Aleta Wondo Press

Aleta Wondo Press የአለታ ወንዶንና አጠቃላይ የሲዳማን ክልል የተመለከቱ የተለያዩ መረጃዎችን የሚሰጥ የፌስቡክ ገፅ!! https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

የአለታ ፍሬ አልጋ ወራሹ አሰልጣኝ — አምሃ ዘውዱ*******************//**************  04/11/2018 ዓ.ም ውልደቱና ዕድገቱ በሲዳማ ክልል አለታ ወንዶ ከተማ ነው። ባ...
11/07/2026

የአለታ ፍሬ አልጋ ወራሹ አሰልጣኝ — አምሃ ዘውዱ
*******************//**************

04/11/2018 ዓ.ም

ውልደቱና ዕድገቱ በሲዳማ ክልል አለታ ወንዶ ከተማ ነው። ባልተሳካው የተጫዋችነት ህይወቱ ተስፋ ያልቆረጠ፣ ነገውን አስቦ ለእያንዳንዷ ስኬት ዋጋ የከፈለ ትጉህ ሰራተኛ ነው። ከትምህርቱ ጎን ለጎን ጥሩ እግር ኳስ ተጫዋች መሆን ይሻ የነበረው አምሃ በአንድ ወቅት ያስተናገደው ጉዳት በፈለገው ልክ የሚወደውን እግር ኳስ እንዳይጫወት ማነቆ ሆነበት።

አገግሞ ለመመለስ የተቻለውን ሁሉ ቢያደርግም ነገሮች ግን ያንን ያክል ቀላል አልሆኑም።እንደ ቀልድ ስር የሰደደው ጉዳት እግር ኳስ መጫወትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲያቆም አስገደደው። ገና የሦስት ዓመት ልጅ ሳለ ነበር የትውልድ ቀዬውን ለቆ ወደ ሀዋሳ የመጣው። የአክስቱ ልጆች ጋርም ተቀምጦ ኑሮን አንድ ብሎ የጀመረባት ከተማ ወትሮም የሰው ፍቅርን ታውቅበታለችና አምሃንም በዋዛ አለቀቀችውም።

የወላጅ ናፍቆት ሲበረታ ክረምትን ጠብቆ ወደ አለታ ወንዶ ከተማ ያመራል። ምስጋና ለአሁኑ የሀዋሳ ከተማ አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ይሁንና አምሃ ለመጀመሪያ ጊዜ ኳስን ማንከባለል የጀመረው በሸዋ ጨርቃጨርቅ ፕሮጀክት ነበር።ያ ጊዜ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤም አር አይ ምርመራ የሚደረግበት ወቅት በመሆኑ የዚህ ፕሮጀክት ታዳጊዎች በአግባቡ ተመዝነው ለተለያዩ የእግርኳስ ታዳጊ ቡድኖች የመጫወት ዕድልን አግኝተዋል።

አምሃ 2006 ላይ ከገጠመው ጉዳት በፊት ከሸዋ ጨርቃጨርቅ ፕሮጀክት በተጨማሪ ያኔ ትልቅ ስም ለገነቡት ለሴንትራል ሆቴል ፣ ለአለታ ወንዶ ተክሌ ሆቴል እና ለሌላኛው የአለታ ወንዶው ልዩ ሆቴል ተጫውቶ በዋንጫ የታጀቡ ዓመታትን አሳልፏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ31 ዓመታት ትዕግሥት በኋላ ሱዳንን አሸንፎ ለአፍሪካ ዋንጫ ሲበቃ አምሃ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ ደስታውን መቋቋም አቅቶት አልቅሷል።ያ የአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ቡድን ለእርሱም ቢሆን አዲስ የህይወት መንገድ ፈጥሮለታል። "አሰልጣኝ መሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተመኘሁት ያንን ብ/ቡድን ስመለከት ነው።" የሚለው አምሃ "መምህር የነበሩት ጋሽ ሰውነት ያመጡት ስኬት ህልሜን በእውን አሳይቶኛል።" ይላል።

እርግጥ ነው ይህ በወሬ ብቻ የቀረ ምኞት አይደለም።ቀስ በቀስ እየተተገበረ የሚገኝ መሻት እንጂ።አምሃ ከመጀመሪያም የሰው እጅ አልጠበቀም። ገና የ17 ዓመት ታዳጊ እያለ ነበር ቢ ቤስት የተባለ የታዳጊ ፕሮጀክት በዛ ለጋ ዕድሜው በማቋቋም ሙያውን የተቀላቀለው። ቀን ቀን ተማሪ፣ አመሻሽ ደግሞ የእግር ኳስ አስተማሪ የሆነው አምሃ ከዓመታት ቆይታ በኃላ 2011 ላይ ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ እና ማኔጅመንት ኢንጅነሪንግ በመጀመሪያ ድግሪ ተመርቋል።

ወዲያውም በሙያው ስራ አግኝቶ ሀገሩን እያገለገለ ጎን ለጎን ደግሞ ብዙ የለፋበትን ቢ ቤስት ቡድኑን ያሰለጥናል። ይህን እያደረገ እንደምንም አንድ ዓመት ሞላው። "ሰዎች ስራህን እንደቀልድ እንዴት ታቆማለህ።"ይሉኛል።"እኔ ግን ልክ እንደ ስራው ሁሉ ኳሱን ማሰልጠን ማቆም አልችልም።"የሚለው አምሃ የተመረቀበትን ሙያ ሙሉ ለሙሉ ትቶ የሙሉ ጊዜ አሰልጣኝ ሆነ።

