Addis Daily

Addis Daily Athletics and Ethiopian football News, Information and Event. NEWS , INFORMATION

በሲድኒ ማራቶን አዲሱ ጎበና🇪🇹 ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ::ለ24ኛ ጊዜ በተደረገው የሲድኒ ማራቶን ውድድር አዲሱ የገባበት 2 ሰአት 04 ደቂቃ 42 የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖም ተመዝግ...
30/08/2026

በሲድኒ ማራቶን አዲሱ ጎበና🇪🇹 ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ::

ለ24ኛ ጊዜ በተደረገው የሲድኒ ማራቶን ውድድር አዲሱ የገባበት 2 ሰአት 04 ደቂቃ 42 የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖም ተመዝግቧል።

ባለፈው ዓመት ሀይለማርያም ኪሮስ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፎ የነበር ቢሆንም በዚህ ዓመት አዲሱ ጎበና ከአንድ ድቂቃ በላይ በማሻሻል አሸንፏል።

በውድድሩ ጭምዴሳ ደበሌ 2ኛ ደርጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ 2 ስዓተ 04 ደቂቃ 46 ሰከንድ የገባበት ስዓት ሆኗል።

ጀማል መኮንን 5ኛ ሲወጣ የባለፈው ዓመት አሸናፊ ሀይለማርያም ኪሮስ ደግሞ 6ኛ ደርጃን ይዞ ውድድሩን ፈጽሟል።

በሴቶች በተደረገው ውድድር ኬንያዊቷ ፒርስ ጅፕችርችር🇰🇪 አሸናፊ ሆናለች። 2:18: የገባችበት ስዓት ሆኗል።

ኢትዮጵያዊያኑ ሹሬ ደምሴ፣ ሄቨን ሀይሉ እና መሰረት አበባየሁ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

በዓለም አትሌቲክስ የሜጀር ደረጃ ከተሰጣቸው ማራቶኖች መካከል አንዱ የሆነው የአውስትራሊያው ሲድኒ ማራቶን ነገ ይካሄዳል።   |  በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚሳተፉበት በዚህ ማራቶን በወንዶች ም...
29/08/2026

በዓለም አትሌቲክስ የሜጀር ደረጃ ከተሰጣቸው ማራቶኖች መካከል አንዱ የሆነው የአውስትራሊያው ሲድኒ ማራቶን ነገ ይካሄዳል።

| በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚሳተፉበት በዚህ ማራቶን በወንዶች ምድብ ከዓለማችን ፈጣን ሰዓቶች መሀል የአንዱ ባለቤት የሆነው አትሌት ሲሳይ ለማ🇪🇹 የአሽናፊነት ቅድመ ግምቱን አግኝቷል።

አትሌት ሲሳይ በማራቶን 2 ሰዓት 01:48 የሆነ ፈጣን ሰዓት ያለው ሲሆን፤ የቦታው ክብረወሰን ባለቤቱ ኃይለማሪያም ኪሮስ፣ ዳዊት ወልዴ፣ ልኡል ገብረስላሴ፣ ሰይፉ ቱራ እና አዲሱ ጎበና ሌሎች ጠንካራ ኢትዮጵያውያን ተፎካካሪዎች ናቸው።

በ10 ሺህ ሜትር እና በሀገር አቋራጭ ውድድሮች በርካታ ውጤት ያስመዘገበው አትሌት ሀጎስ ገብረሕይወት ለመጀመሪያ ጊዜ ሲድኒ ላይ በማራቶን ይሳተፋል።

በሴቶች ምድብም ቢሆን ጠንካራ የሆኑ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይካፈላሉ።

ሹሬ ደሚሴ፣ ሄቨን ኃይሉ፣ መሠረት አበባየሁ እና አበሩ አያና ለአሸናፊነት የሚሮጡ ሲሆን፤ ኬንያዊቷ ፔሬስ ጄፕቺርቺር🇰🇪 የኢትዮጵያውያኑ ዋና ተፎካካሪ እንደምትሆን ይጠበቃል።

የሲድኒ ማራቶን እ.አ.አ የ2000 የሲድኒ ኦሊምፒክ መካሄድን ምክንያት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን፤ የወንዶች የቦታው ክብረወሰን በኃይለማሪያም ኪሮስ የተያዘ ነው።

የዓለም ግማሽ ማራቶን የዓለም ሪኮርድ በኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ተሰበረ::    |  ዛሬ በአርጀንቲና🇦🇷 መዲና ቦነስ አይረስ በተካሄደውና በዓለም አቀፍ አትሌቲክስ እውቅና በተሰጠው የግማሽ...
23/08/2026

