Mekelle Central Amharic

Mekelle Central Amharic መረጃ መስጠት፣ ማሳተፍ፣ ማብቃት
(1)

ዜና: የአውሮፓ ህብረት እና አጋሮቹ በሰሜን  #ኢትዮጵያ አዲስ ግጭት እንዳይቀስቀስ አስጠነቀቁበኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የሚገኙ የአውሮፓ ህብረት ልዑካን፣ የአባል ሀገራት ኢምባሲዎች እንዲ...
26/08/2026

ዜና: የአውሮፓ ህብረት እና አጋሮቹ በሰሜን #ኢትዮጵያ አዲስ ግጭት እንዳይቀስቀስ አስጠነቀቁ

በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የሚገኙ የአውሮፓ ህብረት ልዑካን፣ የአባል ሀገራት ኢምባሲዎች እንዲሁም የካናዳ፣ #ኖርዌይ እና #እንግሊዝ ኤምባሲዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በአንክሮ እየተከታተሉት መሆኑን አስታውቀዋል። አምባሳደሮች እና የልዑካን ቡድኖች ሁሉም ወገኖች የፕሪቶርያ የዘላቂ ተኩስ ማቆም ስምምነቱን በቅንነት እና በግልጽነት እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በአዲስ አበባ እና በመቐለ ያደረጉትን ውይይት ያደነቀው የመግለጫው አካል፣ በድርቅ እና ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ በተጎዳው የትግራይ ክልል እንደገና ወታደራዊ ግጭት ቢቀስቀስ በህዝቡ ላይ የከፋ ውድመት እንደሚያስከትል አሳስቧል።

በተመሳሳይ #አሜሪካ በበኩሏ የኦባሳንጆን ጉብኝት የደገፈች ሲሆን፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንደገና ግጭት ሊቀስቀስ ይችላል የሚለው ስጋት እየጨመረ መምጣቱን ገልጻለች። የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ እና የአፍሪካ ህብረት የአሜሪካ ሚሲዮን ጉዳይ ፈጻሚ ዋልተር ፖርክስ ፣ #ኦባሳንጆ የአፍሪካ ህብረት መመሪያቸውን ለመወጣት የሚያደርጉት ጥረት ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ በቅርቡ ወደ #ትግራይ እንደሚመለሱ ተስፋ አድርገዋል። የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲ ተወካዮች መሪዎች ሚሊዮኖችን እየጎዳ ያለውን ድርቅ ቅድሚያ እንዲሰጡ እና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል የህወሓት-መራሹ የትግራይ ክልል አስተዳደር ባለስልጣናት ኦባሳንጆ ነሐሴ 18 ቀን በመቐለ ያደረጉት ጉብኝት ያለ ቅድመ ቀጠሮ የተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ ከፌደራል መንግስት በኩል ለሰላምና ደህንነት ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የተገኘ አዲስ ሃሳብም ሆነ ተጨባጭ ውጤት አለመኖሩን አስታውቀዋል። ክልሉ በሰኔ ወር ለድርድር መነሻ ይሆናሉ ያላቸውን አምስት ነጥቦች ያቀረበ ሲሆን፣ እነሱም “ኢኮኖሚያዊ እገዳውን እና ከበባውን ማንሳት፣ ወታደራዊ ከበባውን ማቆም እና የደህንነት ስጋቶችን መቀነስ፣ የተያዙ ቦታዎችን መመለስ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀደመ ቀያቸው መመለስ እንዲሁም የህወሓትን ህጋዊ እና ፖለቲካዊ ህልውና ማረጋገጥ” ናቸው።

ኦባሳንጆ በሰኔ ወር ውይይት አድርገው ከተመለሱ በኋላ በሁለት ሳምንት ውስጥ እመለሳለሁ ቢሉም ተከታታይ እርምጃ አለመወሰዱን ያስታወቀው ህወሓት-መራሹ አስተዳደር፣ ባለፉት አራት ዓመታት የተደጋገሙ ያልተፈጸሙ ቃል ኪዳኖችን የመድገም ፍላጎት እንደሌለው ገልጿል። ሆኖም ሂደቱ በዋና ዋና ዓለም አቀፍ አጋሮች የሚደገፍ ከሆነ በጊዜ የተገደበ ድርድር ለማድረግ አሁንም ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።

ዜና:  #ኦባሳንጆ የመቐለ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ፤  #ህወሓት ለድርድር ቅድመ-ሁኔታዎችን አስቀመጠ።መቐለ: የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት   ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ  #መቐለ ያደረ...
25/08/2026