የማይታመን ተግባር ቢመስልም እርሱ ለእግር ኳሱ ተሰጥቷልና ሳያቅማማ አድርጎታል። ያመናት እግርኳስ አልካደችውም።ቀስ በቀስ ለተሻለ ማዕረግ አበቃችው እንጂ።ሀዋሳ ከተማን በሲዳማ ልዩ ልዩ ሻምፒዮና አሸናፊ ያደረገው አምሃ፣ የሲዳማ ከ17 ዓመት በታች ቡድንን ደግሞ 2016 ላይ በሀገር አቀፍ ውድድር ለፍፃሜ አብቅቶ በኢትዮ ኤሌክትሪክ በመለያ ምት ተሸንፎ 2ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

ይህ ሰው ከ2 ዓመት በፊት 2014 ላይ የተወለደባትን ከተማ አለታ ወንዶን በአሰልጣኝነት ይዞ በኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውጤታማ በማድረግ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሊግ አብቅቷል። ይህም በአካባቢው የጀግና ያክል ተቆጥሮ እንዲወደድ አድርጎታል። ከአምሃ አፍ ሁሌም የማይጠፋ አንድ አሰልጣኝ አለ። "እሱ ሙያዬን እንዳሻሽልና ሙሉነት እንዲሰማኝ ዋጋ ከፍሎልኛል።"ይላል።ይህ የተባለው ሰው የወቅቱ የመቻል እግርኳስ ክለብ አሰልጣኝ የሆነው ሙሉጌታ ምህረት ነው።

የሀዋሳው ፍሬ ሙሉጌታ ምህረት አምሃ ለፈለገው ነገር ሁሉ ቅርቡ ነበር።አንዳንዴማ የራሱን ቡድን እንዲያሰለጥንና ሙያውን እንዲያሳድግ ያደርገው ነበር። አንዳንዴ ደግሞ ከአምሃ ቡድን ጋር የራሱን ቡድን የወዳጅነት በማጫወት ለታዳጊዎች ልምዱን ያካፍላል። "ለዛሬ መድረሴ አንድም በእርሱ ነው።" ሲል አምሃ ተናግሯል።

2017 ላይ የሲዳማ ከ20 ዓመት በታች ቡድን ዋና አሰልጣኝ ተደርጎ የተሾመው አምሃ ለታመነበት ቦታ የሚመጥን ሰው መሆኑን ለማሳየት ጊዜ አልወሰደበትም። አሰላና ቡራዩ ላይ በነበረው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡናን እየመራ ምድቡን በአንደኝነት አጠናቀቀ።

ሀዋሳ ላይ በነበረው የማጠቃለያ ውድድር ደግሞ በፍፃሜው አዳማ ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሲዳማ ቡናን ለዋንጫ አበቃው። በዓመቱ ዳግም ቡድኑን ለዋንጫ ያበቃው አምሃ ታዳጊ ቡድኑ በመድረኩ ወጥነት ያለውና ኢ-ተገማች እንዲሆን በማድረግ ስኬትን በስኬት ላይ ደርቧል።

የዲ ላይሰንስ ፍቃድ ያለው አምሃ አንድ አሰልጣኝ የሲ ላይሰንስ ፍቃድ እንዲኖረው ክለብ መያዝ አለበት የሚለው የፌዴሬሽኑን ህግ ጠብቆ ከወራት በኋላ ደግሞ ደረጃውን ወደ ሲ ላይሰንስ ያሳድጋል። ለዚህ ዕድገት ሲዳማ ቡና መንገድ ጠርጎለታል።

አምሃ በ2 ዓመት ውስጥ 12 ተጫዋቾችን ለሊጉ ክለቦች አብቅቷል። ዛሬ በሲዳማ ቡና ዋናው ቡድን ውስጥ የሚገኙት አስቻለው ሙሴ ፣ ፍቃዱ ማጃ ፣ አላዛር እያሱና እያሱ ሮንዴ የእርሱ ሙያ ያረፈባቸው ታዳጊዎች ናቸው። በኢትዮጵያ ቡና የሚገኘው ናትናኤል ፍሬው እና ለሀዋሳ ከተማ የሚጫወተው ናትናኤል ሸገሙ እንዲሁ ከሚጠቀሱት መካከል ናቸው።

አምሃ ይናገራል "ህልሜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት እየመራሁ ለዓለም ዋንጫ ማብቃት ነው" ይላል። መማር የማይሰለቸው፣ ለማወቅ የሚጥርና የተማረውን ለመተግበር እንቅልፍ የሚያጣ ሰው መሆኑ ህልሙ ሊሳካ በትክክለኛው መንገድ ላይ ለመገኘቱ ያሳለፈው ህይወት ምስክር ይመስላል።

በአብርሃም ተስፋዬ

#አምሃ
ከኢቲቪ መዝናኛ የፌስቡክ ገፅ የተወሰደ

የአመራር ውጤታማነትና ሕዝባዊ አገልግሎት በተግባር፦ የአቶ ተሻለ ተስፋዬ ጋቼኖ የአስተዳደር ጉዞ*******************************//***************************...
10/07/2026

የአመራር ውጤታማነትና ሕዝባዊ አገልግሎት በተግባር፦ የአቶ ተሻለ ተስፋዬ ጋቼኖ የአስተዳደር ጉዞ
*******************************//***************************

03/11/2018 — አለታ ወንዶ|
በዘመናዊው የሕዝብ አስተዳደር ውስጥ የአንድ መሪ ስኬት የሚለካው ከወንበር የበላይነት ይልቅ፣ ሥልጣንን ወደ ተጨባጭ ማኅበረሰባዊ አገልግሎት መለወጥ ሲቻል ነው። እንደ ገለልተኛ ሕዝባዊ ሚዲያ ተቋማዊ አሠራሮችንና የአካባቢ ልማቶችን ስንገመግም፣ በጎ ተሞክሮዎችንና ውጤታማ አፈጻጸሞችን ነጥሎ ማሳየት ለቀጣይ መልካም አስተዳደር መጎልበት መሠረት መሆኑን እናምናለን።

