Central Ethiopia News

Central Ethiopia News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia News, Media/News Company, centralethiaffirsa . com, London.

የኢትዮጵያ 20 ታሪካዊ ከተሞችና አሰያየማቸው📍 1. አዲስ አበባ — እቴጌ ጣይቱ ፍልውሃ አካባቢ ሰፍረው ሳለ ያዩትን አዲስ አበባ መሠረት በማድረግ ያወጡት ስም ነው። (ምንጭ፡ የታሪክ ሰነዶች...
14/07/2026

የኢትዮጵያ 20 ታሪካዊ ከተሞችና አሰያየማቸው

📍 1. አዲስ አበባ — እቴጌ ጣይቱ ፍልውሃ አካባቢ ሰፍረው ሳለ ያዩትን አዲስ አበባ መሠረት በማድረግ ያወጡት ስም ነው። (ምንጭ፡ የታሪክ ሰነዶች)

📍 2. አዳማ — በኦሮሚኛ "አዳሚ" (ቁልቋል) ከሚለው ቃል ወይም "አዳማ ቡታ" ከተባለ የነገዱ አባት ስም የመጣ ነው። (ምንጭ፡ የኦሮሚያ ባህል ቢሮ)

📍 3. መቀሌ — "መቐለ" (ተካፈለ/ተከፋፈለ) ከሚለው የትግርኛ ቃል የመጣ ሲሆን፣ በጥንቱ ዘመን የአሞሌ ጨውና የንግድ ዕቃዎች ማከፋፈያ የነበረ ቦታ ነው። (ምንጭ፡ የታሪክ መዛግብት)

📍 4. ሐዋሳ — በሲዳምኛ "ሐዋሳ" ማለት "ሰፊ የውሃ አካል" ወይም "ሐዋሾ" (ሐይቅ) ማለት ነው። (ምንጭ፡ የሲዳማ ባህል ጥናት)

📍 5. ድሬዳዋ — በኦሮሚኛ "Dirree Dhawaa" ማለት "የመድኃኒት ሜዳ" ማለት ሲሆን፣ በሱማሊኛ "Diridhaba" (የዲር ጎሳ ጦሩን የተከለበት) ማለት ነው። (ምንጭ፡ የከተማው የታሪክ ማህደር)

📍 6. ባሕር ዳር — ከተማዋ በጣና ሐይቅ እና በአባይ ወንዝ መነሻ (ባሕር) ዳርቻ ላይ በመቆርቆሯ የተሰጣት ስም ነው።

📍 7. ደሴ — አፄ ዮሐንስ 4ኛ በ1874 ዓ.ም አካባቢውን ሲመለከቱና በሰማይ ላይ ድንቅ ኮከብ ሲያዩ የተሰማቸውን ደስታ ለመግለጽ "ደሴ" (የእኔ ደስታ) አሏት። (ምንጭ፡ የታሪክ መጻሕፍት)

📍 8. ጅማ — "ጅማ" ከሚባለው ታዋቂ የኦሮሞ ነገድ ስም (ጅማ አባ ጂፋር) የመጣ ነው።

📍 9. ሻሸመኔ — "ሻሼ" ከምትባል ጥንታዊት ባለሀብት ሴት እና "መኔ" (ቤት) ከሚለው የኦሮሚኛ ቃል የመጣ ሲሆን "የሻሼ ቤት/ማደሪያ" ማለት ነው።

📍 10. ቢሾፍቱ — በኦሮሚኛ "Bishaanooftuu" (ውሃማ/የበዛ ውሃ ያለበት ቦታ) ማለት ሲሆን፣ ስሙ የተሰጠው በአካባቢው ካሉት በርካታ የክሬተር ሐይቆች የተነሳ ነው። (ምንጭ፡ ስነ-ልሳን ጥናት)

📍 11. ጎንደር — የስሙ መነሻ እስካሁን በሊቃውንት ዘንድ ክርክር ያለበት ሲሆን፣ "ጎንደር" ከተባለ ዛፍ ወይም "የሀገር መሠረት" ከሚል የግዕዝ ስርወ-ቃል እንደመጣ ይገመታል።

📍 12. ሶዶ (ወላይታ ሶዶ) — በኦሮሚኛ "ሶዶ" ማለት "አማች/ዝምድና" ማለት ሲሆን፣ በጥንት ዘመን ልዩ ልዩ ጎሳዎች ለሰላም ስምምነትና ለዝምድና የሚገናኙበት ቦታ ነበር።

📍 13. አርባ ምንጭ — ከተማዋ አጠገብ ከሚገኙት 40 ትናንሽና ትላልቅ የተፈጥሮ የምንጭ ውሃዎች መነሻነት የተሰጣት ስም ነው።

14. ሐረር — "ሀረር" የሚለው ስም "ሀረሪ" ከሚለው የነገዱ ስም የመጣ ሲሆን፣ በጥንታዊ ትርጉሙ "የመገናኛ/የስብሰባ ቦታ" ማለት ነው።

