29/10/2025
ይድረስ:-
ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች፣
ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማህበር፣
ለማህበራት ማደራጃ እና መምሪያ
ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን
እነሆ ንፁሃን ክርስቲያኖች ሲገደሉ፣ ንብረታቸው ሲቃጠል፣ ሲፈናቀሉ ሰባት ዓመታት ተቆጠሩ።
ካህናት አባቶች በመሰውያው ፊት በጠራራ ፀሀይ ተገድለዋል። የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ተደድበዋል፣ ቤተክርስቲያን ታቃጥላለች፣ ምዕመናን በየለቱ ባልተቋረጠ መንገድ ሲገደሉ ይውላሉ።
Global Orthodox Forum ይህ የሆነ ቦታ መቆም አለበት ብሎ ያምናል።
ይህ ሁሉ ዘግናኝ ግፍ ሲፈፀም መንግስት ህግን ከማስከበር ይልቅ ጉዳዩን በማባባስ አልፎም ከፖለቲካ ጋር በማነካካት ያልተገባ ትርጉም እንዲሰጠው በማድረግ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ነው።
የቤተክርስቲያኗ የበላይ ጠባቂ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳዩን ከማውገዝ እና መፍትሄ ከማፈላለግ ይልቅ ዝምታን በመምረጥ ግድያው እየተባባሰ እንዲሄድ አድርጓል።
ቤተክርስቲያን ከዩዲት ጉዲት ዘመን ቀጥሎ በ21ኛው ክ/ዘመን ታይቶ የማይታወቅ ፈተና ከገጠማት ድፍን 7 ዓመታትን አስቆጥራለች። ይህ የሚቀጥል ሲሆን ችገሩን የሚያስቆም መንግስትም ሆነ የቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ አልተገኘም። ለዚህ ብቸኛ መፍትሄው ምዕመኑ ተደራጅቶ ቤተክርስቲያኑን እና ራሱን ከአረመኔዎች መጠበቅ ሲሆን ለዚህም መሰባሰብ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
ቤተክርስቲያን በገዛ ሀገሯ ተሳዳጅ ሆና መኖር አትችልም። ቤተክርስቲያን ራሷ በሰራቻት ሀገር ፈፅሞ እየሞተች መኖር አይሆንላትም። ፍትህን ከነ ክብሯ ትፈልጋለች።
በዚህ ምክንያት በመላው ዓለም ያሉ ምዕመናንን በተለያዩ ማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ማሰባሰብ አስፈላጊ ስለሆነ Global Orthodox Forum የተሰኛ ጥምረት በዛሬው ዕለት ተመስርቷል።
እኛ በተለያዩ ዓለማት እና በሀገር ውስጥ የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን ይህንን የክርስቲያኖች ግድያ ለመመከት ከመሰባሰብ ውጭ የሚያቆምልን አባት ወይም የመንግስት አካል የለም ወደሚል ድምዳሜ ላይ የደረስን ሲሆን በኢትዮጵያ በአራቱም ማዕዘን፣ በአሜሪካ ፣ በአውሮፓ ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ እና ሌሎች አካባቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንቅስቃሴ ለመጀመር የታሰበ ሲሆን ይህንን የቴሌግራም ግሩፕ ለመላው አለም ማዳረስ ፣ በገጠር አካባቢ የሚገኙ ምዕመናን ማዳረስ የእያንዳንዱ የቤተክርስቲያን መቃጠል እና መውደም፣ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መፍረስ ያገባኛል የሚል ምዕመን ግዴታው መሆኑ አውቆ ከዛሬ ጀምሮ ሰዎችን በማስገባት አንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ( Strong Community) መፍጠር እንዳለብን ታምኖበታል።
በዚሁ መሰረት ካሁኑ ሰዓት ጀምሮ ይፋ የተደረገውን የቴሌግራም ግሩፕ በመላው አለም ለሚገኙ አማኞች እንድታሰራጩ እና ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ እያልን እናሳስባለን።
ቴሌግራም👇 https://t.me/globalortho21
ተጨማሪ መረጃዎችን ዘግይተን እናሳውቃለን።