በዚህ ረገድ በአለታ ወንዶ ወረዳ ከተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች እስከ አለታ ጩኮ ከተማ አስተዳዳሪነት፣ በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ ተሻለ ተስፋዬ ጋቼኖ፣ በዕውቀትና በትሕትና የታገዘ መሪነትን በተግባር እያሳዩ ያሉ የአመራር አካል ናቸው።

ሚዲያችን ይህንን የአመራር ጉዞ ትኩረት የሰጠበት ዋነኛው ምክንያት፣ ግለሰባዊ ውዳሴን ለማቅረብ ሳይሆን፣ በአካባቢያችን የተጀመሩ የልማትና የሰላም ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው እና መሰል ሕዝባዊ ተሞክሮዎች እንዲበረታቱ ለማድረግ ነው።
አቶ ተሻለ በአካዳሚክ ዘርፍ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸውን የላቀ የዕውቀት አድማስ ከመሬት ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናኘት፣ የማኅበረሰቡን የልብ ትርታ እያዳመጡ ዝቅ ብሎ ማገልገልን መርሆ አድርገው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ። ይህ ዕውቀትን መሠረት ያደረገ እና ውጤት ተኮር የሆነ የአመራር ጥበብ (Results-Oriented Leadership) የወረዳውን ሁለንተናዊ የፖለቲካ-ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በአዲስ መልክ በመቅረጽ ረገድ ተጨባጭ ለውጦችን እያስመዘገበ ይገኛል።

የአንድ አካባቢ ዘላቂ ዕድገትና ብልጽግና የሚረጋገጠው ለሕዝብ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በሚሰጡና ተቋማዊ አሰራርን ማሳደግ በሚችሉ ብቁ መሪዎች ትከሻ ላይ በመሆኑ፣ ሚዲያችን ለተጀመሩት በጎ ተግባራትና ለታማኝ ሕዝባዊ አገልግሎት ያለውን ሙያዊ እውቅና ይሰጣል።
ይህ ማበረታቻ የአመራሩን ድክመት ከመጠቆምና የሕዝብ ድምጽ ከመሆን ጎን ለጎን፣ የሚሰሩ በጎ ስራዎችን በማጉላት ሚዲያው ያለበትን ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የታለመ ነው።

አቶ ተሻለ ተስፋዬ ጋቼኖ ለነበረዎት ትጋት እያመሰገንን፣ ይህ ተራማጅና ውጤታማ ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የወረዳው ማኅበረሰብም የበኩሉን እገዛ እንዲያደርግ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

Join us our telegram channel :-👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

በአለታ ወንዶ ከተማ የወላጆች ቀን ተከበረ፤ የ11ኛ ክፍል ተማሪው ሙሉቀን ለማ በ99.69 አስደናቂ ውጤት ታሪክ ሰራ*******************************//**************...
09/07/2026

በአለታ ወንዶ ከተማ የወላጆች ቀን ተከበረ፤ የ11ኛ ክፍል ተማሪው ሙሉቀን ለማ በ99.69 አስደናቂ ውጤት ታሪክ ሰራ
*******************************//*************************

03/10/2018 ዓ.ም አለታ ወንዶ — በአለታ ወንዶ ከተማ እና በወረዳው ስር በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ዓመታዊው የ«ወላጆች ቀን» ትናንት ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ የከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የትምህርት ባለሙያዎች፣ መምህራን፣ ወላጆችና ተማሪዎች በነቂስ ተገኝተዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዶች እና የትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት፥ የወላጆች ቀን መከበር በወላጅ፣ በትምህርት ቤትና በተማሪዎች መካከል ያለውን ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸው፤ በቀጣይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የተተኪውን ትውልድ አቅም ለመገንባት የወላጆች ሚና የማይተካ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

የዘንድሮውን የወላጆች ቀን ልዩና ታሪካዊ ያደረገው በአለታ ወንዶ ከተማ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል 'D' ተማሪ የሆነው ሙሉቀን ለማ ያኣሳ ያስመዘገበው አስደናቂ ውጤት ነው።

ተማሪ ሙሉቀን በዓመቱ መጨረሻ 99.69 አማካይ ውጤት (Average) በማምጣት የዕለቱ የክብር ኮከብ መሆን ችሏል።(pictured)
ተማሪ ሙሉቀን ለማ ያስመዘገበው ይህ አስደናቂ ውጤት፥ ያሳየውን ከፍተኛ የጥናት ትጋት፣ የማይበገር ጥረት እና ተፈጥሯዊ አቅም በግልጽ የሚያሳይ ነው።

በትምህርት ኃላፊዎችና በመምህራኑ ዘንድ ከፍተኛ አድናቆት የተቸረው ሲሆን፥ ይህን መልካም ስነ-ምግባርና የጥናት ባህል ይዞ ከቀጠለ ለወደፊቱ ሀገር የምትኮራበት ትልቅ ደረጃ ላይ እንደሚደርስ ሙሉ እምነት ተጥሎበታል።

በዕለቱ የተገኙት የትምህርት ኃላፊዎች እንደገለጹት፥ ሌሎች ተማሪዎች በሙሉ ከዚህ የወርቅ ተማሪ ትልቅ ትምህርት መውሰድ አለባቸው። ውጤት በትጋትና በጠንካራ ስራ የሚገኝ መሆኑን ተማሪ ሙሉቀን በተግባር ያሳየ በመሆኑ፥ መላው የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እሱን አርአያ በማድረግ ለላቀ ውጤት መትጋት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

ተማሪ ሙሉቀን ለማ እና መሰል ጎበዝ ተማሪዎች በትምህርት ማህበረሰቡ ውስጥ መኖራቸው፥ ሌሎችን የሚያበረታታና የተሻለ ለመስራት ትልቅ የተስፋ ስንቅ የሚሆን በመሆኑ መላው የከተማው ህዝብና በትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ታላቅ ኩራት ተሰምቶታል።

ዘገባው በአለታ ወንዶ የትምህርት መድረክና ከማህበራዊ ሚዲያ የተጠናቀረው ነው።

Join us our telegram channel :-👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የአንድ ወር ደመወዝ ስንብት!በወረቀት ላይ ሲሰፍር፣ 17,838 ብር (በዛሬው ምንዛሬ 140 ብር ለአንድ ዶላር ሲሰላ፣ 127 ዶላር) የአንድ ወር ልፋት ዋጋ ይመስላል። ነገር ግን ይህ ቁጥር፣...
23/06/2026

የአንድ ወር ደመወዝ ስንብት!