ዜና: #ኦባሳንጆ የመቐለ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ፤ #ህወሓት ለድርድር ቅድመ-ሁኔታዎችን አስቀመጠ።

መቐለ: የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ #መቐለ ያደረጉትን ያልተጠበቀ ጉብኝት ያጠናቀቁ ሲሆን፣ ህወሓት መራሹ የ #ትግራይ አስተዳደር ከፌደራል መንግስት ጋር ወደ አዲስ ድርድር ለመግባት ባስቀመጣቸው ቅድመ-ሁኔታዎች ምክንያት የሰላም ሂደቱ አዲስ ውጥረት አስተናግዷል።

በውይይቱ ወቅት ህወሓት-መራሹ አስተዳደር የኢኮኖሚ እገዳዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ፣ ወታደራዊ ከበባዎች እንዲቆሙ፣ ህገ-መንግስታዊ ወሰኖች እንዲከበሩ፣ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ እና የህወሓት ህጋዊና ፖለቲካዊ ህልውና እንዲረጋገጥ የሚሉ ጥብቅ ጥያቄዎችን አቅርቧል። ኦባሳንጆ ጥያቄዎቹን ይዘው ከፌደራል ባለስልጣናት ጋር ከተነጋገሩ በኋላ በሁለት ሳምንት ውስጥ እንደሚመለሱ ቃል ቢገቡም፣ የትግራይ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ግን በአዲስ አበባ በኩል ሂደቱን በቅንነት የመምራት ፍላጎት አለመኖሩን አሳውቋል።

የክልሉ አስተዳደር ባለፉት አራት ዓመታት የተደጋገሙ ውጤት አልባ ውይይቶችን የመድገም ፍላጎት እንደሌለው ገልጾ፣ በዓለም አቀፍ አካላት የሚደገፍና የጊዜ ገደብ ያለው ድርድር ከተፈለገ በመጀመሪያ በፌደራል መንግስቱ በኩል የሚፈጸሙ ትንኮሳዎችና እገዳዎች መቆም እንዳለባቸው አስገንዝቧል።

የቀድሞው የናይጀርያ ፕሬዝደንት በዚህ ዓመት ሰኔ ወር ወደ መቐለ ተጉዘው ከህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል እና ከሌላኛው የስራ አስፈፃሚ አባል አዲስአለም ባሌማ ጋ መወያየታቸው አይዘነጋም።

ዜና: በትግራይ የመውሊድ በዓል በአየር ጥቃት ስጋት ምክንያት በሌሊት ሊከበር ነው::መቐለ- በቅርብ ጊዜያት እያጋጠሙ ባሉ የድሮን ጥቃቶች ምክንያት በነዋሪዎች ላይ የተፈጠረውን ስጋት ለመቀነስ...
24/08/2026

ዜና: በትግራይ የመውሊድ በዓል በአየር ጥቃት ስጋት ምክንያት በሌሊት ሊከበር ነው::

መቐለ- በቅርብ ጊዜያት እያጋጠሙ ባሉ የድሮን ጥቃቶች ምክንያት በነዋሪዎች ላይ የተፈጠረውን ስጋት ለመቀነስ፣ በትግራይ ክልል የሚከበረው 1,501ኛው የመውሊድ በዓል በአደባባይ ሳይሆን በሌሊት መስጂዶች ውስጥ ብቻ እንደሚከበር የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ።

የምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሀጂ ሙሐመድ ካህሳይ እንዳሉት፣ ውሳኔው የተላለፈው ተከታታይ የድሮን ጥቃቶች የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው እና ሃይማኖታዊ በዓላትን በነጻነት ለማክበር አስቸጋሪ በመሆኑ ነው። በመሆኑም በዓሉ በዋና ዋና መስጂዶች ዱዓ እና መንዙማ በመቅራት ብቻ ይከናወናል።

ከቀናት በፊትም በተመሳሳይ የደህንነት ስጋት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን የሚያሰባስበው የመቐለ የአሸንዳ በዓል አከባበር መሰረዙ ይታወሳል።

ዜና: በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ  #ትግራይ ተጨማሪ የድሮን ጥቃቶች መፈጸማቸው ተገለጸ፤ የግጭት ስጋቱም እንደቀጠለ ነውመቐለ: በደቡባዊ ትግራይ ራያ አዘቦ ወረዳ ገነቴ በተባለ ቦታ እና በሰ...
24/08/2026

