Aleta Wondo Press

Aleta Wondo Press የአለታ ወንዶንና አጠቃላይ የሲዳማን ክልል የተመለከቱ የተለያዩ መረጃዎችን የሚሰጥ የፌስቡክ ገፅ!! https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

የአለታ ወንዶ አጠቃላይ ሆስፒታል “የእብድ ውሻ እና ተያያዥ በሽታዎች” ክትባት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ!******************//******************AWP 23/12/2017 ...
29/08/2025

የአለታ ወንዶ አጠቃላይ ሆስፒታል “የእብድ ውሻ እና ተያያዥ በሽታዎች” ክትባት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ!
******************//******************

AWP 23/12/2017 ዓ.ም|አለታ ወንዶ

ሆስፒታሉ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንደገለፀው፤ ከዚህ ቀደም የአከባቢው ማህበረሰብ ይህን ክትባት ለማግኘት ብዙ ርቀቶችን ይጓዝ እንደነበር ጠቅሶ፥ አሁን ደግሞ በሆስፒታሉ የእብድ ውሻ በሽታ ክትባት እና ተያያዥ ህክምናዎች መሰጠት መጀመሩን አስታውቋል።

የእብድ ውሻ በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት መሆኑን የገለፀው ሆስፒታሉ፥ በበሽታው በተለከፉ እንስሳት ንክሻ ማለትም በውሻ፤ በድመት፤ በቀበሮ፤ በተኩላ፤ በጅብ፤ በሌሊት ወፍና በሌሎችም ወደ ጤናማ ሰው ሊተላለፍ የሚችል አደገኛ በሽታ መሆኑን አብራርቷል።

ሆስፒታሉ አክሎም፤ ተጋላጭነት ላለባቸው ሰዎች ለበሽታው ከመጋለጣቸው በፊት አስቀድሞ የመከላከያ ክትባትን መስጠት አንዱ የመከላከያ መንገድ መሆኑንም ጨምሮ ገልጿል።

የተነከሰ ሰው ደግሞ በጤና ማዕከላት የሚሰጠውን ክትባትና ተያያዥ ሕክምና በጊዜ መውሰድ አለበት ያለው ሆስፒታሉ፥ የማንኛውንም የእብድ ውሻ በሽታ ሊያስተላልፉ የሚችሉ እንስሳትን ንክሻ ማወቅ ስለማይቻል፣ ንክሻው ካጋጠመን ሳናቅማማ ክትባቱን መውሰድ እንደሚያስፈልግ መክሯል።

መረጃው የሆስፒታሉ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፅ ነው።
Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

በከተማው የህገወጥ ንግድና የዋጋ ቁጥጥር ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠሉ ተነገረ!****************//*****************AWP 19/12/2017|አለታወንዶበአለታ ወንዶ ከተማ፤ ...
25/08/2025

በከተማው የህገወጥ ንግድና የዋጋ ቁጥጥር ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠሉ ተነገረ!
****************//*****************

AWP 19/12/2017|አለታወንዶ

በአለታ ወንዶ ከተማ፤ የህገወጥ ንግድና የዋጋ ቁጥጥር ስራ በተጠናከረ ሁኔታ እንደቀጠለ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ቦጋለ ገልፀዋል።

የቁጥጥር ሂደቱ በዛሬ ዕለት የቀጠለ ሲሆን፤ የህገወጥ ንግድና የዋጋ ጭማሪን ለመቆጣጠር በተቋቋመ ግብረኃይል አማካኝነት አላግባብ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ ማስጠንቀቅያ ከተሰጠ በኃላ እርምጃ መወሰድ መጀመሩን ከንቲባው ጨምረው አስረድተዋል።

በሌላ በኩል በህገ ወጥ መንገድ ከነዳጅ ማዲያ ዉጪ የተከማቸ ነዳጅ በተደረገ ክትትል በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ያስታወሱት ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ቦጋለ፥
በተቋቋመው የህገወጥ ንግድና የዋጋ ጭማሪ ተቆጣጣሪ ግብረሃይል አማካኝነት፤ እያንዳንዱ የንግድ ተቋም የምርት ዓይነትና የዋጋ ተመን እንዲለጥፉ የመቆጣጠር ስራ እንደሚጠናከር ገልፀዋል።

የከተማው ህብረተሰብም በአላግባብ የዋጋ ጭማሪ እና በህገወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ አካላትን፤ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር፤ ጥቆማ ከመስጠት አንስቶ የተሳለጠና ህጋዊ የንግድ ሂደት በከተማው እንዲዳብር የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

በከተማው “የደመወዝ ማሻሻያ ይደረጋል” መባሉን ተከትሎ፤ አለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር በማድረግ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ።********************...
21/08/2025