በወረቀት ላይ ሲሰፍር፣ 17,838 ብር (በዛሬው ምንዛሬ 140 ብር ለአንድ ዶላር ሲሰላ፣ 127 ዶላር) የአንድ ወር ልፋት ዋጋ ይመስላል። ነገር ግን ይህ ቁጥር፣ በበረሃ እንደሚታይ የውሃ ሽንገላ (mirage) ነው፤ የተስፋ መነሻ እንጂ የእውነት መድረሻ አይደለም። ይህ የአንድ የመንግስት ሰራተኛ ወርሃዊ ደመወዝ ሳይሆን የአንድ ህልም መግደያ መሳሪያ እንዴት እንደሚሆን ደረጃ በደረጃ እንመልከት።

1. የመንግስት ስለት:-በግልጽ የሚታየው ቅነሳ

ሰራተኛው የገንዘቡን ጠረን እንኳ ሳያሸት、 የመንግስት ስለቶች የመጀመሪያውን ድርሻ ይወስዳሉ፦

የገቢ ግብር (እስከ 35%): 6,243.3 ብር

የጡረታ መዋጮ (7%): 1,248.6 ብር

በቅጽበት 7,491.9 ብር ከደመወዙ ላይ ተቦጭቆ ይወሰዳል። ይህ ማለት፣ የላቡ ዋጋ ሆኖ እጁ ላይ የሚደርሰው 10,346.04 ብር (ወይም 74 ዶላር) ብቻ ነው። ገና ከመነሻው፣ ከጠቅላላ ገቢው 42% የሚሆነው ጠፍቷል። ይህ ልክ አንድ ገበሬ ካመረተው እህል ግማሹን ማሳው ላይ ትቶ ወደ ቤቱ እንዲሄድ እንደመፍረድ ነው።

2. የህይወት የማይቀሩት ግዴታዎች (gauntlet)

ያቺ 74 ዶላር፣ የህይወትን የማይቀሩ ግዴታዎች (gauntlet) ለመጋፈጥ ስትገደድ፣ እንደ በረዶ ጸሀይ ስር መቅለጥ ትጀምራለች።

* ለትምህርት ቤት ክፍያ (ለ2 ልጆች): ዝቅተኛው 3,000 ብር (21.4 ዶላር)። ይህ ለልጆቹ የተሻለ ህይወት ለመስጠት የሚከፈል መስዋዕትነት ነው፤ እርሱ ራሱ ለማይኖረው ህይወት የሚከፍለው ዋጋ።

* ለትራንስፖርት: ቢያንስ 1,500 ብር (10.7 ዶላር)። በየቀኑ ወደ ስራ ለመሄድ እና ያችንኑ አነስተኛ ደመወዝ ለማግኘት የሚከፈል መጓጓዣ።

* የኤሌክትሪክ ክፍያ: 1,000 ብር (7.1 ዶላር)። ጨለማን ከቤቱ ለማራቅ የሚከፍለው ዋጋ።

* የውሃ ክፍያ: 300 ብር (2.1 ዶላር)። ለህይወት መሰረታዊ ነገር የሚከፈል ክፍያ።

እነዚህን አራት መሰረታዊ ወጪዎች ብቻ ስንደምር 5,800 ብር (41.3 ዶላር) ይሆናል። አሁን ከሰራተኛው የእጅ ቦርሳ ምን ያህል እንደቀረ እንይ፦

10,346.04 (የገባው) - 5,800 (የወጣው) = 4,546.04 ብር

በሌላ አነጋገር፣ ከወሩ መጨረሻ በፊት 20 ቀናት ሲቀሩት፣ በኪሱ ያለው ገንዘብ 32 ዶላር ብቻ ነው!

3. የማይታዩት ሌቦች—የህልም ገዳዮቹ

ያቺ 32 ዶላር እንኳን በሰላም አታድርም። ሶስት ራሶች ያሉት ዘንዶ (hydra) ሊውጣት ይጠብቃታል፦

1. የቤት ኪራይ አውሬነት
በከተማችን፣ የመንግስት ሰራተኛው ቤተሰቡን ይዞ የሚጠለልበት ባለ አንድ ክፍል ቤት ኪራይ እንኳን ከ 5,000 ብር በላይ ነው። ይህ ማለት፣ የቀረችው 4,546.04 ብር የቤት ኪራዩን እንኳን አትሸፍንም። ገና ከወሩ አጋማሽ ላይ፣ የገንዘብ እጥረት (deficit) ውስጥ ገብቷል።

2. የዋጋ ግሽበት እሳት (Inflation)
የሀገራችን የዋጋ ግሽበት ከ30% በላይ ነው። ይህ ማለት፣ ያቺ በኪሱ ያለችው 32 ዶላር፣ ባለፈው ዓመት ከነበረችው 22 ዶላር ጋር እኩል የመግዛት አቅም ብቻ ነው ያላት። ገንዘቡ በእጁ ውስጥ እያለ ዋጋው ይቀልጣል። ዝነኛው ኢኮኖሚስት ጆን ሜይናርድ ኬይንስ እንዳለው፣ “በዋጋ ግሽበት መንግስታት በድብቅ እና ሳይታወቅ የዜጎቻቸውን ሀብት ሊወርሱ ይችላሉ።” ይህ ሰራተኛ የዚሁ ድብቅ ውርስ ሰለባ ነው።

