Central Ethiopia News

Central Ethiopia News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia News, Media/News Company, centralethiaffirsa . com, London.

የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተልማት ማህበሩ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ከተመሰረተ በኋላ አዲስ አበባና ሀደሮ ከተማ ቅርንጫፎች በመክፈት ስራዎች እ...
08/06/2025

የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተ

ልማት ማህበሩ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ከተመሰረተ በኋላ አዲስ አበባና ሀደሮ ከተማ ቅርንጫፎች በመክፈት ስራዎች እየሰራ ነው።

ከኢፌድሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ወስዶ ስራውን የጀመረው የጠምባሮ ልማት ማህበር የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለመስራት ዓላማ ይዞ በአዋጅ የተቋቋመ ነው።

ማህበሩ በትምርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርናና አካባቢ ጥበቃ አንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴ ጀምሯል።

ዛሬ ላይም በሀዋሳና አካባቢው ከሚኖሩ የብሄረሰቡ ተወላጆች ጋር በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።

#ደሬቴድ

ጠቅላይ ምንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ እና ቀደመዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በስምብጣ ቀበሌ የአቦካዶ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አስቀመጡ
03/06/2025

ጠቅላይ ምንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ እና ቀደመዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በስምብጣ ቀበሌ የአቦካዶ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አስቀመጡ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክትየገጠር ኮሪደር ልማት ሀገርን የመለወጥ ሰፊ ራዕይ የተሰነቀበት ሀገራዊ ውጥን ነው።  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከንባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወ...
02/06/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የገጠር ኮሪደር ልማት ሀገርን የመለወጥ ሰፊ ራዕይ የተሰነቀበት ሀገራዊ ውጥን ነው።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከንባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሀሚዶ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማትን አስጀምረናል።

በተጨማሪም በቀበሌው የሚኖረው አንድ የአርሶ አደር ሞዴል የገጠር መንደርን የጎበኘን ሲሆን፣ አርሶ አደሩ ጽዱ፣ ጤናማና ለማየት እጅግ ማራኪ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን በመኖሪያ ግቢው ውስጥ በመፍጠር ምሳሌ የሚሆን ስራ አከናውኗል። ጽዱ የመኖሪያ ስፍራን ከመፍጠር ባለፈ በሌማት ትሩፋትና ጓሮ አትክልት ልማት ላይም ንቁ ተሳተፎ እያድረገ ይገኛል። ይህ ስራ በሁሉም አካባቢ በትብብር ሊሰፋ ይገባል።

እንዲሁም በዞኑ ልዩ የተፈጥሮ ገጸ በረከት የሆነው ሀምበርቾ ተራራን በማህበረሰብ ተሳትፎ የኢኮ ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተከናወኑ ስራዎችም እጅግ የሚደነቁ ናቸው።

በተራራው የተገነባው 777 የመወጣጫ ደረጃ አካባቢውን ተደራሽ የመስህብ ስፍራ ያደርገው ሲሆን፣ ተራራ መውጣትና የተለያዩ የአእዋፋት ዝርያዎችን መመልከት የሚወዱ ቱሪስቶች ወደ እዚህ ስፍራ በመምጣት ማራኪ ጊዜን ማሳለፍ ይችላሉ።

# ኤፍ ኤም ሲ

የገጠሩን ማሕበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የገጠር ኮሪደር በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገጠሩን ማሕ...
02/06/2025

የገጠሩን ማሕበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የገጠር ኮሪደር በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገጠሩን ማሕበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ዛሬ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ሲንቢጣ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆኑ ሞዴል የገጠር መንደሮች ግንባታን አስጀምረናል ብለዋል።

ሞዴል የገጠር መንደሮቹ ቀላል ወጪ የሚጠይቁ እና በአካባቢው በሚገኙ ግብዓቶች የሚገነቡ ሲሆኑ÷ አርሶ አደሩም ጤናማ እና ክብር ያለው ሕይወት እንዲኖር እንደሚስችሉ ተናግረዋል፡፡

በአካባቢው ከ2 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በመስኖ የበቆሎ ምርጥ ዘር ብዜት እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እየተካሄደ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል፡፡

ይህም ከዚህ ቀደም በጎርፍና ድርቅ አደጋ ይታወቅ የነበረውን አካባቢ የልማት ተምሳሌት ያደርገዋል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)።

24/05/2025
22/05/2025

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰርቅ ሰውቢሰቀል ደስ ይለኛል

የጉራጌ ህብረተሰብ አንድነትና የልማት ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ተናገሩ።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በጉልባማ አመታዊ...
11/05/2025

የጉራጌ ህብረተሰብ አንድነትና የልማት ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ተናገሩ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በጉልባማ አመታዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የገጠር እና የከተማው ህዝብ አስተሳስሮ በተገቢው መምራት ያስፈልጋ ብለዋል።

