Global Orthodox Forum

Global Orthodox Forum Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Global Orthodox Forum, News & Media Website, London.

በመላው ዓለም ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን ወደ አንድ ቋት የማሰባሰብ ዘመቻ መጀመሩን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው። የማሰባሰቡ ዋና ዓላማ ቤተክርስቲያንን ከባህል፣ ከቀኖና እና ከዶግማ ጥሰት መከላከል፣ ቤተክርስቲያን ከሚደርስባት ዘርፈ ብዙ ትንኮሳ ራሷን ችላ እንድትቆም ማድረግ ነው። ምዕመናን ይህን ቻናል በመላው አለም ተደራሽ እንዲሆን በባለቤትነት መንፈስ እንድትሰሩ እናሳስባለን።

ይድረስ:-ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች፣ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማህበር፣ለማህበራት ማደራጃ እና መምሪያለመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እነሆ ንፁሃን ክርስቲያ...
29/10/2025

ይድረስ:-

ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች፣

ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማህበር፣

ለማህበራት ማደራጃ እና መምሪያ

ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን

እነሆ ንፁሃን ክርስቲያኖች ሲገደሉ፣ ንብረታቸው ሲቃጠል፣ ሲፈናቀሉ ሰባት ዓመታት ተቆጠሩ።
ካህናት አባቶች በመሰውያው ፊት በጠራራ ፀሀይ ተገድለዋል። የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ተደድበዋል፣ ቤተክርስቲያን ታቃጥላለች፣ ምዕመናን በየለቱ ባልተቋረጠ መንገድ ሲገደሉ ይውላሉ።

Global Orthodox Forum ይህ የሆነ ቦታ መቆም አለበት ብሎ ያምናል።

ይህ ሁሉ ዘግናኝ ግፍ ሲፈፀም መንግስት ህግን ከማስከበር ይልቅ ጉዳዩን በማባባስ አልፎም ከፖለቲካ ጋር በማነካካት ያልተገባ ትርጉም እንዲሰጠው በማድረግ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ነው።

የቤተክርስቲያኗ የበላይ ጠባቂ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳዩን ከማውገዝ እና መፍትሄ ከማፈላለግ ይልቅ ዝምታን በመምረጥ ግድያው እየተባባሰ እንዲሄድ አድርጓል።

ቤተክርስቲያን ከዩዲት ጉዲት ዘመን ቀጥሎ በ21ኛው ክ/ዘመን ታይቶ የማይታወቅ ፈተና ከገጠማት ድፍን 7 ዓመታትን አስቆጥራለች። ይህ የሚቀጥል ሲሆን ችገሩን የሚያስቆም መንግስትም ሆነ የቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ አልተገኘም። ለዚህ ብቸኛ መፍትሄው ምዕመኑ ተደራጅቶ ቤተክርስቲያኑን እና ራሱን ከአረመኔዎች መጠበቅ ሲሆን ለዚህም መሰባሰብ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

ቤተክርስቲያን በገዛ ሀገሯ ተሳዳጅ ሆና መኖር አትችልም። ቤተክርስቲያን ራሷ በሰራቻት ሀገር ፈፅሞ እየሞተች መኖር አይሆንላትም። ፍትህን ከነ ክብሯ ትፈልጋለች።

በዚህ ምክንያት በመላው ዓለም ያሉ ምዕመናንን በተለያዩ ማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ማሰባሰብ አስፈላጊ ስለሆነ Global Orthodox Forum የተሰኛ ጥምረት በዛሬው ዕለት ተመስርቷል።