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) መርዝ
ከቀረችው ገንዘብ ላይ ዳቦ ሲገዛ、 ዘይት ሲሸምት、 ለልጁ ደብተር ሲገዛ 15% ቫት ይከፍላል። ይህ በድህነት ላይ የሚጣል ቀረጥ ነው፤ በህይወት ለመቆየት የሚከፈል ቅጣት።

ስለዚህ፣ ይህ ሰራተኛ በወር 32 ዶላር ይዞ ለቤተሰቡ ምግብ፣ ልብስ ህክምና እና ሌሎች ያልተጠበቁ ወጪዎችን እንዲሸፍን ይጠበቃል። ይህ የሂሳብ ስሌት ሳይሆን、 የጭካኔ ማሳያ ነው። ይህ ሰው የሚኖረው ከደመወዙ ሳይሆን ከእዳ ፣ከእድር እና ከሰዎች ርህራሄ ላይ ተንጠልጥሎ ነው።

ታዋቂው ጸሀፊ ቪክቶር ሁጎ እንዳለው “ድህነት ሰውን ወንጀለኛ ሲያደርገው、 ህብረተሰቡ ደግሞ ወንጀሉን ይቀጣል።” ይህ ሰራተኛ በየወሩ የሚፈረድበት ፍርድ、 በህይወት የመኖር ወንጀል ነው። ደመወዙ የልፋቱ ዋጋ ሳይሆን、 ሊያሸንፈው በማይችለው ውድድር ውስጥ እንዲቆይ የሚሰጠው ወርሃዊ ማስታወሻ ነው። ይህ የአንድ ሰው ታሪክ ሳይሆን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዝምታ የዋጣቸው ዜጎች ህያው ምስክርነት ነው።

(ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኘ)

ሮሪ ሲዳማ (በልጠህ ታይ ሲዳማ)!*******************(ከEBC Sport የተወሰደ) ለዓመታት ሳይታክት በየስታዲየሙ እየዞረ ለቡድኑ ከፍታ ሲል ኪሱን አራቁቶ፣ ያለውን ሁሉ ሰጥቶ ለተ...
21/06/2026

ሮሪ ሲዳማ (በልጠህ ታይ ሲዳማ)!
*******************
(ከEBC Sport የተወሰደ)

ለዓመታት ሳይታክት በየስታዲየሙ እየዞረ ለቡድኑ ከፍታ ሲል ኪሱን አራቁቶ፣ ያለውን ሁሉ ሰጥቶ ለተጓዘው ደጋፊ ሲዳማ ቡና አሁን ከ20ዎቹ ክለቦች እንደ ስሙ በልጦ ታይቷል።

ልባቸው በዚህ ክለብ ፍቅር የተሰረቀ በርካታ ደጋፊዎች ቡድኑን ማየት ደስታቸው ሆኖ ፆም ውለው ፆም አድረዋል። በየስታዲየሙ አጥር ስር የሚሸጡ እንደ አሳንቡሳ ፣ ሸንኮራ ፣ ቆሎና ዳቦ በሻይ ያሉ ምግቦችን እንኳን አንዳንዶቹ በቅጡ መግዛት አይችሉም። እነሱ የሚፈልጉት አንድ ነገር ብቻ ነው። ሲዳማ ቡናን በመከራ ውስጥ ለከፍታ ማብቃት።

በሲዳማ ባህል የተራበ እያለ ጠግቦ ማደር አይቻልም። ተካፍሎ መብላት የዚህ ህዝብ መገለጫ ነው።ይህ ደግሞ ምንም ሳይኖረው ሜዳ ለተገኘው ለዛ ደጋፊ ተስፋው ጭምር ነው።

የዚህ ክለብ የልብ ደጋፊ ከሆኑት መካከል የእያሱ ሲዳን ያክል ታማኝ ማግኘት ይከብዳል። ይህ ወጣት በየስታዲየሙ የፊት ገፅታውን በመቀያየር ተመልካቾችን ያዝናናል። እርሱ ሌላ ስራ የለውም የሙሉ ሰዓት የሲዳማ ቡና ደጋፊ ነው።

ይህ ክለብ ባለበት ሁሉ እርሱ አለ። ክለቡ ፀሐይም ሆነ ዝናብ ሲመታ እያሱንም ይመታዋል። ክለቡ ውጤት ባጣም ባገኘም ጊዜ ሁኔታዎች ሳይቀይሩት በፅናት ቆሟል። በቅርቡ ይህ ወጣት የአቅም ውስንነት ሲገጥመው የክለቡ ደጋፊዎች አስፈላጊውን ድጋፍ አድርገው በሁለት እግሩ አቁመውታል። እዚያ ቤት የደከመን ጥሎ፣ የበረታን ብቻ ይዞ መሻገር አይታሰብም። አንዱ የአንዱን ተካፍሎ ይደጋገፋል እንጂ።እያሱ ሲዳም ዛሬ በሙሉ ጉልበቱ ድጋፉን ቀጥሎ እንደ ሲዳማ ቡና ሁሉ ሻምፒዮን ሆኗል።

እርሱን የሚመስሉ ቁጥራቸው ጥቂት አይደለም። እነርሱ በፅናት የቆሙ ፤ ከመሸነፍ ማሸነፍን የመረጡ ፤ ከዛሬ ይልቅ ነጋቸውን የተመለከቱ ናቸው። ይህ ክለብ በዚህ ውብ ደጋፊ እጅጉን የታደለ ነው።

ሲዳማ ቡና ዓመቱን ሙሉ በየሄደበት የሚያበረታውና የሚያጀግነው አላጣም። አዳማም ሆነ አዲስ አበባ እነርሱ አሉ። ከሁሉ የሚያስገርመው ስራቸው የቀን ተቀን የሆኑ የአካባቢው ተወላጆች ሲዳማ ቡና ጨዋታ ካለው የክለቡን መለያ ለብሰው ስታዲየም ይገኛሉ።ከዚህ ክለብ የግል ህይወታቸው እንኳን አይበልጥም። ስለምን ታዲያ ሲዳማ ቡና ከደጋፊዎች ይበልጣል? ያለእነርሱስ ይህ ክለብ ይህንን አንዴት ማድረግ ቻለ?

