Endalk Fm

Endalk Fm የሀሳብ ድሀ ላላመሆን መረጃ ሀብት ማድረግ።

ስንቴ ከጎናችን ከተለየ ሰስት ቀናት አለፈ።ይህ ፎቶ የተነሳንበት አጋጣሚ ሳስብ ለስራ ያለው ጉጉት ነው። ስራ ለመውጣት እየተሯሯጠ እያለ እኔ ሙባረክ ጌረሞ ሄኖክ ተክሌ ሞቅ ያለ ጨዋታ ይዘን ...
06/01/2026

ስንቴ ከጎናችን ከተለየ ሰስት ቀናት አለፈ።

ይህ ፎቶ የተነሳንበት አጋጣሚ ሳስብ ለስራ ያለው ጉጉት ነው። ስራ ለመውጣት እየተሯሯጠ እያለ እኔ ሙባረክ ጌረሞ ሄኖክ ተክሌ ሞቅ ያለ ጨዋታ ይዘን ነበር። ሳቃችን ማርኮት እየተቻኮለም ጠጋ አለ ።ሙባሪክ ፎቶና ቪድዮ መቅረፅ ጀመረ። ሳቃችን ገታ አረግነው።

የኔ ከርታታ ነፍስህ በሰላም ትረፍ።ሌላ ምን ይባላል ።

አንደበቱ ከፉ ነገር ፈፅሞ ማይወጣውትእግስት፣ ቻይነት ታታሪነት ዋጋው የነበረ ወንድማቻት ባልደረባችን በሞት አጣነው።ስንቴ ነፍስህ በሰላም ትረፍ
03/01/2026

አንደበቱ ከፉ ነገር ፈፅሞ ማይወጣው

ትእግስት፣ ቻይነት ታታሪነት ዋጋው የነበረ ወንድማቻት ባልደረባችን በሞት አጣነው።
ስንቴ ነፍስህ በሰላም ትረፍ

ትውልድን በእውቀት ለማነፅ ፣ ፖለቲካን በጥበብ ለመያዝ ፣ልማትን ለማስረፅ ፣ ታሪክን ለትውልድ እንዴት ማውረስ እንደሚገባ የተከተሉት የህይወት ፍልስፍና ይደንቀኛል ። ትምህርት ሊወሰድበት ይገ...
30/12/2025

ትውልድን በእውቀት ለማነፅ ፣ ፖለቲካን በጥበብ ለመያዝ ፣ልማትን ለማስረፅ ፣ ታሪክን ለትውልድ እንዴት ማውረስ እንደሚገባ የተከተሉት የህይወት ፍልስፍና ይደንቀኛል ። ትምህርት ሊወሰድበት ይገባል ።

አዝማች ይርጋ ገብሬ ከእሳቸው ብዙ መማር ትርፍ አለው።
ነፍስ ይማር ለወዳጅ ዘመድ መፅናናትን ያድል !!!

በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው  ወልቂጤ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በህዝብ ተሳትፎ የሚከናወኑ ትልልቅ የልማት...
27/12/2025

በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው


ወልቂጤ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በህዝብ ተሳትፎ የሚከናወኑ ትልልቅ የልማት ሥራዎች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና የብልጽግና ጉዞን የሚያፋጥኑ መሆናቸው ተገለጸ።

በክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር ከቀቤና ልማት ማህበር ጋር በመተባበር ለሚገነቡት "ኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል" እና "ለፈትሁዲኒ ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት" ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ ዛሬ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ለልማት ፕሮጀክቶቹ ግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ1 ቢሊዮን 700 ሺህ ብር በላይ ቃል ተገብቷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ኑርዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተከናወኑ ነው።

እነዚህ የልማት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ የክልሉን የብልጽግና ጉዞ እንደሚያፋጥኑ ተናግረዋል።