በከተማው “የደመወዝ ማሻሻያ ይደረጋል” መባሉን ተከትሎ፤ አለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር በማድረግ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ።
************************//*************************

AWP ነሐሴ 15/2017 ዓ.ም|አለታወንዶ

መንግስት ከመስከረም 1፤ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለመንግስት ሠራተኛዉ ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መወሰኑን በይፋ ማሳወቁን ተከትሎ፤ አላግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱን የከተማው ንግድና ገበያ ልማት ጽሕፈት ቤት አሳውቋል።

የከተማው ንግድና ገበያ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ መንገሻ ኩያራ እንደገለፁት፤ የደመወዝ ማሻሻያ ዉሳኔ ከንግድና ግብይት ስርዓቱ ጋር ምንም የምያገናኘው ጉዳይ እንደሌለ አንስተዋል።

ምርትና አገልግሎት አቅራቢ ተቋማት፤ የደመወዝ ማሻሻዉን በማሳበብ ያለ አግባብ የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ እንድቆጠቡ ያሳሰቡት የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መንገሻ ኩያራ፥ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌላቸውና ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪ እንቅስቃሰዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋል ብለዋል።

አክለውም አቶ መንገሻ ኩየራ፤ ምርት የሚደብቁና ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አስፈላጊዉን እርምጃ ለመውሰድ እንዲቻል፤ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸዉ የፀጥታ አካላት በመታባበር እንዲሰራ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።
Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የABM ትምህርት ቤት ተማሪዎች በክልል ደረጃ ክፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸው ታወቀ።**//*AWP ነሐሴ 05/2017 ዓ.ም|አለታ ወንዶ በአለታ ወንዶ ከተማ የሚገኘው ABM በተሰኘው የግል ትምህ...
11/08/2025

የABM ትምህርት ቤት ተማሪዎች በክልል ደረጃ ክፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸው ታወቀ።
**//*

AWP ነሐሴ 05/2017 ዓ.ም|አለታ ወንዶ

በአለታ ወንዶ ከተማ የሚገኘው ABM በተሰኘው የግል ትምህርት ቤት የሚማሩ ተማሪዎች ዘንድሮ በ2017 ዓ.ም በተሰጠው ክልል አቀፍ የ6ኛ ክፍል ፈተና፤ በአጠቃላይ በክልል ደረጃ ሶስት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ፤ ሁለት ተማሪዎች 1ኛ እና አንድ ተማሪ ደግሞ 4ኛ ደረጃ መያዛቸው ተውቋል።

በሲዳማ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ የፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ነሐሴ 12/2017 ይፋ የተደረገ ሲሆን፥ በውጤት ደረጃ ከአንድ እስከ አስር ያስመዘገቡ ተመሪዎች ዝርዝርም ይፋ መደረጉ ታውቋል።

ABM የተሰኘው ትምህርት ቤት በአለታ ወንዶ ከተማ የሚገኝ የግል ትምህርት ቤት ሲሆን፤ በመምህርነት ሙያና በትምህርት አመራር ከፍተኛ ቅቡልነት ያላቸው ባለሙያዎችን በማሰማራት ሥራውን በይፋ ሲጀምር ሁለተኛ ዓመቱ ነው።

Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

በሲዳማ ክልል የ2017 ዓ.ም 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!ነሐሴ 05/2017ትምህርት ቢሮበሲዳማ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈ...
11/08/2025

በሲዳማ ክልል የ2017 ዓ.ም 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!
ነሐሴ 05/2017
ትምህርት ቢሮ

በሲዳማ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤት ፈተናው በአጭር ጊዜ ውስጥ በቴክኖሎጂ በመታገዝ እርማቱ ተካሂዶ ይፋ ሆኗል።

ተማሪዎችም ከታች በተቀመጡት በሁለት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ ሲሆን
➊ በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ (Web browser Application) ላይ
1) 👉 ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://sidama.ministry.et ለ6ኛ ክፍል ተፈታኞች https://sidama6.ministry.et የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2)👉 በሚመጣው ቅጽ (form) ላይ
የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እናቅ የመጀመሪያ ስም (First Name) በማስገባት
3)👉ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡

❷ በተጨማሪም 👉 በሚለው የቴሌግራም ቦት ላይ በመግባት ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ ሲሆን ለመጀመሪያ
👉start የሚለውን ይጫኑ!
👉በመቀጠልም ክፍልዎን ይምረጡ
👉ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ
👉በመቀጠል የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው ማቅረብ ይችላሉ። ቅሬታቸውንም ለማቅረብ

➌በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ላይ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ

1) 👉 ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://sidama.ministry.et/ #/complaint እና https://sidama6.ministry.et/ #/complaintየሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2)👉 በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ
የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number)እና
የተማሪውን የመጀመሪያ ስም (First Name)በማስገባት
3)👉 የትምህርት ዓይነት አሳይ(Fetch course) የሚለውን ቁልፍ በመጫን
4)👉 ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ
5)👉በመጨረሻም ሪፖርት (Add Complaint) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ።

🎯 ማስታወሻ ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡
ነሐሴ 05/2017 ዓ.ም
ትምህርት ቢሮ

ከ2800 በላይ ተማሪዎች የሚሳተፉበት የ12ኛ ክፍል ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ!******************//*******************AWP 20/11/2...
27/07/2025

ከ2800 በላይ ተማሪዎች የሚሳተፉበት የ12ኛ ክፍል ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ!
******************//*******************

AWP 20/11/2017 ዓ.ም

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በክልሉ ከሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተውጣጡ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ6 ተከታታይ ሳምንታት የሚቆይ ልዩ የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ፤ ፕሮግራሙ የክልሉ መንግስት የተማሪዎችን ዉጤታማነት ለማረጋገጥ እየሰራቸው ካሉ ሥራዎች አንዱ መሆኑን ገልጸው፥ የልዩ ማጠናከሪያ ትምህርቱ ዓላማ መጪው ዓመት ለ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የሚዘጋጁ ተማሪዎችን ከወዲሁ ማብቃት መሆኑን በንግግራቸው አንስተዋል።

“ይህ ጊዜ ነገያችሁን የምትሰሩበት ስለሆነ የቀረበላችሁን ዔድል በሚገባ በመጠቀም ውጤታማ እንድትሆኑ” በማለት የአደራ መልእክታቸውን የቋጩት ኃላፊው፥
ለዚህ ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ለተለዩ መምህራንም፤ ለተማሪዎቹ ውጤታማነት የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ በማለት አደራ ብለዋል።

ሀላፊው አክለውም 2800 የተለዩ ተማሪዎች አስፈላጊው ነገር ሁሉ ተሟልቶላቸው በዩኒቨርሲቲው ቆይተው የልዩ ትምህርቱ ተጠቃሚ ከመሆናቸው በተጨማሪ ቀሪ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችና በሁሉም የክፍል ደረጃ የሚገኙ ተማሪዎች በሙሉ በየአካባቢያቸው ከክረምት በጎ ሥራ አካል ተደርጎ የማጠናከሪያ ትምህርት እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

የዩኒቨርስቲው ምክትል ፕረዚዴንት ዶ/ር እንጅነር ፍስሃ ጌታቸውም በበኩላቸው የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ ለተማሪዎቹ ስኬት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል ገብተው ተማሪዎች ይህን እድል ተጠቅመው ውጤታማ እንዲሆኑ ምክራቸውን ለግሰው መልካም ቆይታን ተመኝተውላቸዋል።

በመጨረሻም ለተማሪዎችና ለመምህራን በተናጠል ስለሚኖራቸው ቆይታ ዝርዝር ኦሪየንተሽን ተሰጥቶ መድረኩ የተጠናቀቀ ሲሆን በነገው እለት የመጀመሪያው ቀን የማጠናከሪያ ትምህርት ይጀመራል።

መረጃው የክልሉ ትምህርት ቢሮ ነው!

Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የሀዘን መግለጫ=====//====AWP 17/11/2017 ዓ.ም| ALETA WONDOየደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ተክሉ ከዚህች ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ። የ...
24/07/2025

የሀዘን መግለጫ
=====//====

AWP 17/11/2017 ዓ.ም| ALETA WONDO

የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ተክሉ ከዚህች ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ።

የኃላፊው ድንገተኛ ሞት ዜና የተሰማው በዛሬው ዕለት ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም ነው።

ከመምህርነት አንስቶ በተለያዩ የመንግስት የሥር ምድቦች እየሰሩ እንደቆዩ የሚነገርላቸው አቶ ሙሉነህ ተክሉ፤ የሞት ዜናቸው እስከተሰማ ድረስ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ፅሕፈት ቤት ኃላፊ ነበሩ።

ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለሥራ ባልደረቦቹ መፅናናትን እንመኛለን።

Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የ 1990ዎቹ አለታ ወንዶ ከነማን የወከለ የእግር ኳስ ቡድን!📷 Wegene Yohannes
22/07/2025

የ 1990ዎቹ አለታ ወንዶ ከነማን የወከለ የእግር ኳስ ቡድን!

📷 Wegene Yohannes

Address

Aleta Wondo, Sidama
Wendo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aleta Wondo Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share