሳሽ አንገቱን በመውጋትና በማረድ፤ ሁለተኛ ተከሳሽ ጀርባውን በመውጋት የግድያ ወንጀል መፈፀማቸው በተከሳሾች መዝገብ ሰነድ ማረጋገጥ ተችሏል።

በዚህ መሠረት ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአለታ ወንዶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት 8/8/2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት፤ ሆን ብለው የግድያ ወንጀል በመፈፀማቸው፡ አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሽ የዕድሜልክ ፅኑ እስራት፤ ሶስተኛ ተከሳሽ 20 ዓመት፤ አራተኛ ተከሳሽ 18 በፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውስኖ፤ ወደ ይርጋለም ማረሚያ ተልከዋል።

መረጃው የአለታ ወንዶ ከተማ ፖሊስ ፅሕፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ነው።

Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

በዛሬው ዕለት የአለታ ወንዶ ከተማ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ማን ናቸው? *******************//*****************...
09/04/2025

በዛሬው ዕለት የአለታ ወንዶ ከተማ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ማን ናቸው?
*******************//********************

የአለታ ወንዶ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ 01/08/2017 ዓ.ም ባካኼደው ስብሰባ፤ አቶ ሳሙኤል ቦጋለ የከተማ አስተዳደር ከንቲባ፤ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ፤ አቶ በለጠ ጥበቡ የከተማው የግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ እንዲሁም፥ አቶ ንጉሴ ጋዊቻ የከተማው ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾሟል።
***
ከተሿሚዎቹ መሀከል: በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ማን ናቸው?

ትውልድና ዕድገታቸው በአለታ ወንዶ ከተማ ሲሆን፤ ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አንስቶ እስከ መሠናዶ በተወለዱባት ከተማ እንደተከታተሉ የታሪክ ማህደራቸው ያትታል።
...

በGIS (ጂ.አይ.ኤስ) እና በUrban Engineering በጀመረ የትምህርት ዝግጅታቸው፥ በሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ከከፍተኛ ባለሙያነት እስከ Cadastral Survey expert፤ የማዘጋጃ ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የከተማ ፕላን ዘርፍ ኃላፊ ሆነው፡ በከተማዋ እንደሰሩ የሚነገርላቸው አቶ ሚንጃሞ፥ የተለያዩ የዓለም ከተሞችን፡ የዕድገት ልምድና ተሞክሮ ተዟዙረው እንደሰለጠኑ ይወሳል።
***
በዓለም ከተሞች ፎረም፤ በጃፓኗ ቶኪዮ የከተሞች ሥልጠና፤
የኬንያዋን ናይሮቢ፥ የአረቦችን ዱባይ የከተሞች አሰፋፈር ዕድገት ሁኔታ እንደቃኙ ታሪካቸው ያስረዳል።

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መዲና ሀዋሳ፤ አሁን ያላትን የዕድገት ቁመናና መልክ እንድትይዝ፥ የአቶ ሚንጃሞ እጅ እንደታከለባት ይወሳል።

እንደ አለታ ከተማ ያሉ ለማደግ ምቹ ዕድልና ሁኔታ እያላቸው፤ የተሻለ በትምህርትና በሥራ ልምድ የታገዘ ልምድ ያለው አመራር በማጣቷ፤ ወደኃላ እየተጎተተች ላለች ከተማ እንደ ሚንጃሞ ያሉ አመራሮች ያስፈልጓታል።

አለታ ወንዶ ከተማ ከዕድሜዋ ልክ የሚታይ የልማት፤ የመልካም አስተዳደርና የመሠረተ ልማት አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ፥ በዘርፉ የተማሩ ብቁ የሆኑ፤ በተግባርና በውጤት የተደገፈ ሙያ ያካበቱ አመራሮች በሚያስፈልጉበት ጊዜ፤ እንደ ሚንጃሞ ገላግሌ ያሉ አመራርን አግኝታለች።

አወድሰን የተቀበልናቸው አዲስ አመራሮቻችን በተወደሱበት ልክ ለህዝቡ የሚጠቅም፤ ይኽ ነው ተብሎ የሚነገር ሥራ ሲሰሩ ማወደሳችንን የምንቀጥል ሲሆን፥ የራሳቸውን ሀብትና ገፅታ ለመገንባት የህዝብ ወንበር ይቆናጠጡ ዘንድ ደግሞ አንፈቅድም።

መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸውም ከወዲሁ እንመኛለን።

  01/08/2017 ዓ.ምupdate news የአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ አቶ ሳሙኤል ቦጋለ የከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ምክት...
09/04/2025

01/08/2017 ዓ.ም
update news
የአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ

አቶ ሳሙኤል ቦጋለ የከተማ አስተዳደር ከንቲባ

አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ

አቶ በለጠ ጥበቡ ከየከተማው የግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ

አቶ ንጉሴ ጋዊቻ የከተማው ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾሟል።

መረጃው የአለታ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ገፅ

ዜና ሹመት*********  01/08/2017የአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት 01/08/2017 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ አቶ ሳሙኤል ቦጋለን የከተማው ከንቲባ አ...
09/04/2025

ዜና ሹመት
*********

01/08/2017
የአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት 01/08/2017 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ አቶ ሳሙኤል ቦጋለን የከተማው ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

ከተማዋን ባለፉት አስራሰባት ወራት ገደማ በከንቲባነት ሲያስተዳድሯት የነበሩት አቶ ባራሳ ባልጉዱ፤ በቦታው ተገኝተው ለአዲሱ ተሿሚ ርክክብ አድርገዋል።

አዲስ ስለተሾሙት ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ቦጋለ ዝርዝር መረጃ የምናቀብ ይሆናል ።

መረጃው የከተማው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ገፅ ነው ።

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ    09/07/2017 ዓ.ም
18/03/2025

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

09/07/2017 ዓ.ም

ድምፃዊት ትብለጥ ተከሰተ ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣት!**********************//*****************  10/03/2017 ዓ.ምየኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ 2017 ዓ....
19/11/2024

ድምፃዊት ትብለጥ ተከሰተ ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣት!
**********************//*****************
10/03/2017 ዓ.ም

የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ 2017 ዓ.ም ባዘጋጀው ሀገር አቀፍ “ክብር ለጥበብ” የተሰኘ፤ ለተለያዩ የጥበብ ሰዎች የእውቅና መርሀ ግብር አዘጋጅቷል።

በመርሃግብሩ ላይ በሙዚቃ ዘርፍ ለድምፃዊት ትብለጥ ተከስተ ዕውቅናና ሽልማት ተሰጥቷታል።

ድምፃዊት ትብለጥ ተከስተ በሀገራችን የሙዚቃ እንዱስትሪ በተለይም በተለያዩ በሲዳሙ-አፎ ዜማዎች የምትታወቅ፥ ስመጥርና ግንባርቀደም የጥበብ ሰው ናት።

Follow us
Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

ዜና ዕረፍት *******  23/01/2017አለታ ወንዶ አቶ ሜልሜላ ሻላሞ ከዚህች ዓለም በሞት ተለዩ!!**************//**************አቶ ሜልሜላ ሻላሞ ከአባታቸዉ አቶ ሻላሞ...
03/10/2024

ዜና ዕረፍት
*******
23/01/2017
አለታ ወንዶ

አቶ ሜልሜላ ሻላሞ ከዚህች ዓለም በሞት ተለዩ!!
**************//**************

አቶ ሜልሜላ ሻላሞ ከአባታቸዉ አቶ ሻላሞ ኖቴ እና ከእናታቸዉ ወ/ሮ ቡኩሎ ያኡ በ1937ዓ.ም በቀድዉ አጠራር በሲዳሞ ክፍለ-ሀገር ሲዳማ አውራጃ አለታ ወንዶ ወረዳ ሺሻ ማሪያም እንደተወለዱ የሚነርላቸው ሲሆን፤
በአለታ ወንዶ ከተማ በንግድ ሥራና በተለያዩ የአገልግሎት ስራዎች የቆዩ መሆናቸውን እንዲሁም ለሰው ልጅ ባላቸው ቀና አመለካከት ተወዳጅ የነበሩ፤ አስታራቂና መካሪ እንደነበሩ የታሪክ ማህደራቸው ያስረዳል።

አቶ ሜልሜላ ሻላሞ በተወለዱ በ80 ዓመታቸው መስከረም 23/2017 ዓ/ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።
Source Habtamu Petros

Address

Aleta Wondo, Sidama
Wendo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aleta Wondo Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share