ዜና: በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ #ትግራይ ተጨማሪ የድሮን ጥቃቶች መፈጸማቸው ተገለጸ፤ የግጭት ስጋቱም እንደቀጠለ ነው

መቐለ: በደቡባዊ ትግራይ ራያ አዘቦ ወረዳ ገነቴ በተባለ ቦታ እና በሰሜን ምዕራብ ትግራይ እንደባጉና አካባቢ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። ይህም በክልሉ ያለውን የጸጥታ ስጋት የበለጠ አባብሶታል።

በጥቃቱ ሳቢያ የደረሰው የሰው ጉዳት ወይም የንብረት ውድመት መጠን በይፋ አልተረጋገጠም፤ የአካባቢው ባለስልጣናትም እስካሁን ይፋዊ መግለጫ አልሰጡም።

ይህ አዲስ የድሮን ጥቃት የተሰማው በትግራይ ክልል ዋና ከተማ #መቐለ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ከ5 ህፃናት ጨምሮ ቢያንስ 13 ሰዎች መቁሰላቸውን የዓይደር ሆስፒታል ይፋዊ መግለጫ ባወጣ በሰሞኑ ነው። በመቐለ የተፈጸመው ጥቃት ለመኖሪያ አካባቢዎች አቅራቢያ የደረሰ ሲሆን በቤት-ንብረት ላይም ጉዳት አድርሷል። በዚሁ ዕለት በመቐለ ኩሓ አካባቢ ሁለተኛ ጥቃት መፈጸሙ የተገለጸ ቢሆንም በወቅቱ የደረሰ የሰው ጉዳት አልተዘገበም።

በዚህ ወር በትግራይ ውስጥ ከተፈጸሙት ተከታታይ የድሮን ጥቃቶች መካከል በመቐለ የተከሰተው አንዱ ነው። እንደ አካባቢው ባለስልጣናት ዘገባ፣ ከትግራይ ዋና ከተማ መቐለ 15 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በሚገኘው #ዳንደራ አካባቢ ባለፈው ሳምንት በተፈጸመ ጥቃት የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ ሌላ 1 ሰው ደግሞ ቆስሏል። ቀደም ሲል ደግሞ በራያ አላማጣ ወረዳ ሌላ የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ተዘግቦ ነበር።

የእርስ በእርስ ውጥረቱ መጨመር እና ተከታታይ የአየር ጥቃቶች በክልሉ ትልቁን ዓመታዊ ባህላዊ በዓል አስተጓጉለዋል። ባለስልጣናት በጥቃቱ ስጋት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ስታዲየም ያከማች የነበረውን ዋናውን የመቐለ የአሸንዳ በዓል አከባበር ሰርዘዋል።

ይህ አዲስ ጥቃት የተፈጸመው በትግራይ ክልል አመራሮች እና በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት መካከል ባለው የፖለቲካ ውጥረት ምክንያት እ.ኤ.አ. በ2022 በፕሪቶሪያ ስምምነት የተጠናቀቀው ጦርነት እንዳገረሽ የሚሰጋበት ሁኔታ ባለበት ወቅት ነው።

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ለእነዚህ ተከታታይ የአየር እና የድሮን ጥቃቶች ኃላፊነት መውሰዱን በይፋ አላሳወቀም።

ዜና: በአምስተርዳም ዳም ስኩዌር ለትግራይ ሴቶችና ለዘውዱ ሃፍቱ ፍትህ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደበኔዘርላንድስ አምስተርዳም በሚገኘው ታዋቂው ዳም ስኩዌር አደባባይ ለዘውዱ ሃፍቱ እና ለ...
22/08/2026

ዜና: በአምስተርዳም ዳም ስኩዌር ለትግራይ ሴቶችና ለዘውዱ ሃፍቱ ፍትህ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ

በኔዘርላንድስ አምስተርዳም በሚገኘው ታዋቂው ዳም ስኩዌር አደባባይ ለዘውዱ ሃፍቱ እና ለሌሎች ግፎች ለተፈፀመባቸው የትግራይ ሴቶችና ልጃገረዶች ፍትህ የሚጠይቅ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። ተሰልፈው የወጡት ሰልፈኞች ለዘውዱ እና ለሁሉም ዘውዱዎች ፍትህ እንዲሰጥ፣ የትግራይ ሴቶች በሰላም እና በደህንነት የመኖር መብታቸው እንዲከበር እንዲሁም ለተበደሉት ድምፅ እንደሚሆኑ በአንድ ድምፅ አውጀዋል።

