Ethiopian Report ኢትዮጵያን ሪፖርት

Ethiopian Report ኢትዮጵያን  ሪፖርት this page is opened to broadcast update and currently news on Ethiopia and the whole africa .

31/08/2024

ሌሎች አካላት ቀጠናውን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ቆማ እንደማትመለከት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫው ሌሎች አካላት ቀጠናውን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ቆማ እንደማትመለከት አስታውቋል።

መግለጫው የወጣው በትናንትናው እለት የግብፅ የጦር አውሮፕላኖች ወደ ሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ ቀሳቁስ እና ወታደሮችን ማጓጓዛቸው ይፋ ከሆነ በኋላ ነው።

"ኢትዮጵያ ብሄራዊ ፀጥታዋን ሊያውኩ የሚችሉ በቀጠናው እየተከናወኑ ያሉ ድርጊቶችን በንቃት እየተከታተለች ነው" ያለው መግለጫው የሶማልያ መንግስት ከውጭያዊ ሀይሎች ጋር በማበር ቀጠናው ላይ ውጥረት እየፈጠረ ነው ብሎ ከሷል።

መግለጫው አክሎም "ለአጭር ግዜ እና እርባና ቢስ ጥቅም ብለው አካባቢው ላይ ውጥረት የሚነዙ ሀይሎች ለድርጊታቸው ተጠያቂ ይሆናሉ" ብሏል።

ይሁንና መግለጫው በትናንትናው እለት አውሮፕላኖችን ወደ ሶማልያ ያሰማራችውን ግብፅን በስም አልጠቀሰም።

የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት ይህን የግብፅ እና ሌሎች ሀገራት ስምሪት ያፀደቀው ሲሆን እ.አ.አ ከጃንዋሪ 1/2025 ጀምሮ በሶማልያ በመሰማራት ሲቪል ዜጎችን ከአልሻባብ ሀይሎች ጥቃት የመከላከል ስራ ተሰጥቶታል።

ሂደቱ ገፍቶ ግብፅ ጦሯን በሶማልያ ካሰፈረች ሀገሪቱ ከደቡብ ሱዳን በመቀጠል በኢትዮጵያ ጎረቤቶች ያላት ሁለተኛ መገኘት ይሆና
via

31/08/2024

ተመልሰናል

የትህነግ ምሽጎች በዝቋላ ወረዳ አሸባሪው ትህነግ በዋግኸምራ ዞን በዝቋላ ወረዳ ቅዳሚት ቀበሌ ይህን የመሰለ ምሽግ ሰርቶ ነበር። ሆኖም ጥሎት ፈርጥጧል።  ምስል፦ ከዋግኸምራ ኮሙኒኬሽን ገፅ
13/09/2022

የትህነግ ምሽጎች በዝቋላ ወረዳ

አሸባሪው ትህነግ በዋግኸምራ ዞን በዝቋላ ወረዳ ቅዳሚት ቀበሌ ይህን የመሰለ ምሽግ ሰርቶ ነበር። ሆኖም ጥሎት ፈርጥጧል።

ምስል፦ ከዋግኸምራ ኮሙኒኬሽን ገፅ

ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶኬንያ በወርሃ ነሐሴ መጀመርያ ባካሄደችውና በ1963 ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣች ወዲህ ለአምስተኛ ጊዜ በተካሄደው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የነበሩትን ራይላ ኦዲንጋን በማሸነ...
13/09/2022

ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ

ኬንያ በወርሃ ነሐሴ መጀመርያ ባካሄደችውና በ1963 ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣች ወዲህ ለአምስተኛ ጊዜ በተካሄደው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የነበሩትን ራይላ ኦዲንጋን በማሸነፍ ዊሊያም ሩቶ ፕሬዝዳንትነት መሆን የቻሉ ሲሆን፤
ለአስር ዓመት ኬንያን ሲያስተዳድሩ የቆዩት ኡሁሩ ኬንያታ የፕሬዝዳነትነት ዘመናቸውን አጠናቅቀው ፕሬዝዳነትነትን አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የሚረከቡት የትግራይ ኃይሎች በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የሚደረገውን ድርድር በተቀበሉ ከሁለት ቀናት በኋላ መሆኑ ነው።

ዊሊያም ሩቶ በበዓለ ሲመታቸው ላይ ከ40 በላይ የሃገራት መንግሥታት እና የመንግሥታት ተጠሪዎችን መጋበዛቸዉ የተዘገበ ሲሆን፤ በሥነ-ስርዓቱ ከተጋበዙት መካከል፤ የኢትዮጵያ፤ ግብጽ፤ ዩጋንዳ፤ ናይጀሪያ፤ ጋና እና፤ የደቡብ አፍሪካ መሪዎች ይገኙበታል።

ኬንያ በ1963 ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣች ጀምሮ ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው ጠንካራ የፀጥታ እና የምጣኔ ሃብት ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸው የጀመረችውም በ1945 እኤአ መሆኑ ይገለፃል። በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደሌ፣ ሁለቱ አገራት ጣልያን ኢትዮጵያን ከወረረችበት ጊዜ ጀምሮ ጠንካራ ግንኙነት ፈጥረው መቀጠላቸውን ያወሱት በቅርቡ ነው። “ከኬንያ ጋር ልዩ የሆነ ግንኙነት አለን። ይህንን ግንኙነት የጀመሩት አባቶቻችን ናቸው። የሁለቱ አገራት ግንኙነት ልዩ ነው።” ብለዋል አምባሳደር ባጫ።