15. ነቀምቴ — "ነቀምቴ" የሚለው ስም በአካባቢው ከነበረው "ነቀምት" ከተባለ የኦሮሞ ጎሳ ስም የመጣ ነው።

16. አሰላ — በኦሮሚኛ "አሰላ" ማለት "ምቹ/መልካም መሬት" ወይም "ለኑሮ የሚስማማ ሰፊ ቦታ" ማለት ነው።
17. ደብረ ማርቆስ — በጥንቱ ስሟ "መንቆረር" ትባል የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በንጉሥ ተክለሃይማኖት ዘመን በቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ስም ተሰየመች።

18. ሆሳዕና — መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "አሁን አድን" ማለት ነው። ከተማዋ ቀደም ሲል "ዋቸሞ" (በሀዲያኛ ሰፊ/ሀብታም) ትባል ነበር።

19. አክሱም — "አኩ" (በጥንታዊ ሳባዊ/አገው ቋንቋ ውሃ) እና "ሹም" (አለቃ/ገዢ) ከሚሉ ቃላት የመጣ ሲሆን "የውሃ አለቃ" ወይም "የውሃ ማጠራቀሚያ" ማለት ነው። (ምንጭ፡ የፊደልና ስርወ-ቃል ጥናት)

20. ጅጅጋ — በሱማሊኛ "ጅጅጋ" ማለት "ቀጥ ያለ/ምቹ ሜዳ" ወይም ፈረሶች የሚጋለቡበት ሜዳማ ቦታ ማለት ነው።
ምንጭ፡ የሱማሌ

 #በ70 ዓመታቸው በኢኮኖሚክስ ት/ት የመጀመሪያ ዲግሪ ያጠናቀቁ ጀግና እናት🏆
12/07/2026

#በ70 ዓመታቸው በኢኮኖሚክስ ት/ት የመጀመሪያ ዲግሪ ያጠናቀቁ ጀግና እናት🏆

10/07/2026
01/07/2026
16/06/2026

"በጋራ ለመበልፀግ የሚያስፈልገው መተባበር ብቻ ነው፣ ከደባል አጀንዳ በመውጣት ለጋራ እድገት መስራት ይገባል"

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በቁጥር ************ የመራጮች ቁጥር - 54, 057, 861 የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች - 42እጩ ተወዳዳሪዎች - 10 ሺህ 438የግል ዕጩዎች - 80 ...
30/05/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በቁጥር
************

የመራጮች ቁጥር - 54, 057, 861

የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች - 42

እጩ ተወዳዳሪዎች - 10 ሺህ 438

የግል ዕጩዎች - 80

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ታዛቢዎች - 55

የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች - 59

የኢጋድ ታዛቢዎች - 26

የሚዲያ ተቋማት - 68

56ቱ የሀገር ውስጥ 12ቱ የውጭ ሀገር ሚዲያዎች

#በምርጫብቻ

የዴሞክራሲ ማዕዘን፦ የምርጫ ካርድ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታየ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጫ ቀን ለመድረስ የቀሩት 3 ቀናት ብቻ ናቸው። ይህች አጭር ጊዜ ለሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ...
29/05/2026

የዴሞክራሲ ማዕዘን፦ የምርጫ ካርድ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጫ ቀን ለመድረስ የቀሩት 3 ቀናት ብቻ ናቸው። ይህች አጭር ጊዜ ለሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሚከፈትበት ታላቅ ዋዜማ ናት።

"ሲታጠቁ አንገትን፣ ሲፈርዱ ልብን" እንደሚባለው፣ ዛሬ በጦር መሣሪያ ሳይሆን በነፃና ፍትሃዊ የምርጫ ካርድ የሀገርን ዕጣ ፈንታ ለመወሰን የልብ ውሳኔ የምናደርግበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ምርጫ እንዲሁ በየሥርዓቱ የሚደገም ተራ የፖለቲካ ክንውን ሳይሆን፣ የሕዝብን እውነተኛ ውክልና የሚያረጋግጥበትና የሀገረ መንግስት ግንባታን በፅኑ መሠረት ላይ የሚጥል ታላቅ መሣሪያ ነው።

"ቤት በምሰሶ፣ ሀገር በሕዝብ" እንደሚባለው ሁሉ፣ ማንኛውም ፅኑ እና ዘላቂ መንግስት ሊገነባ የሚችለው በሕዝብ ነፃ ፈቃድና ማህበራዊ ውል ላይ ሲመሠረት ነው።

ዜጎች ድምፃቸውን በነፃነት ሲሰጡ፣ መንግስት ደግሞ ያንን አደራ ተቀብሎ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስና ሕግን ለማክበር ቃል ይገባል። ይህ እምነትና መከባበር ሲጎለብት የሀገር ሉዓላዊነትና አንድነት ከመቼውም ጊዜ በላይ ይጸናል።

የሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ በብዙ ውጣ ውረዶችና በኃይል የመንግስት ሥልጣን የመያዝ አባዜ ያለፈበት መሆኑ አይዘነጋም። ይሁን እንጂ ከምርጫ ውጭ የሚገኝ ሥልጣን ዘላቂ ሰላምንና ልማትን ሊያመጣ እንደማይችል ታሪክ ደግሞ ደጋግሞ አስተምሮናል።

በተቃራኒው በምርጫ ካርድ የሚገኝ ሰላማዊ ስልጣን የመንግስትን ተቋማዊ ጥንካሬ ያጎለምሳል። ተቋማት በግለሰቦች ፍላጎት ሳይሆን በሕግ የበላይነትና በሕዝብ አመኔታ ላይ ሲገነቡ፣ ሀገረ መንግስቱ ማንኛውንም ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮችን የመቋቋም አቅሙ የላቀ ይሆናል።

የምርጫ ካርድ የጥይት ድምፅን በሰላማዊ የሃሳብ ድምፅ የሚተካ፣ የሀገርን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን የዜጎች ዋነኛ የሥልጣን መሣሪያና የሰለጠነ ማህበረሰብ መገለጫ ነው።

ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የአንድ ወገን ሥራ አይደለም፤ "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ የሁሉንም ዜጋ ንቁ ተሳትፎ ይፈልጋል። መጪው ትውልድ የሚኮራባት፣ ሰላሟ የተጠበቀና ያደገች ሀገርን እንዲረከብ ዛሬ የምናደርገው ተሳትፎ ወሳኝ ድርሻ አለው።

ለትውልድ የተሻለች ሀገር የማቆየት ታሪካዊ አደራ ያለብን እኛ ዜጎች ነን። ይህንን ድርሻችንን የምንወጣው ደግሞ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድና የዜግነት ኃላፊነታችንን በንቃት በመወጣት ነው። መጪው ምርጫ የሀገራችንን የወደፊት አቅጣጫ የሚቀይስ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ ዜጋ ሂደቱ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይገባል።

ቀሪ ቀናትን በንቃትና በኃላፊነት ስሜት በመጠባበቅ፣ የዴሞክራሲ ባህላችንን የምናሳድግበትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የምንረባረብበት ወቅት ሊሆን ይገባል።

"ዛሬ የዘሩት ነገ ይበቅላል" እንደሚባለው፣ በምርጫ ካርዳችን የምንሰጠው እያንዳንዱ ድምፅ ለነገዋ የተሻለች ሀገር የምናስቀምጠው ጠንካራ የማዕዘን ድንጋይ ነው።

ኢቢሲ

ማንም ከተጠያቂነት አያመልጥም።
18/04/2026

ማንም ከተጠያቂነት አያመልጥም።

08/04/2026

ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) የዘንድሮዉን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ480 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረጉ

ሆሳዕና፣ መጋቢት 30፣2018፡-የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር) የዘንድሮዉን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ480 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳደር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ480 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል ።

በዚህም መሠረት በመደበኛ ፍርድ ቤት በወንጀል ጉዳይ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት በመታረም ላይ ከነበሩ ታራሚዎች መካከል የይቅርታ አዋጁና ደንቡ የሚጠይቀውን መመዘኛ አሟልተው ለተገኙ፣ በመደበኛ ወንድ 455፣ሴት ደግሞ 14 በድምሩ ለ469፣እና በልዩ ሁኔታ ወንድ 11 በአጠቃላይ ለ480 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ የተደረገላቸው መሆኑን ርዕሰ-መስተዳደሩ ገልፀዋል፡፡

ይቅርታ ከተደረገላቸው 480 ታራሚዎች መካከል 474ቱ በሙሉ ይቅርታ ከእስር እንዲፈቱ የተወሰነ ሲሆን፣ 6ቱ ከእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ቅናሽ በማድረግ በይቅርታ የተፈቱ ስለመሆናቸውም ጠቁመዋል፡፡

ይቅርታ የተገረገላቸው የህግ-ታራሚዎች በማረሚያ ቆይታቸው መልካም ስነ-ምግባር ያሳዩ፣ በፈፀሙት የወንጀል ድርጊት የተፀፀቱና አንዳንዶቹም ከተጎጂዎች እርቅ የፈፀሙ፣ ካሳና መቀጮ የከፈሉ ስለመሆናቸው በየደረጃው ተረጋግጦ ስለቀረበ ህብረተሰቡ ይህን በመገንዘብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጠይቀዋል ።

ይቅርታ ተጠቃሚዎችም ከሚኖሩበት ማህበረሰብ ሲቀላቀሉ ፣በመልካም ስነምግባራቸው አርዓያ በመሆን ህብረተሰቡን እንዲክሱ ክቡር ርዕሰ-መስተዳደሩ አሳስበዋል፡፡

Address

Centralethiaffirsa @gmail. Com
London
HALABAALEKOUNITED

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share