ስታዲየም ውስጥ ይህ ደጋፊ “ውጤት ውጤት ውጤት ፤ ዋንጫ ዋንጫ ዋንጫ” ያለባቸው ጊዚያት ጥቂት የሚባሉ አይደሉም። ዛሬ ግን ይህ ሁሉ በደስታ ተቀይሯል።

ይህ ክለብ የ22 ዓመታት የምሰረታ ዕድሜ አለው። ሻምፒዮን ሲሆን ግን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በቅርብ ዓመታት የሊጉ ሻምፒዮን ሆነው ካሳዩት የክልል ክለቦች ጅማ አባ ጅፋር ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ፋሲል ከነማ በመቀጠልም ሲዳማ ቡና አራተኛው ክለብ ነው። ከሊጉ ምስረታ ጀምሮ ከተቆጠረ ግን ሀዋሳ ከተማን ጨምሮ አምስተኛው የክልል ክለብ ሆኗል።

ዘንድሮ የዓመታት ቁጭቱን ለመደምደም በሁሉም ነገር ስል ሆኖ የመጣው ሲዳማ ቡና በሊጉ ጥራት ያለው ስብስብ ካላቸው ክለቦች አንዱ ሆኗል። ያሬድ ባየህ ፣ አቤል ያለው ፣ ሱራፌል ዳኛቸው ፣ ፍቅረእየሱስ ተ/ብርሃን ፣ ዮሴፍ ዮሐንስ ፣ ደግፌ አለሙ ፣ ብሌስ ናጎ ፣ ብርሃኑ በቀለ ፣ መስፍን ታፈሰ ፣ ሬድዋን ናስርና ደስታ ደሙ እና ሌሎችም የዓመት ልፋታቸው አሁን ፍሬ አፍርቷል።

የክለቡ የታዳጊ ቡድን ፍሬ የሆኑት አማካዩቹ አስቻለው ሙሴ እና መላኩ አሰፋም ቢሆኑ ይህንን ቡድን እንኳን በጉድለቱ በሙላቱ ዘመንም ደግፈውታል። በተለይ ከተስፋ ቡድን አድገው ብዙም ሳይጓዙ መንገድ ለሚቀሩ ተስፈኞች የእነዚህ ታታሪ ተጫዋቾች ህይወት አስተማሪ ነው።

የሀሳብና የስነ-ምግባር ባለቤት የሆነው አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹም በታመነበት ልክ ሆኖ ተገኝቷል። እንደተጋጣሚ አቀራረብና መልክ ቡድን የሚገነባው አሰልጣኙ፤ አምና በወላይታ ዲቻ ቤት አብሮት ከሰራው የሀዋሳው ፍሬ ቅዱስ ጋር እየተደጋገፈ ክለቡን ለሌላ ክብር አብቅቷል።

ሲዳማ ቡና በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ከ4 ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ብቻ ሲያሳካ ደጋፊዎች እጅጉን አዝነውና ተጨንቀው ነበር። ያንን አፅናኝ መዝሙር፦

“ ሂንጎሞና ሂጊንኬ ፣ ማጋኖ አራራሚንኬ
ተኔ ቴኤ ዲአንፎሞና ቴቾላ ፋሪሲኖሞና”

የሚለውን በተደጋጋሚ እየዘመሩ አልቅሰዋል። አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ ግን በዚህ አልተደናገጠም። የተዳከመ የሚመስለውን የቡድኑን ስነ-ልቦና ጠግኖ ዳግም ተነሳ። የክለቡን ውል በቅጡ ያልተረዱ አንዳንዶች አዝነውበታል ፤ ያወቁት ግን ከጎኑ ቆመው ከሀዘን ማግስት አብረውት ተደስተዋል። አሁን በሲዳማ ቡና እግርኳስ ታሪክ ከማይዘነጉት አሰልጣኞች መካከል አንዱ ያሬድ ገመቹ ሆኗል።

ለዚህ ክለብ ዋጋ ከከፈሉት መካከል የቀድሞ የቡድኑ አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ አንዱ ነው። ከቀድሞ ዳራ ከነማ እስከ አሁኑ ሲዳማ ቡና ድረስ አንዴ በተጫዋችነት አንዴ ደግሞ በአሰልጣኝነት መሰረት ጥሏል። በተለይ ተጫዋች በነበረበት ወቅት ይርጋለም ሁለገብ ስታዲየም የሚገኘው ደጋፊ የዚህ የቀድሞ ኮከብ ወዳጅ ነበር።

በሲዳማ የማይደራደረው ዘርዓይ ሜዳ ላይ ከመፈንከት እስከ እስከ መደብደብ ብዙ ደርሶበታል። ዛሬ የልጅነት ክለቡ በሊጉ ነግሶ ሲመለከት ምን ይሰማው ይሆን?

በቀድሞ ሲዳማ ዞን ልዩ ልዩ ሻምፒዮና ውድድር ላይ የተገኘው አጥቂው ይገዙ ቦጋለ በቅርብ ዓመታት ለዚህ ቡድን ዕድገት ዋጋ ከከፈሉት አንዱ ነው። አርባምንጭ ከተማ ቤት ሆኖ የቀድሞ የልጅነት ቡድኑ ሻምፒዮን ሆኖ ሲመለከት በእርሱስ አዕምሮ ምን ይመላለስ ይሆን?