እኛ በተለያዩ ዓለማት እና በሀገር ውስጥ የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን ይህንን የክርስቲያኖች ግድያ ለመመከት ከመሰባሰብ ውጭ የሚያቆምልን አባት ወይም የመንግስት አካል የለም ወደሚል ድምዳሜ ላይ የደረስን ሲሆን በኢትዮጵያ በአራቱም ማዕዘን፣ በአሜሪካ ፣ በአውሮፓ ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ እና ሌሎች አካባቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንቅስቃሴ ለመጀመር የታሰበ ሲሆን ይህንን የቴሌግራም ግሩፕ ለመላው አለም ማዳረስ ፣ በገጠር አካባቢ የሚገኙ ምዕመናን ማዳረስ የእያንዳንዱ የቤተክርስቲያን መቃጠል እና መውደም፣ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መፍረስ ያገባኛል የሚል ምዕመን ግዴታው መሆኑ አውቆ ከዛሬ ጀምሮ ሰዎችን በማስገባት አንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ( Strong Community) መፍጠር እንዳለብን ታምኖበታል።

በዚሁ መሰረት ካሁኑ ሰዓት ጀምሮ ይፋ የተደረገውን የቴሌግራም ግሩፕ በመላው አለም ለሚገኙ አማኞች እንድታሰራጩ እና ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ እያልን እናሳስባለን።

ቴሌግራም👇 https://t.me/globalortho21

ተጨማሪ መረጃዎችን ዘግይተን እናሳውቃለን።

29/10/2025

#ልብ ሰባሪ ዜና

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ሀገረ ስብከት፣ ጉና ወረዳ፣ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ ውስጥ በታጠቁ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት፣ የሁለት ዓመት ህጻንን ጨምሮ 14 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን ከማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን የወጣው መረጃ አመለከተ።

ጥቃቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ፍርሃትና ስጋትን አስነስቷል።

ከስፍራው የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ገደማ ነው።

ታጣቂዎቹ፣ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑትን እነዚህን ግለሰቦች ከየቤታቸው በኃይል አስወጥተው በጥይት እንደገደሏቸው ተገልጿል።

ከተጎጂዎቹ መካከል ስድስቱ ጥቃቱ ከመፈጸሙ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ታፍነው መወሰዳቸውንም መረጃው አክሏል።

በዚህ አሰቃቂ ጥቃት ህይወታቸውን ካጡት መካከል የሁለት ዓመት ህጻን እንዲሁም የ76 ዓመት አዛውንት ይገኙበታል።

በተጨማሪም፣ ሁለት ሰዎች በደረሰባቸው ከባድ ጉዳት ምክንያት ለተሻለ ህክምና በአቅራቢያው ወደምትገኘው አቦምሳ ከተማ መወሰዳቸው ታውቋል።

የሟቾቹ የቀብር ሥነ ሥርዓት በአካባቢው በሚገኙት በገገሌ በዓለወልድ እና በሞዬ ቅዱስ ዮሐንስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በየመኖሪያ ቀያቸው መፈጸሙ ተገልጿል።

ይህ ጥቃት በአካባቢው ሲፈጸም የመጀመሪያው እንዳልሆነ ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሁኔታ ስምንት የእምነቱ ተከታዮች በታጠቁ ኃይሎች መገደላቸውን ምንጮች አስታውሰዋል።

ምንም እንኳን ጥቃቱን የፈጸመው አካል ማንነት በመረጃው ላይ በግልጽ ባይጠቀስም፣ የአርሲ ዞንን ጨምሮ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት "ሸኔ" ተብሎ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነግ) እና ሌሎች ታጣቂ ቡድኖች ይንቀሳቀሳሉ።

በእነዚህ አካባቢዎች በሚፈጠሩ ግጭቶች ወቅት ንጹሃን ዜጎች በተደጋጋሚ ለጥቃት ሲዳረጉ ቆይተዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ በአካባቢው የተፈጠረውን ውጥረት ለማረጋጋት የሀገር መከላከያ ሠራዊት በስፍራው መሰማራቱ ተገልጿል።

ሆኖም የአካባቢው ነዋሪዎች በቀጣይ ሊፈጠር በሚችል ጥቃት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደሚገኙ መረጃው አመላክቷል።

የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘገባ፣ በቀበሌው ያለው ስጋት ከፍተኛ በመሆኑ፣ የሀገረ ስብከቱ ጽህፈት ቤት ከመንግሥት ጋር በቅርበት በመስራት የባሰ ችግር እንዳይፈጠር መከላከል እንዳለበት አሳስቧል።

እስካሁን ድረስ ከፌደራልም ሆነ ከክልሉ መንግሥት ጥቃቱን አስመልክቶ በይፋ የተሰጠ መግለጫ የለም።

፩ One Media
Your #1 choice

Unity in News, Power in Voice.