የሁለቱ የጉራጌ ዞን አስተዳደሮች አንድነት ለማስቀጠል ይበልጥ ተግቶ መስራት ያስፈልጋል።

የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌሎች ጎረቤቶቹና ከመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ ፍሬያማ ማድረግ እንደሚገባ በዚህ ረገድ ያለው አኩሪ የሆነው የአብሮነት ባህሉ ማስቀጠል ይገባል።

የልማት ማህበሩን የልማት አቅም የሚያጠናክሩ አሰራሮች እና የአሰራር ማዕቀፎች በማዳበር ይበልጥ ጠንክሮ እና ጎልቶ እንዲወጣ ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።

የህዝባችን የስራ ባህል ዕሴቶቹ ይበልጥ በማልማትና በማጠናከር ከሁሉም ህዝቦች ጋር በጋራ የሚሰራበት ባህል ይበልጥ ማጉልበት ያስፈልጋል ሲሉ ዶ/ር እንዳሻው ተናግረዋል።

የጉራጌ ባህልና ልማት ማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሺሰማ ገ/ስላሴ እንደገለፁት; የጉራጌ ህዝብ እውቀቱ፣ ጉልበቱና ሀብቱ ከመንግሥት ውስን የልማት በጀት ጋር በማቀናጀት የአካባቢው የልማት ስራዎች በመተግበር የካበተ ልምድ ያለው ሲሆን ትውልዱ በየአካባቢው ህብረተሰቡ፣ ባለሃብቱና ሌሎች አጋር ድርጅቶችና አደረጃጀቶችን በማስተባበር የተለያዩ የልማት ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎የህብረተሰቡን የልማት ችግሮች በተደራጀ መንገድ ለመፍታት በየአካባቢው የነበሩ አደረጃጀቶች በመቀናጀት ጉልባን መስርተዋል።

‎ማህበሩ ከተመሰረተ ጀምሮ አላማው መሰረት ያደረጉ በርካታ የልማት ስራዎች ማከናወኑን የተናገሩት አቶ ሺሰማ አባላቱ፣ ደጋፊዎቹና አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ላይ የልማት አሻራው ማኖሩን ገልፀዋል።

‎ከህዝቡ የልማት ፍላጎት አኳያ ማህበሩ ብዙ ተግባራት እንደሚጠበቅበት የተናገሩት ሰብሳቢው በገጠሙት ፈተናዎች ሳይበገር ዛሬም ባልተቋረጠ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ ይገኛል ብለዋል።

‎የማህበሩ መስራቾች በቴሌቶን ባሰባሰቡት ሀብት 80 በመቶ ለወረዳዎች የተሰጠ ሲሆን በቀሪዉ 20 በመቶ 5 ፕሮጀክቶች ማለተም የቡታጅራ ዋና ጽ/ቤት፣ የአዲስ አበባ የባህል ማዕከል፣ የወልቂጤ ሆስፒታል፣ አረንጓዴ ኢኒሼቲቭ እና የልማት ስራዎች ሲሆኑ የፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

‎ ለወልቂጤ ሆስፒታል ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ግንባታው ከተጀመረ ወዲህ ቦርዱ ለወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ያስረከበ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታው በማጠናቀቅ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተናግረዋል።

‎በቡታጅራ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የማህበሩ ጽ/ቤት እስከ አንደኛ ወለል ያለውን ግንባታ በማጠናቀቅ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን በአዲስ አበባ የሚገኘው የባህል ማዕከል ግንባታ አፈፃፀም በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ ቢሆንም የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሙሉበሙሉ አለመጠናቀቃቸው እንደሚያስገኝ ገልፀዋል።

‎የማህበሩ አቅም እየተጠናከረ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ተቀናጅቶ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።


በታደለ ገመቹ

ዜና ሹመት የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት አቶ በረከት ከድር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ፅ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በመሆን ተሹመዋል ። መልካም...
10/05/2025

ዜና ሹመት
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት አቶ በረከት ከድር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ፅ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በመሆን ተሹመዋል ። መልካም የስራ ጊዜ
መረጃው የስ/መ/ኮ ነው

 ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር) የዶክትሬት (Phd) ትምህርታቸውን ማጠናቀቅ በማስመልከት መላዉ የኮሚ...
08/05/2025



ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር)

የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ (ዶ/ር) የዶክትሬት (Phd) ትምህርታቸውን ማጠናቀቅ በማስመልከት መላዉ የኮሚሽኑ አመራሮች እና ፈፃሚዎች የእንኳን ደስ ያልዎ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

07/05/2025

Address

Centralethiaffirsa @gmail. Com
London
HALABAALEKOUNITED

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share