ሲዳማ ቡና ካሸነፈ ‘ያስቆጠረው አዲስ ግደይ መሆን አለበት’ እስኪባል ድረስ ስም የወጣለት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋች በዚህ ውጤት ከሚደሰቱት መካከል ነው።

ይህ ቡድን አንድ ቀን የደሞዝ ጥያቄ ተነስቶበት አያውቅም። የተጫዋቾችን ጥቅማ ጥቅምም ቢሆን ሳያጓድል ከፍሏል። ይህ ደግሞ በስነ- ልቦና የጠነከረና በነገሮች በቀላሉ የማይሸነፍ ቡድን አድርጎታል።

የክለቡ የቦርድ አመራሮች መደበኛ ስራቸውን አስተካክለው ሁሌም ስታዲየም ይገኛሉ። ከጨዋታ በፊትም ሆነ በኋላ መልበሻ ክፍል ድረስ ሄደው እዚህ ነን በርቱልን ይላሉ። የክለቡን ውጥንም በየጨዋታው ለተጫዋቾቹ ያስገነዝባሉ። ይኸው ዛሬ ሁሉም ከሻተው ቦታ ተገኝቷል።

ሲዳማ ቡና የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል። ሮሪ ሲዳማ!

በአብርሀም ተስፋዬ

የቀድሞው የአለታ ከነማ እግርኳስ ተጫዋች የነበረው መሃመድ ኑር አረፈ!****************************//*************************  19/09/2018 ዓ.ምየአለታ ...
27/05/2026

የቀድሞው የአለታ ከነማ እግርኳስ ተጫዋች የነበረው መሃመድ ኑር አረፈ!
****************************//*************************

19/09/2018 ዓ.ም

የአለታ ከነማ የቀድሞው ተጫዋችና የፊት መስመር አጥቂ የሆነው መሃመድ ኑር/ማሙዶ ማረፉ ተሰምቷል።

ከዓመት በፊት ህንድ ሀገር ለጉበት ንቅለ ተከላ እንደኼደ የተነገረለት መሃሙድ ኑር፥ ህክምናውን በተሳካ ሁኔታ አከናውኖ ወደ ሀገር ቤትቢመለስም፥ የማረፉ ዜና ከዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ ተሰምቷል።

መሃሙድ ኑር በእግርኳስ ተጫዋችነቱ ደማቅ አሻራ አሳርፎ ያለፈ ጎበዝ ተጫዋች ሲሆን፥ ከህዝቡም ዘንድ ተወዳጅነት ያለው ነው።

በቀድሞው የአለታ ከነማ ተጫዋች ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ፥ ለወዳጅ ቤተሰብ እንዲሁም ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል!!

News Source and 📷 Wegene Yohannes

አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ የአለታ ጩኮ ከንቲባ ሆነው በመሾማቸው፣ የከተማዋ ነዋሪዎች በአዲሱ ሹመት ደስታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ***********************//*******************...
11/05/2026

አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ የአለታ ጩኮ ከንቲባ ሆነው በመሾማቸው፣ የከተማዋ ነዋሪዎች በአዲሱ ሹመት ደስታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ
***********************//*******************

AWP 03/09/2018 ዓ.ም

የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ፣ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ጋርሣሞን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ መሾሙን አስታውቋል።
አዲሱ ከንቲባ የቀድሞውን ተሿሚ አቶ ቶርባ ቶሼን በመተካት ነው ወደ ስልጣን የመጡት።

ሹመቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በአለታ ጩኮ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ የሆነ የደስታ ስሜት ተስተውሏል። ነዋሪዎቹ አዲሱ ከንቲባ ካላቸው የተከማቸ ልምድና የአካዳሚክ ብቃት አንጻር፣ ከተማዋ ለረጅም ጊዜ ስትጠይቃቸው የነበሩ አንገብጋቢ የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ምላሽ ያገኛሉ የሚል ትልቅ እምነት ጥለውባቸዋል።

አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ጋርሣሞ በዘርፉ የበቃ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና በመንግሥት የአመራር እርከኖች ውስጥ ውጤታማነታቸውን ያስመሰከሩ መሪ ናቸው። ከዚህ ቀደም፦
በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ በሲዳማ ክልል መንግሥት መዋቅሮች፣ እንዲሁም በቅርቡ በአለታ ወንዶ ከተማ በነበራቸው የተለያዩ ኃላፊነቶች የሚታዩና ውጤታማ ሥራዎችን ሲያከናውኑ እንደነበር ይታወቃል።

ይህ ካላቸው ሰፊ የመንግሥት ሥራ ልምድና አቅም አንጻር፣ አለታ ጩኮን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ ያሸጋግራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
አለታ ጩኮ ከተማ በአሁኑ ወቅት ተደራራቢ የመሠረተ ልማት ችግሮች የተጋረጡባት ከተማ መሆኗ ይታወቃል።

የመንገድ፣ የውሃ፣ የኤሌክትሪክና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ጥያቄዎች የአዲሱ ከንቲባ ቀዳሚ የቤት ስራዎች እንደሚሆኑ ይገመታል። ይሁን እንጂ አዲሱ ከንቲባ ያላቸውን የአመራር ጥበብና ቁርጠኝነት በመጠቀም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ እንደሚፈቱ በሕዝቡ ዘንድ ያለው ተስፋ እጅግ ከፍተኛ ነው።

የዛሬው የአቶ ሚንጃሞ ገላግሌ ሹመት ለአለታ ጩኮ አዲስ የልማትና የለውጥ ምዕራፍ ይከፍታል ተብሎ ይታመናል። ሕዝቡም ከአዲሱ አመራር ጎን በመቆም ከተማዋን ለመለወጥ ዝግጁ መሆኑን እየገለጸ ይገኛል።
ለአዲሱ ከንቲባ አቶ Minjamo G. Garsamo መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን!