በቴሌግራም ይጎብኙን👇

https://t.me/OneMedia21
https://t.me/OneMedia21
https://t.me/OneMedia21

በፌስቡክ ይጎብኙን👇

https://www.facebook.com/share/19e9vUSLNk/

በቲክቶክ👇

tiktok.com/

እጅግ አሳዛኝ ዜና በሸገር ሀገረ ስብከት ዓለም ገና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት  ቄስ ዮሐንስ ግርማ ቅዳሜ ለእሁድ  ለቅዳሴ አገጋግሎት በሎሊት ወደ ቤተክርስቲያን እየሄዱ ...
23/06/2025

እጅግ አሳዛኝ ዜና

በሸገር ሀገረ ስብከት ዓለም ገና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ቄስ ዮሐንስ ግርማ

ቅዳሜ ለእሁድ ለቅዳሴ አገጋግሎት በሎሊት ወደ ቤተክርስቲያን እየሄዱ ባሉበት ወቅት ቤተክርስቲያኑ በር መግብያ በር ላይ በጩቤ ማንነታቸው ባልታወቀ ተወግተው መገደላቸውን የመረጃ ምንጮች አድርሰውናል !

ከቅርብ ግዜ ወዲህ የቅድስት ቤተክርስቲያን ዲያቆናት ካህናትና መነኮሳት ባልታወቁ ሰዎች በሚል እየተገደሉ ነው ::

የአባታችንን ነፍስ ፈጣሪ ከቅዱሳኑ ጋር ይደምርልን ፣ ለቤተሰቡም መጽናናትን ያድልልን ፣

በአስቸኳይ ይፈቱ፣ #አባታችን ሊቀ ብርሃናት የኔታ ይባቤ በላይ ለምን ታሠሩ? የቅኔ፣የ፹፩መጻሕፍት፣የአቡሻኽር፣የጥበባት መምህሩ፣ የናዳ ገዳም አበ ምኔት (አስተዳዳሪ)ለበርካታ ዓመታት ደከመኝ ...
21/06/2025

በአስቸኳይ ይፈቱ፣

#አባታችን ሊቀ ብርሃናት የኔታ ይባቤ በላይ ለምን ታሠሩ?
የቅኔ፣የ፹፩መጻሕፍት፣የአቡሻኽር፣የጥበባት መምህሩ፣ የናዳ ገዳም አበ ምኔት (አስተዳዳሪ)

ለበርካታ ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ወንበር ዘርግተው ደቀ መዛሙርት አብዝተው ሲያስተምሩ የኖሩ እያስተማሩ ያሉ ናቸው።

እንደ አባትነታቸው ትጉኅ አበ ምኔት ናቸው መቆፈሪያ ይዘው ዕርፍ አርቀው ሞፈር ጠርቀው አርሰው ቀፍረው ትሩፋት ሠርተው ገዳም ገድመው የኖሩ የሚኖሩ አባት ናቸው።

እንደ ሰባኪ ዙረው የሚያስተምሩ እያስተማሩ ያሉ ሐዋርያ ናቸው።

የኔታ ይባቤ አይደለም መታሠር በወርቅ ወንበር ተቀምጠው ያስተምሩን የሚባሉ ረቂቅ ሊቅ፣ምጡቅ ባለ አእምሮ ናቸው።

ለየኔታ ይባቤ በላይ የማይሆን ፍትህ ምን አይነት ነው?