በሰልፉ ላይ የተሳተፉት ወገኖች በሴቶች ላይ የተፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶች እና የመብት ጥሰቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙና በድርጊቱ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የተሳተፉ አካላት በህግ ፊት ቀርበው ተጠያቂ እንዲሆኑ አጥብቀው ጠይቀዋል። በተጨማሪም በሴቶችና ልጃገረዶች ላይ በሚደርሱ በደሎች ላይ የሚታየው ዝምታ እንዲያበቃና ህብረተሰቡ ድምፁን እንዲያሰማ ጥሪ አቅርበዋል።

ሰልፈኞቹ መልእክታቸውን በኢትዮጵያ ለሚገኙ የኔዘርላንድስ እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች፣ ለአፍሪካ ህብረት፣ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እና ለተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ያደረሱ ሲሆን፣ ሙሉ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ቃላቸውን ጠብቀው ትግላቸውን እንደማያቋርጡ ገልፀዋል።

የዚህ ህዝባዊ ቁጣና የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ በ32 ዓመቷ ዘውዱ ሀፍቱ ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ እና ተከተሎ የመጣው የህግ ሂደት ነው። በነሐሴ 2015 ዓ.ም. በዘውዱ ላይ ከተፈፀመው አሰቃቂ ጥቃትና ግድያ ጋር በተያያዘ ቀደም ሲል የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩ ተከሳሾችን በቅርቡ የመቐለ መካከለኛ ፍርድ ቤት በነፃ ማሰናበቱ በትግራይና በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ተሟጋቾች ዘንድ ትልቅ ቅሬታና ቁጣን አጫሯል።

ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ በፆታ ተኮር ጥቃቶች ላይ የሚሰጠውን የፍትህ ስርዓት ክፍተት የሚያሳይ ነው በሚል የተቃወሙት ሰልፈኞቹ፣ በወንጀሉ ላይ የተሳተፉ አካላት በሙሉ በህግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ፍትህ እንዲያገኙ አጥብቀው ጠይቀዋል።

https://youtu.be/j09jxWPlI_s
21/08/2026

https://youtu.be/j09jxWPlI_s

በዛሬው የዜና ጥቅል፤ አሜሪካና #ኢትዮጵያ የፈረሙት የመከላክያ ስምምነት ምንድነው? ይዘን ቀርበናል። #ህወ...

 #ዜና: በኤሌክትሪክ በሚሰሩ ሳይክሎች የተገጩት የጣልያኗ  #ኮሞ ከተማ ከንቲባ ከእንግዲህ በከተማዋ ሳይክሎች እንዳይነዱ አገዱ::በ  #ጣልያን ኮሞ ከተማ ከንቲባ አሌሳንድሮ ራፒንስ በኤሌክት...
21/08/2026

#ዜና: በኤሌክትሪክ በሚሰሩ ሳይክሎች የተገጩት የጣልያኗ #ኮሞ ከተማ ከንቲባ ከእንግዲህ በከተማዋ ሳይክሎች እንዳይነዱ አገዱ::

በ #ጣልያን ኮሞ ከተማ ከንቲባ አሌሳንድሮ ራፒንስ በኤሌክትሪክ በሚሰራ ሳይክል አደጋ ከተመቱ በኋላ ተሽከርካሪዎቹ በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ የሚከለክል ውሳኔ አስተላለፉ።

ከንቲባው ውሳኔውን ያስተላለፉት የከተማዋን ነዋሪዎችና የጎብኚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሆነ ገልጸዋል። እንደ ውሳኔው ከሆነ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በጥቃቅን የከተማዋ 30 ጎዳናዎች ላይ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሳይክሎችን ማሽከርከር ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ይሆናል።

ከንቲባ ራፒንስ ለጣልያን ዜና አገልግሎት በሰጡት አስተያየት “ሰዎች ውሳኔ የሚሰጡት ከአጋጠማቸው ልምድ ተነስተው ነው፤ እኔም በእነዚህ አውሬ ሳይክሎች የደረሰብኝን ጉዳት በደንብ አውቀዋለሁ” ብለዋል።

በርካታ የ #አውሮፓ ከተሞች የኤሌክትሪክ ሳይክሎች የትና እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የሚወስኑ ደንቦችን ያወጡ ቢሆንም፣ ከተለመዱት በእግር በሚሸከረከሩ መደበኛ ሳይክሎች ላይ ግን እስካሁን የተጣለ እገዳ የለም።