የመጀመሪያው የኬንያ ፕሬዚዳንት፣ ጆሞ ኬኒያታ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት የነበራቸው ናቸው። እንደ አገር መሪ ብቻ ሳይሆን፣ እንደጥብቅ ጓደኛ ጭምር ያወሩና ይመክሩ ነበርም ይባልላቸዋል። በኬንያ መዲና ናይሮቢ ሦስት ታላላቅ አውራ ጎዳናዎች አንዱ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ስም የተሰየመ ሲሆን በቅርቡም የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሚገኝበት ከተሰየመው ጎዳና በተጨማሪ አዲስ የፍጥነት መንገድ ስታስመርቅ በስማቸው እንዲሆን ወስናለች።

ግንቦት 14 1955 ዓ/ም 34 የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ አንድነት (የአሁኑ አፍሪካ ሕብረት) ድርጅትን ለመመስረት በአዲስ አበባ ላይ ስብሰባ ሲጀምሩ በአስተሳሰብ የተለያየ ፅንፍ ላይ የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችን ከእርስበርስ ልዩነታቸው ወጥተው ሁሉም በወንድማማችነት መንፈስ እንደ አንድ ቤተሰብ እንዲያስቡ፤ ለሦስት ቀናት ከመከሩ በኋላ ግንቦት 17 1955 ዓ/ም የአፍሪካ አንድነትን እውን አድርገዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ከቀዳማዊ ኃይለስላሴ ጋር ለምስረታው እውን መሆን የጋናው ክዋሜ ንኩርማን ጨምሮ የኬኒያው ጆሞ ኬኒያታ ከፍተኛውን አስተዋፅኦ አድርገዋል።

የትግራዩን ጦርነት ተከትሎ ምዕራባዊያን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና በሚያራምዱት ወቅታዊ አካሄድ የተነሳ ተሰናባቹ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬኒያታ ከኢትዮጵያ የሚፃረር አቋም እንዲያራምዱ ብዙ ጫና ሲደረግባቸው እንደነበር ይገለፃል።
ከኬኒያ ምርጫ ሂደት ውስጥ ተሸናፊው ራይላ ኦዲንጋ በቅስቀሳቸው ወቅት የቀጣናውን ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአሉታዊ ምሳሌ ሲጠቅሱ መደመጣቸው የሚታወስ ሲሆን ተሰናባቹ ኡሁሩ ኬኒያታ ከቀናት በፊት ሲናገሩ "ስልጣናቸውን ለተመራጩ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በደስታ እንደሚስረክቡ ይሁን እንጂ ኬንያ በራይላ ኦዲንጋ ብትመራ የተሻለ ይሆን ነበር ሲሉ ተደምጠዋል።

አሸናፊው ሩቶ ከቀደመው 2007ቱ የኬንያ ምርጫ ጋር በተያያዘ ከምዕራባዊያን ሀገራት የተለያዩ ጫናዎች በተለይም በአለማቀፉ ፍርድ ቤት ክስ ተመስርባቸው እጅ ሳይሰጡ ተቋቁመው በአሸናፊነት የዘለቁ ፖለቲከኛ ናቸው።

በእለተ ማክሰኞ የመሪነት መንበሩን የሚረከቡት ዊሊያም ሩቶ የኬኒያ ፕሬዝደንት ሆነው መመረጣለውን ተከትሎ ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ለሚኖራት ትብብር መልካም አጋጣሚ ነው የሚሉት በርካቶች ናቸው።
#የዓባይልጅ

Esleman abay

13/09/2022

በዛሬው እለት ጁንታው ላይ የተፈፀሙ ስኬታማና ኢላማቸውን የመቱ የአየር ጥቃቶች

1. በመቀሌ ከተማ የሚገኘው የድምፀ ወያኔ ስቱዲዮ እና ማሰራጫ፣
2:- ደደቢት አንድ T-52 ትንሽክ ፣
3:- ወርቄ ውላይ የተሰባሰበ በርካታ ታጣቂ ከነ አመራሩ ላይ፣
4:- ተኩለሽ ሸወይ ማርያም ላይ ስብሰባ ላይ በነበሩ የጁንታው ታጣቂዎች ላይ፣
5:- በደደቢት አካባቢ በተመሳሳይ ስብሰባ ላይ በነበሩ ታጣቂዎች ላይ፣
6. በቲሃ እየተካሄደ ባለው ጦርነት የጁንታው ኃይል ከቅማንት ታጣቂ ጋር በመሆን በከፈተው ውጊያ ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ሸሽቷል። በዚህም በርካታ የጁታው እና የቅማንት ታጣቂ እንዲሁም ቡድኑ ይጠቀምበት የነበረው ሬዲዮ ተማርኳል።
7. በአፋር ግንባር አብአላ አመራር ያለበት የታጣቂ ስብስብ ላይም እርምጃ ተወስዷል

13/09/2022

ውድ ኢትዮጵያዊያን እንኳን ለ2015 ዓ.ም አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ እያልን አዲሱ አመት የሰላም የፍቅር የብልፅግና ይሁንልን።

Adresse

Adiss Street
Adissan

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Ethiopian Report ኢትዮጵያን ሪፖርት publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Partager