መምህራችንን አባታችንን ፍቱልን።
እኔም የየኔታ ይባቤ በላይ ልጅ ነኝ።
እሥራታቸው እሥራቴ፣መከራቸው መከራየ ነው።

አድባር የሆኑትን ትልቅ ሰው ማሠር ትልቅ ስህተት ነው።

ለሀገር ባበረከቱት፣የወንጌል፣የሰላም፣የልማት፣የቅኔ፣የሀገር በቀል ዕውቀት፣የአቡሻህር፣የአርአያነት አስተዋጽኦ ሽልማታቸው እሥራት እና እንግልት ሊሆን አይገባም።

ሊቁ አባታችንን ሲሸለሙ እንጂ ሲታሠሩ መስማት ትልቅ ዕዳ ነው።

ከገዳማቸው ሂዶ በየኔታ ይባቤ ተመክሮ ያልተጽናና፣ተገሥፆ ያልተረጋጋ፣ከመስቀላቸው ተባርኮ ከጸበሉ ተጠምቆ ዕረፍተ ህሊና ያላገኘ ሰው የለም ማለት ይቻላል።

የኔታ ያለ ውግንና የሁሉም መምህር፣የሁሉም አባት፣የሁሉም ዘር ቀለም ሳይለዩ አስተማሪ፣የሁሉም ፊት ደረት ሳይለዩ ገሥፆ መካሪ ናቸው።

እንዲህ ያሉትን የኔታችንን አባታችንን በክብር ወደ ገዳማቸውና ወደ ማስተማሪያ ወንበራቸው መልሱልን።

"ቢያድጥ ቢያድጥ ወደላይ ያድጣል?"

©Elite EOTC Nation

ሰበር መረጃ፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተች።Elite EOTC Nation
17/06/2025

ሰበር መረጃ፣

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተች።

Elite EOTC Nation

በአለም አቀፍ ደረጃ  የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞችን በአንድ የመሰባሰቢያና Platform ውስጥ እንዲሰባሰቡ የሚያደርግ ፕሮጀክት የተጀመረ መሆኑን ለመግለፅ እን...
03/06/2025

በአለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞችን በአንድ የመሰባሰቢያና Platform ውስጥ እንዲሰባሰቡ የሚያደርግ ፕሮጀክት የተጀመረ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

አፋጣኝ ምላሽ ስለሚያስፈለግ ኦርቶዶክሳውያን ለጓደኞቻችሁ አድርሱ።

https://t.me/eliteeotcnation
https://t.me/eliteeotcnation
https://t.me/eliteeotcnation

የመሰባሰቢያችን ዋና ዓላማ:-

✅በዋናነት የቤተክርስቲያናችንን ትምህርት፣ ባህል፣ ትውፊት እና ዶግማ በመላው ዓለም ማስፋፋት ሲሆን በሀገር ውስጥ የሚካሄዱ ህገወጥ ፣ ቤተክርስቲያን የማይወክሉ እንቅስቃሴዎችን ማስተካከል እና መግታት፣

✅ በቤተክርስቲያናችን ላይ በየጊዜው የሚነሱ የውሸት ማዕበሎችን ለምዕመናኑ ግንዛቤ እንዲያገኝ በማድረግ መግታት እና ትክክለኛ አስተምሮውን ማስተላለፍ፣

✅ ትክክለኛ አባቶችን ከቆብ ከለበሱ ተኩላ እና ፖለቲከኛ አባቶች በመለየት ለህዝቡ ትክክለኛ መረጃን በማቀበል የራሱን አቋም እንዲወስድ ማድረግ፣ እንዲሁም ቤተክርስቲያን እንዳይጎዱ መከላከል።

✅ የፈረሱ፣ የታቃጠሉ እና የሚታደሱ ቤተክርስቲያንን በእውቀት፣ በገንዘብ እና በሀሳብ መርዳት።

✅ ምዕመኑ ዘመኑን ዋጅቶ ቤተክርስቲያኑን ከነጣቂ ተኩላዎች እንዲጠብቅ፣

✅ጳጳስ መስለው በቤተክርስቲያን ውስጥ የገቡ በርካታ ፖለቲከኞች እንዳሉ በማስገንዘብ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማድረግ፣ አስፈላጊ ከሆነም በስም እና በመረጃ በማጋለጥ ቤተክርስቲያንን ማዳን፣