Join us our telegram channel :-👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress

Subscribe our YouTube channel 👇
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

የቀድሞው የአለታ ወንዶ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የማዘጋጃ ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ፣ የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ። **********************/...
11/05/2026

የቀድሞው የአለታ ወንዶ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የማዘጋጃ ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ፣ የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ።
**********************//***********************
03/09/2018 ዓ.ም

የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፣ የቀድሞው የአለታ ወንዶ ከተማ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የነበሩትን አቶ ሚንጃሞ ጋላግሌ ጋርሳሞን፥ የከተማ አስተዳደር ከንቲባነት ሹመት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

አቶ ሚንጃሞ ገላግሌ በአለታ ወንዶ ከተማ አመራርነታቸው በውጤታማነት የሚታወቁ ሲሆኑ፥ በዛሬው ዕለት የቀድሞውን የአለታ ጩኮ ከተማ አስተዳደር ከተማ ከንቲባ አቶ ቶርባ ቶሼን በመተካት ነው ከንቲባ ሆነው የተሾሙት።

13/04/2026
በአለታ ወንዶ ከተማ የመሠረተ ልማት ውድቀትና የአመራር ብልሹ አሰራር ነዋሪዎችን ለአንገብጋቢ ቅሬታ ዳረገ********************//****************AWP 04/08/201018...
13/04/2026

በአለታ ወንዶ ከተማ የመሠረተ ልማት ውድቀትና የአመራር ብልሹ አሰራር ነዋሪዎችን ለአንገብጋቢ ቅሬታ ዳረገ
********************//****************

AWP 04/08/201018 ዓ.ም [አለታ ወንዶ - ሲዳማ]

በሲዳማ ክልል አንጋፋ ከሆኑ የንግድ ማዕከላት አንዷ የሆነችው የአለታ ወንዶ ከተማ፣ በአሁኑ ወቅት በአስተዳደራዊ ውድቀትና በመሠረተ ልማት መፈራረስ ምክንያት ነዋሪዎቿ መራር አቤቱታ እያሰሙ ይገኛሉ።

ከተማዋ ካላት የንግድና የኢኮኖሚ አቅም አንጻር ማደግ ሲገባት፣ በአመራሩ ቁርጠኝነት ማጣት ምክንያት ወደ ኋላ እየተጎተተች መሆኗን የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

በከተማዋ ዋነኛ ችግር ሆኖ የቀጠለው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት የህዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ ከባድ አድርጎታል።
ለቀናትና ለሳምንታት የሚጠፋው መብራት በከተማዋ በሚገኙ ጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሰ ሲሆን፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ ለማግኘት ደግሞ እናቶችና ህጻናት ረጅም ርቀት ለመጓዝ ተገድደዋል።
ይህ ችግር እየታወቀ ለአመታት መፍትሔ አለማግኘቱ የነዋሪዎችን ቁጣ ቀስቅሷል።

ሌላው በከተማዋ እየታየ ያለው አሳሳቢ ክስተት የወጣቱ ስራ አጥነት መባባስ ነው። ወጣቶች እንደሚገልጹት በከተማዋ የስራ ዕድልም ሆነ ማንኛውም አገልግሎት ለማግኘት ችሎታና እውቀት ሳይሆን "ገንዘብና የዘመድ አዝማድ ትስስር" የግድ አስፈላጊ እየሆነ መጥቷል።
"ገንዘብና ዘመድ ያለው ብቻ አገልግሎት የሚያገኝባት ከተማ ሆናለች" የሚሉት ወጣቶች፣ የፍትሃዊነት መጓደሉ ለስደትና ለተስፋ መቁረጥ እንደዳረጋቸው ይናገራሉ።

ነዋሪዎች ለዚህ ሁሉ ውድቀት ዋነኛ ተጠያቂ የሚያደርጉት የከተማዋን አመራር አካላት ነው። አመራሩ ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ከማገልገል ይልቅ፣ በሙስናና በግል ጥቅም ተሳስሮ ራሱን በማበልጸግ ላይ ተጠምዷል የሚል ሰፊ ወቀሳ እየቀረበበት ይገኛል። ከተማዋ ከመቼውም ጊዜ በላይ ወደ ኋላ እያዘገመች ባለችበት ወቅት፣ አመራሩ በቢሮ ተዘግቶ የመሬትና የሀብት ክፍፍል ላይ ማተኮሩ የከተማዋን እድገት ገድሎታል ተብሏል።

ከሁሉ በላይ የነዋሪዎችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ትኩረት የሳበው፣ አመራሩ ለህዝብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ ነው።
በከተማዋ ያለውን የመሠረተ ልማት ችግር፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር በመቃወም በማህበራዊ ሚዲያ (Facebook) ሀሳባቸውን የሚገልጹ ወጣቶች ከፍተኛ የማስፈራራትና የእስር ሰለባ እየሆኑ መሆናቸው ተጠቁሟል።
"ጥያቄያችንን ከመመለስ ይልቅ እጃችንን በማሰርና በማስፈራራት ዝም ለማሰኘት ይጥራሉ" የሚሉት ወጣቶች፣ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የመናገርና የመጠየቅ መብት አደጋ ላይ መውደቁን በምሬት ይገልጻሉ።

በአጠቃላይ የአለታ ወንዶ ከተማ ነዋሪዎችና ወጣቶች፣ ይህ አይነቱ አምባገነናዊና ሙስና የነገሰበት የአመራር ዘይቤ እንዲቆም በጥብቅ ይፈልጋሉ።
የሚመለከተው የክልልና የፌዴራል መንግሥት አካላት በከተማዋ ያለውን ሁኔታ በአካል ተገኝተው እንዲያዩ፣ የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄ እንዲመልሱና በህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ወከባና እስር በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ ጥሪ ቀርቧል።
Join us our telegram Channel👇
https://t.me/httpstelegrammealetawendopress
Subscribe our YouTube channel ??
https://youtube.com/?si=gBoNTIgrGQVo-ErC

စာတို

Address

Aleta Wondo, Sidama
Wendo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aleta Wondo Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share