ለአብነትም የቀቤና ልዩ ወረዳ ዘመናዊ ሆስፒታል እና አዳሪ ትምህርት ቤት የልማት ፕሮጀክቶች ባለቤትና ዋነኛ ተጠቃሚ ህዝብ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቶቹ ከመንግስት በተጨማሪ በህዝቡ ቀጥተኛ ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እንደሚከናወኑ የተናገሩት መሃመድ (ዶ/ር) የክልሉ መንግስት ፕሮጀክቶቹ ስኬታማ እንዲሆኑ ድጋፉን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የቀቤና ልማት ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ ሙአዝ በድሩ (ዶ/ር)፤ የሚገነባው አዳሪ ትምህርት ቤት ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

ትምህርት ቤቶቹን በቴክኖሎጂ በማደራጀት የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲያፈሩ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የሆስፒታሉ ግንባታም የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውም አመልክተዋል።

በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡ ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነትና የወረዳውን ልማት የሚያጠናክሩ ናቸው ያሉት ደግሞ የቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሃመድአሚን በደዊ ናቸው።

የሆስፒታሉ ፕሮጀክት ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት መደላድል እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

በተለይ የእናቶችና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ እና ለሕክምና ወደ ሌሎች ከተሞች ይደረግ የነበረን ጉዞ ይቀንሳል ብለዋል።

በዛሬው እለትም ለፕሮጀክቶቹ ማስፈጸሚያ የሚሆን ከ1 ቢሊዮን 700 ሺህ ብር በላይ ብር ቃል መገባቱን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥም ወደ ግንባታ እንደሚገባ አመልክተዋል።

በህብረተሰቡ ተሳትፎ ለሚገነቡ የሕክምና እና የትምህርት ፕሮጀክቶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ለይላ ነጋሽ የተባሉ የልዩ ወረዳው ነዋሪ ናቸው።

ለእነዚህ ልማቶች ከግብርና ሥራቸው በሚያገኙት ገቢ ብር 500 ሺህ ለመለገስ ቃል መግባታቸውን ገልፀዋል ።

አቶ መሃመድ ሀሰን የተባሉ ነዋሪም ለአዳሪ ተምህርት ቤቱና እና ለሆስፒታሉ ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

በገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና የአካባቢው ተወላጆች ተገኝተዋል።

27/12/2025
የት ሃገር የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው ? ህንፃ ቤተክርትያኑ ምን ይባላል ?
25/12/2025

የት ሃገር የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው ? ህንፃ ቤተክርትያኑ ምን ይባላል ?

ቃላችን ለምን ታጠፈ ? ቀጠሮአችን እንዴት ተዘነጋ ?ዩኒቨርስቲያችን ኑ ትዝታችሁን አጣጥሙ ቤታችሁ ጠይቁ ሲል። 75  አመታት የልገሳ ቆይታው በማስመልከት ። አልማዝ እዩቤልዩ። ከትምህርት በላ...
25/12/2025

ቃላችን ለምን ታጠፈ ? ቀጠሮአችን እንዴት ተዘነጋ ?