✅ንዋይ የሚወዱ የቤተክርስቲያን ሰዎችን ወደ ትክክለኛው ስርዓት እንዲመጡ ካልሆነ ግን ለአማኙ ማህበረሰብ አስፈላጊውን መረጃ በመስጠት ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ማድረግ፣

✅በቤተክርስቲያን ላይ የሚደረጉ ስርቆቶችን በረቀቀ መንገድ በመከታተል ማጋለጥ እና የእርምት እርምጃ መውሰድ፣

✅በቤተክርስቲያናችን ላይ በተጠና መልኩ የተሳሳተ አስተምሮ የሚሰጡ ሀሳዊ መምህራንን እንዲሁም ኢአማንያን በመከታተል አስፈላጊውን የመልስ ትምህርት መስጠት።

✅ በቤተክርስቲያን ላይ ፀያፍ የጥላቻ ንግግር፣ የሚያደርጉ ግለሰቦችን መገሰፅ የማይመለሱ ከሆነ ለህግ ማቅረብ፣ ህግ የማይቀጣቸው ከሆነ አስፈላጊ የሚባለውን እርምጃ መውሰድ።

✅ሌሎች የእምነት ተቋማት የኢኦተቤክቷን አክብረው እና ተከባብረው እንዲኖሩ የሚያስተሳስር አስተምሮን መስጠት፣

✅የመንግስት ባለስልጣናት በቤተክርስቲያናችን ላይ የሚያደርጉት የረቀቀ ሴራ በማጋለጥ ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲያገኝ ማድረግ፣

✅ መንግስት የዘረጋው የትምህርት ስርዓት ፀረ ኦርቶዶክሳዊ ወይም ኦርቶዶክሳዊ አስተሳሰብን የማይወክል በመሆኑ በተደራጀ መልኩ ምክረሃሳቦችን የያዘ ፕሮፖዛል በማዘጋጀት በማቅረብ የሚመለከተው አካል የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ማድረግ፣

✅ ቤተክርስቲያን በምትገኝበት ቦታ ሁሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲስፋፉ፣ የአብነት ተምህርት ቤቶች እንዲገነቡ፣ማድረግ፣

ሲሆን ሌሎች በዚህ ላይ ያልተጠቀሱ አጀንዳዎች የሚኖሩ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

ስለሆነም በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን ከላይ የተጠቀሱት ፕሮጀክቶቻችን ከግብ የምናደርሳቸው በጋራ ሆነን በመሆኑ በታሪክ አጋጣሚ አሁን ላይ ቤተክርስቲያን እየደረሰባት ያለውን ግፋ እና እንግልት እንዲሁም መርጦ ግድያ እያንዳንዳችን ሊያሳስበን የሚገባ በመሆኑ የበኩላችንን ስራ እንድንሰራ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃችኋለን።

በእቅዳችን መሰረት የመጀመሪያው ስራችን ቻናሉን 10,0000 ኦርቶዶክሳውያን አንዲቀላቀሉ ማድረግ ነው።

ሁለተኛው እቅድ በመላው ዓለም ያሉ እና እኛ በምንደርስባቸው አካባቢዎች ተወካዮችን መሰየም፣

እነዚህን ሁለት ስራዎች እስከ ሰኔ 30 ድረስ ማጠናቀቅ ይጠበቅብናል።

እግዚአብሔር ይርዳን!!!!

በዚህ ሊንክ መመዝገብ ይችላሉ👇👇👇
https://t.me/eliteeotcnation
https://t.me/eliteeotcnation
https://t.me/eliteeotcnation
https://t.me/eliteeotcnation

02/06/2025

እንኳን ወደ የላቁ እና የተመራመሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ማህበረሰብ መገኛ ፔጅ በደህና መጣችሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ እና ብንኖር ኦርቶዶክሳውያንን በአንድ ቋት ውስጥ አስገብተን ወንጌል እንዲማሩ እና ለቤተክርስቲያናችን ዘብ እንዲቆሙ ይደረጋል፡፡ያቆየን!!

Address

London
WC1A1AA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Global Orthodox Forum posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share