የዓለም ግማሽ ማራቶን የዓለም ሪኮርድ በኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ተሰበረ::

| ዛሬ በአርጀንቲና🇦🇷 መዲና ቦነስ አይረስ በተካሄደውና በዓለም አቀፍ አትሌቲክስ እውቅና በተሰጠው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ርቀቱን በ56፡51 ሰዓት በመጨረስ የዓለም ሪኮርድን ተቆጣጥሯል።

ዮሚፍ በዚህ ድንቅ ብቃቱ በኡጋንዳዊው ጃኮብ ኪፕሊሞ🇺🇬 ፖርቹጋል፣ ሊዝበን ላይ ተመዝግቦ የነበረውን የ57፡20 ሰዓት የዓለም ሪኮርድ (ገና የፀደቀ ባይሆንም) በ29 ሰከንድ አሻሽሎታል። በዚህም አትሌቱ በኦክቶበር 2024 ቫሌንሺያ ላይ በ57፡30 አስመዝግቦት የነበረውን የዓለም ሪኮርድ በድጋሚ በእጁ ማስገባት ችሏል።

ኪፕሊሞ ባለፈው ዓመት ባርሴሎና ላይ 56፡42 ገብቶ የነበረ ቢሆንም የውድድሩ ሁኔታዎች ከዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ህጎች ጋር ሙሉ በሙሉ ባለመጣጣማቸው ምክንያት እንደ ዓለም ሪኮርድ ሊፀድቅለት አልቻለም ነበር።

በቦነስ አይሬሱ የሴቶች ውድድር ደግሞ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ፎተን ተስፋይ ርቀቱን በ1፡03፡57 ሰዓት በመጨረስ አሸንፋለች።

በ2ዐ26 13ኛ ከተማ በሆነችው የፖላንዷ ሲሌሲያ  የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያዊያን🇪🇹 አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ለአሸናፊነት ቅድመ ግምት አግኝተዋል፡፡ በሴቶች 5ሺህ እና 15ዐዐ ሜትር...
23/08/2026

በ2ዐ26 13ኛ ከተማ በሆነችው የፖላንዷ ሲሌሲያ የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያዊያን🇪🇹 አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ለአሸናፊነት ቅድመ ግምት አግኝተዋል፡፡

በሴቶች 5ሺህ እና 15ዐዐ ሜትር እንዲሁም በወንዶች 3ሺህ ሜትር መሰናክል ኢትዮጵያዊያኑ ከሚካፈሉባቸው ርቀቶች መካከል ናቸው፡፡

በሴቶች 5000 ሜትር ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉ ሲሆን ፤ ልቅና አምባው ፣ፍሬወይኒ ሃይሉ፣ አሳየች አይቼው እና የኔዋ ንብረት ከወዲሁ የአሸናፊነት ቅድመ ግምቱን አግኝተዋል፡፡

በ1500 ሴቶች ደግሞ አስቀድማ ለዳይመንድ ሊጉ ፍፃሜ ውድድር ያለፈችው ብርቄ ኃይሎም ፣ ሳሮን በርሄ እና ፅጌ ድጉማ ይጠበቃሉ፡፡

ሳሙኤል ፍሬው እና ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር ላይ እንደሚሳተፉ ተረጋግጧል፡፡

የዳይመንድ ሊጉ 13ኛ ከተማ በሆነችው ሴሊሲያ የአጭር ፣ መካከለኛ እና የሜዳ ተግባራት ውድድሮች ይካሄዱባታል፡፡

የ2026 የዋንዳ ዳይመንድ ሊግ 12ኛ መዳረሻ ከተማ የስዊዘርላንዷ ሉዛን ከተማ ስትሆን በመድረኩ 9 ኢትዮጵያውያን🇪🇹 አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ይሳተፋሉ።     |   ዛሬ ከአመሻሽ አንድ ሰ...
21/08/2026

የ2026 የዋንዳ ዳይመንድ ሊግ 12ኛ መዳረሻ ከተማ የስዊዘርላንዷ ሉዛን ከተማ ስትሆን በመድረኩ 9 ኢትዮጵያውያን🇪🇹 አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ይሳተፋሉ።

| ዛሬ ከአመሻሽ አንድ ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ መካሄድ የሚጀምር ሲሆን በሴቶች 800ሜ ሳይዳ ፀሀየ በብቸኝነት ስትሳተፍ ኔዘርላንዳዊቷ ቦል-ፌሜክ፣ አሜሪካዊቷ ሁርታ ክሌከር፣ ከቦትስዋና ኖዌ ኦራቲሌ፣ ከኬኒያ ኦዲራ ሊላን ጠንካራ ተፎካካሪ ናቸው።