 #ዜና: በትግራይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በተፈጸመ የአየር ጥቃት 14 ሰዎች መቁሰላቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀመቐለ— የ  #ትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ነሐሴ 14 ቀን 201...
21/08/2026

#ዜና: በትግራይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በተፈጸመ የአየር ጥቃት 14 ሰዎች መቁሰላቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ

መቐለ— የ #ትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. #መቐለ ከተማ በሚገኙ “የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በፌደራል መንግሥት” የተፈጸመውን የአየር ጥቃት እንደሚያወግዝ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በጥቃቱ ሳቢያ “14 መምህራንና የቤተሰቦቻቸው አባላት አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ ጥረትና ድካም ባፈሩት ንብረት ላይም ከፍተኛ ውድመት” መድረሱን ቢሮው ገልጿል።

“በትግራይ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን በደልና ውድመት” የሚቃወመው የትግራይ ትምህርት ቢሮ መግለጫ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው መምህራንና የቤተሰብ አባላት ፈጣን ምህረትና ጤንነትን ተመኝቷል። በተጨማሪም በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ይህንን ድርጊት እንዲያወግዙና ለተጎዱት መምህራንና ቤተሰቦቻቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ትላንት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ ሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ የአውሮፕላን ጥቃቶች ተፈጽመዋል።

የመጀመሪያው ጥቃት በሐወልቲ ክፍለ ከተማ “ዳ ማርያም” ቤተክርስቲያን አቅራቢያ የሚገኙ የመኖሪያ ቤቶችን ላይ ሲሆን፣ ሁለተኛው ጥቃት ደግሞ በኲሓ አካባቢ ተመዝግቧል።

በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ ሰዎች፣ ህፃናትን ጨምሮ፣ ወደ ዓይደር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድንገተኛ ህክምና ክፍል ተወስደው አስፈላጊው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። ይህ ድርጊት የተፈጸመው በፌደራል መንግሥትና በህወሓት ባለስልጣናት መካከል ያለው አጠቃላይ ውጥረት በድጋሚ እያየለ በመጣበትና የሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ስጋት ላይ በወደቀበት ወቅት ነው።

“ትዕግስቱም ወሰን ያለው በመሆኑ”  #ህወሓት መራሹ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ጣልቃ ገብነት ጥሪ አቀረበመቐለ: በትግራይ እንደ አዲስ የተጋጋ...
21/08/2026

“ትዕግስቱም ወሰን ያለው በመሆኑ”

#ህወሓት መራሹ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ጣልቃ ገብነት ጥሪ አቀረበ

መቐለ: በትግራይ እንደ አዲስ የተጋጋጠውን ውጥረትና በቅርቡ የተፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ህወሓት-መራሹ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ጣልቃ ገብነት ጥሪ አቀረበ። #ትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በመቐለ ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግሥት እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎች ቀጣናውን ወደ አዲስ አጥፊ ጦርነት ከማስገባታቸው በፊት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዝምታውን ሰብሮ ጥቃቶቹን በግልጽ እንዲያወግዝ ጠይቋል።

በመግለጫው መሠረት፣ የፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም መስተጓጎሉን ተከተሎ የፌደራል መንግሥት “በራያ፣ #እንትጮ፣ #ሽራሮ” እና በሌሎች አካባቢዎች የድሮን ጥቃቶችንና የወታደራዊ ኃይል እንቅስቃሴዎችን አጠናክሯል። በተለይም ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ሸረሪና በተባለ ቦታ የተፈጸመው ጥቃት፣ ነሐሴ 4 ቀን በደቡባዊ ትግራይ #መረዋ ወረዳ በሚገኝ ትምህርት ቤት ላይ የተካሄደው የድሮን ድብደባ፣ እንዲሁም በዋጃ ቲሙጋ ወረዳ ማርያም ኩቢ መንደር የተፈጸሙ የከባድ መሣሪያ ጥቃቶች በሰላማዊ ሰዎችና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም ነሐሴ 12 ቀን በ #መቐለ አቅራቢያ በሚገኘው #ዳንደራ መንደር እንዲሁም በቅርቡ በመቀሌ ከተማ ሐወልቲ ክፍለ ከተማ ሞሞና ሰፈር በሚገኙ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በተፈጸሙ የአየር ጥቃቶች ሕፃናትን ጨምሮ ቢያንስ 13 ሰዎች መቁሰላቸውና መኖሪያ ቤቶች መደመሰሳቸው በመግለጫው ተጠቅሷል። እነዚህ ጥቃቶች የሰዎችን ሕይወት ከመቀጠፋቸው ባለፈ፣ በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ ፍርሃት የፈጠሩና የሴቶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ቅርሶች መግለጫ የሆነውን የእሸንደ በዓል አከባበር ሆን ብለው ለማስተጓጎል የተደረጉ ናቸው ሲል የህወሓት አስተዳደር ከሷል።