ዩኒቨርስቲያችን ኑ ትዝታችሁን አጣጥሙ ቤታችሁ ጠይቁ ሲል። 75 አመታት የልገሳ ቆይታው በማስመልከት ። አልማዝ እዩቤልዩ።
ከትምህርት በላይ ፍቅር የተጋመድንበት ፣ ከእውቀት በላይ አብሮነትን የሸመትንበት ፣ኢትዮጵያዊነትን ያፀናንበት ቤታችን አንጋፋው የጋራ ጎጆችን ጠርቶናል ።
አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚዘወርበት ።ዓለም በአጉሊ መነፅር ምታይበትአንጋፋ ተቋም ነው።
ታድያ የኛ የማይረሴው ቡድን ቀጠሮ ነበረን።
በምረቃችን 2002 ዓ.ም ሃገርህን እወቅ ጉዞ አሰናድተን ጥያ አለም አቀፍ ቅርስ ጉብኝተን ችግኝ ተክለን ።በ10 አመት ዳግም ልንገናኝ ቀጠሮ ይዘን ነበር። ዘንግተን ተሰብሳቢ አጥተን ወይስ ሁኔታዎች ገድቦን
ያ ቀጠሮ ምታስታውሱ ሀያል ግሩፕ አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ከታህሳስ 21 እስከ 24/2018 ዓ.ም ለመገናኘት ብንሞክር ምን ይመስላችኋል ? ሃሳብ ስጡበት።
ኮሜርስ፣ fbe ፣ዋናው ግቢ ፣4 ኪሎ ፣ 5 ኪሎ ፋርማሲ : የካቲት 12 :ጥቁር አንበሳ ፣ጳውሎስ
ይድረስ
ሰብሳቢያችን #ሳህሌ አለሙ አደራ ተቀባዩ አስቻለው ምን እየሰራቹህ ይሆን ?
---------

ያለ ፍላጎታቸው በማጠብ ቀጯቸው "የዓለማችን ቆሻሻው ሰው" የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቷቸው የነበሩት ኢራናዊው አሙ ሀጂ በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ከ60 ዓመታት በላይ ገላቸውን ሳ...
24/12/2025

ያለ ፍላጎታቸው በማጠብ ቀጯቸው

"የዓለማችን ቆሻሻው ሰው" የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቷቸው የነበሩት ኢራናዊው አሙ ሀጂ በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ከ60 ዓመታት በላይ ገላቸውን ሳይታጠቡ ኖረዋል።

አሙ ሀጂ በኢራን ገጠራማ አካባቢ እራሳቸውን ከሰው አግልለው ለበርካታ አስርት ዓመታት የኖሩ ሲሆን፣ "ሳሙና እና ውሃ ያሳምሙኛል" በሚል እምነት ገላቸውን ከመታጠብ ተቆጥበው ቆይተዋል።

ከዓመታት ሙከራ በኋላ፣ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች አሙ ሀጂን አሳምነው ለመጀመሪያ ጊዜ ገላቸውን እንዲታጠቡ አድርገዋቸው ነበር። ሆኖም ግን ገላቸውን ታጥበው ብዙም ሳይቆዩ ጤናቸው እየተዛባ በመሄዱ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

የአሙ ሀጂ ህይወት እና አመጋገብ እጅግ ያልተለመደ የነበረ ሲሆን፣ ይህ አኗኗራቸውም በዓለም ዙሪያ የብዙዎችን ትኩረት ስቦ ቆይቷል።

ይህ ቤተክርስቲያን የሚገኘው ? እና ስሙ ደግሞ-----
23/12/2025

ይህ ቤተክርስቲያን የሚገኘው ? እና ስሙ ደግሞ-----

በ6 ወር ይህ ሆነ ይህ ተሰራ ቢባል ማን ያምናል ?እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር  በጥራት በውበት እጅ ከአፍ ሚያስጭን ቤተመንግሥት እና ቢሮ በሆሳዕና ...
21/12/2025

በ6 ወር ይህ ሆነ ይህ ተሰራ ቢባል ማን ያምናል ?

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር በጥራት በውበት እጅ ከአፍ ሚያስጭን ቤተመንግሥት እና ቢሮ በሆሳዕና አሰገንብተዋል። ስልጣን ያልፋል ስራው ለትውልድ ይቆያል።

አንድ ጓደኛዬ በቴክኖሎጂ ነክ ሃገራዊ ተቋም ስለሚሰራ ከዚህ የተነሳ ግቢው ዘልቆ ለስራ መግባቱን ነግሮኛል።

ለማመንም ለመናገርም የሚደንቅ #ቅንጡ ቤተመንግሥት መመልከቱን ነግሮኛል።

21/12/2025

Address

Wolkite
KEY

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Endalk Fm posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share