በ 5000ሜ ወንዶች ካሀይሪ ቤጂጋ፣ ኩማ ግርማ፣ ሽመልስ ንጉሴ፣ መዝገቡ ስሜ እንዲሁም ጌትነት ዋለ ተሳታፊ ናቸው። ከባህሬን ብርሀኑ ባለው ከአሜሪካ ግራንት ፊሸርና ሌሎችም ይጠበቃሉ።

በሴቶች 3 ሺህ ሜ መሰናክል ደግሞ ኬና ቱፉ፣ አለምናት ዋለ፣ መሰረት የሻነህ ሲሳተፉ ከኬንያ ፌይዝ ቼሮቲች ለአሸናፊነት ቅድመ ግምት አግኝታለች።

ውድድሩ ቀደም ብሎ የሚጀምር ቢሆንም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ርቀቶች ከአመሻሽ 3 ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል።

ማሪያ ፔሬዝ በግማሽ ማራቶን እርምጃ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን አሰመዘገበች።   |   ስፔናዊቷ ማሪያ ፔሬዝ🇪🇦 በቢርሚንግሃም በተካሄደው የአውሮፓ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች ግማሽ ማራቶን ...
15/08/2026

ማሪያ ፔሬዝ በግማሽ ማራቶን እርምጃ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን አሰመዘገበች።

| ስፔናዊቷ ማሪያ ፔሬዝ🇪🇦 በቢርሚንግሃም በተካሄደው የአውሮፓ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች ግማሽ ማራቶን እርምጃ ውድድር 1:30:06 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ አዲስ የዓለም ክብረወሰን በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፋለች።

በ35 ኪሎሜትር እርምጃም የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ፔሬዝ፣ በ2018 በበርሊን ካሸነፈች በኋላ 2ኛውን የአውሮፓ ሻምፒዮና ድሏን ማግኘቷ ነዉ።

በውድድሩ ጣሊያናዊቷ አሌክሳንድሪና ሚሃይ የብር፣ የዩክሬኗ ሊዩድሚላ ኦልያኖቭስካ ደግሞ የነሐስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።

የ30 ዓመቷ ማሪያ ፔሬዝ በፓሪስ ኦሊምፒክ የማራቶን ርምጃ ውድድር አሸናፊ ስትሆን በቡዳፔስት እና ቶኪዮ ዓለም ሻምፒዮና በ35 እና 20 ኪሎ ሜትር የእርምጃ ውድድር የድርብ ድል ባለቤት ናት።

09/08/2026
በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ🇪🇹 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ🥇 አገኘች::    |   በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ፅጋብ እና ሽቶ ጉሚ 1ኛ እና 2ኛ በመሆን ውድድራቸ...
09/08/2026

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ🇪🇹 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ🥇 አገኘች::

| በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት ዮርዳኖስ ፅጋብ እና ሽቶ ጉሚ 1ኛ እና 2ኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

ዮርደዳኖስ ፅጋብ የውድድሩ አሸናፊ በመሆን ወርቅ ሜዳሊያ🥇 ስታገኝ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 8:43.65 ወስዶባታል። ሽቶ ጉሚ 8:45.06 በሆነ ጊዜ 2ኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ🥈 ስታገኝ፣ ዩጋንዳዊቷ ቻሪቲ ቼሮፕ 3ኛ🥉 ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።

ይህ ውድድር ትናንት በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ከተመዘገበው የወርቅ ሜዳሊያ በኋላ በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮናው የተገኘ 2ኛው ወርቅ ሆኗል።

ኢትዮጵያ🇪🇹 ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ🥇 አስመዘገበች።   |   በአሜሪካ ኦሪገን እየተካሄደ ባለው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና፤ በ...
08/08/2026

ኢትዮጵያ🇪🇹 ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ🥇 አስመዘገበች።

| በአሜሪካ ኦሪገን እየተካሄደ ባለው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና፤ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ የወርቅና ብርና ሜዳሊያ አግኝታለች።

አትሌት አልማዝ ዮሐንስ ርቀቱን በ9:15.81 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።

አትሌት ወሰኔ አሰፋ ደግሞ 9:30.50 በሆነ ጊዜ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን🥈 በመያዝ የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች።

ኢትዮጵያ እስካሁን በውድድሩ አንድ የወርቅ🥇 ፣ ሁለት🥈🥈 የብር እና አንድ የነሀስ🥉 ሜዳልያ አግኝታለች።

Address

London

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Daily posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Daily:

Shortcuts

Share