ለሰላምና ለቀጣናው ረጋታ ሲሉ እስካሁን ከፍተኛ ትዕግስት ማሳየታቸውን የጠቀሰው ቢሮው፣ ይህ ትዕግስት ግን እንደ ድክመት ወይም ሕዝብንና ግዛትን የመጠበቅ አቅም እንደሌለው ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት አሳስቧል። የትግራይ አስተዳደር ለሰላማዊ ውይይት ያለው ቁርጠኝነት የጸና ቢሆንም ትዕግስቱም ወሰን ያለው በመሆኑ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አሁኑኑ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪውን አስተላልፏል።

 #ዜና: ኢትዮጵያና  #አሜሪካ በወታደራዊና በዲፕሎማሲ ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ወደ አዲስ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችላቸውን ሁለንተናዊ የስትራቴጂክ መከላከያና ደህንነት ትብብር ለመስረፅ መስ...
21/08/2026

#ዜና: ኢትዮጵያና #አሜሪካ በወታደራዊና በዲፕሎማሲ ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ወደ አዲስ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችላቸውን ሁለንተናዊ የስትራቴጂክ መከላከያና ደህንነት ትብብር ለመስረፅ መስማማታቸውን የመከላከያና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቁ።

መቐለ- ስምምነቱ የተደረሰው በኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር በሜጀር ጄኔራል የተመራ ከፍተኛ የወታደራዊ ልዑክ በ #ዋሺንግተን ባደረገው የሥራ ጉብኝት ወቅት ነው። የኢትዮጵያ ልዑክ በፔንታጎን ከአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ረዳት የመከላከያ ሚኒስትር ብሪያን ጄ. ኤሊስ እና ከሌሎች ከፍተኛ የመከላከያ ባለስልጣናት ጋር ተወያይቷል።

እንደ መከላከያ ሚኒስቴር ገለጻ፣ የታሰበው ስትራቴጂካዊ ትብብር በዘላቂ ሀገራዊ ጥቅም፣ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በላቀ እምነት እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድና በሰፊው ቀጣና ዘላቂ ሰላምና ጸጥታን ለማረጋገጥ በሚደረጉ የጋራ ጥረቶች ላይ የተመሰረተ ይሆናል። ሜጀር ጄኔራል ተሾመና ብሪያን ኤሊስ በውይይቱ ወቅት የተደረሱ ማዕቀፎችን ወደ ተግባር ለመቀየርና የሁለትዮሽ መከላከያ ግንኙነቱን ወደፊት የሚቀጥል ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከአሜሪካ በመጣ የወታደራዊ ቡድን የሚሰጠውና በሰብአዊ መብቶች እንዲሁም በዓለም አቀፍ ወታደራዊ ሕጎች ላይ ያተኮረው ስልጠና በኢትዮጵያ ሰላም ማስከበር ማዕከል ተጀምሯል። በመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዳይሬክቶሬት የስልጠና ዳይሬክተር ሌተና ኮሎኔል ምናሴ ሀይሉ፣ የኢትዮጵያ ቀጣናዊ ተጽዕኖ እያደገ መምጣቱ ሀገራት ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ እንዳበረታታ ገልጸው፣ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን አለመረጋጋት ለመቅረፍ
አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአሜሪካው ስልጠና ቡድን አስተባባሪ ሌተና ኮሎኔል ዛካሪ ማክአርተር በበኩላቸው፣ ዋሺንግተን ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኗን ገልጸው፣ ኢትዮጵያ በተለይም በሶማሊያ ሰላምና ጸጥታን ለማስፈን የምታደርገውን ወሳኝ ሚና አድናንቀዋል። ይህ አዲስ ስምምነት ሁለቱ ሀገራት በጋራ ወታደራዊ እርምጃዎችን የማቀድና የማስፈጸም አቅማቸውን እንደሚያሳድገው ተገልጿል።

Address

London

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekelle Central Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share