Bench Sheko Tv

Bench Sheko Tv ይህ የቤንች-ሸኮ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው።
መልካም ዕሴትን እንገነባለን!

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላሚዛን- አማን ፣ ግንቦት 22፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦...
30/05/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ሚዛን- አማን ፣ ግንቦት 22፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦
የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል እያደረገ ያለውን ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል አሉ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ በሰው ኃይል፣ በትጥቅና በቴክኖሎጂ ያደረገውን ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ለፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማብራሪያ ሰጥቷል።

በዚሁ ወቅት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ለምርጫው ያደረገው ዝግጅት እጅግ ጠንካራ መሆኑን ተናግረዋል።

ምርጫውን ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች የተለያዩ ሙከራዎችን እያደረጉ ቢሆንም መከላከያ ሠራዊት ከሌሎች የፀጥታና ደኅንነት ኃይሎች ጋር እነዚህን የጥፋት ዕቅዶች ማክሸፉን አረጋግጠዋል።

አክለውም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅና በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው÷ የጋራ ግብረ ኃይሉ ከምርጫ ቦርድ ጋር መረጃዎችን በመለዋወጥና ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እየሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም በቅድመ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሂደት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች እና የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ደህንነት በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን አንስተዋል።

ቀሪውን የምርጫ ሒደት ሰላማዊነት ለማረጋገጥ አስፈላጊ የሆነ ሎጂስቲክስና ትጥቅ መሟላቱን እንዲሁም ለተልዕኮው የሚመጥን በቂ ስልጠናና ኦሪንቴሽን የወሰደ የሰው ኃይል በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል መሰማራቱን ገልጸዋል።

በቀጣይ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ በቴክኖሎጂ የታገዘ የፀጥታና ደህንነት የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስገነዘቡት፡፡

ከምርጫው በኋላ የሚከናወኑ ሒደቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ ግብረ ኃይሉ ሙሉ ዝግጅት ማድረጉንም ኮሚሽነር ጀነራሉ አረጋግጠዋል።

ኤፍ ኤም ሲ


‎በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተሉ
‎📌Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61580291218857
‎📌Tiktok https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
‎📌Telegram https://t.me/benchshekotelevision
‎📌 youtubehttps://www.youtube.com/-Mizan-Aman


ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ የፈረንሳዩ እግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አንስቷል፡፡ፒኤስጂ ከአስቸጋሪ አጀማ...
30/05/2026

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ

የፈረንሳዩ እግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አንስቷል፡፡

ፒኤስጂ ከአስቸጋሪ አጀማመር በኋላ አርሰናልን …. በሆነ ውጤት በመርታት ነው ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካት የቻለው፡፡

ጨዋታው በጀመረ በ6ኛው ደቂቃ ካይ ሃቨርትዝ ለአርሰናል የመሪነቷን ግብ አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ በአርሰናል 1 ለ 0 መሪነት ተጠናቅቋል፡፡

ይሁን እንጂበሁለተኛው አጋማሽ ፒኤስጂ በ65ኛው ደቂቃ በኡስማን ዴምቤሌ የፍጹም ቅጣት ምት ግብ አቻ ሆኗል።

መደበኛ የጨዋታ ጊዜው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎም ጨዋታው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ያመራ ሲሆን፥ በዚህም ሳይሸናነፉ ቀርተዋል።

በመጨረሻም የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ አሸናፊን ለመለየት በተሰጠ የመለያ ምት ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ ማንሳት ችሏል።
ኤፍ ኤም ሲ

አርሰናል 1 - 0 ፒኤስጂ የመጀመሪያ አጋማሽ...አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የመጀመሪያው አጋማሽ አርሰናል ፒኤስጂን 1 ለ 0 ...
30/05/2026

አርሰናል 1 - 0 ፒኤስጂ የመጀመሪያ አጋማሽ...

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የመጀመሪያው አጋማሽ አርሰናል ፒኤስጂን 1 ለ 0 እየመራ አጠናቅቋል።

የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት ያደረገው ዝግጅት (በምሥል)
30/05/2026

የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት ያደረገው ዝግጅት (በምሥል)

በመገናኛ ብዙሃን የተደረገው የተወዳዳሪ ፓርቲዎች  ቅስቀሳ ማንን መምረጥ እንዳለብን በቂ ግንዛቤ አስጨብጦን  የድምፅ መስጫውን  ቀን በጉጉት እንድንጠብቅ አድርጎናል  -የሚዛን አማን ከተማ ነ...
30/05/2026

በመገናኛ ብዙሃን የተደረገው የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ቅስቀሳ ማንን መምረጥ እንዳለብን በቂ ግንዛቤ አስጨብጦን የድምፅ መስጫውን ቀን በጉጉት እንድንጠብቅ አድርጎናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች።

‎ሚዛን -አማን ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (ቤ.ሸ.ቴ)

‎ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ተኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅሰቀሳ ሲያደርጉ ቆይቷል።

‎ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን ሲያካሂዷቸው የነበረውን የምርጫ ቅሰቀሳ ክርክር ሲከታተሉ እንደነበር የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል።

‎የተፎካካሪ ፖለቲካ ፖርቲዎች ያደረጓቸው የነበረው ክርክሮች ማንን መምረጥ እንዳለብን በቂ እወቀት እንዲኖረን አድርጓል ሲሉም ተናግረዋል።

‎የተፎካካሪ ፓርቲዎች ያደረጓቸው የምረጡን ቅስቀሳና ክርክሮች የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ቀኑን በጉጉት እንድንብቅ አድርጎናል ሲሉ ጨምረው ገልፀዋል።

‎ብዙአየሁ አሣሣኸ



‎በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተሉ
‎📌Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61580291218857
‎📌Tiktok https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
‎📌Telegram https://t.me/benchshekotelevision
‎📌 youtubehttps://www.youtube.com/-Mizan-Aman


ግንቦት 24 ለሚካሄደው ምርጫ፤ የምርጫ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ ደርሶናል- በሚዛን-አማን ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች።ሚዛን አማን ፦ ግንቦት 22/2018ዓ.ም (ቤ.ሸ....
30/05/2026

ግንቦት 24 ለሚካሄደው ምርጫ፤ የምርጫ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ ደርሶናል- በሚዛን-አማን ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች።

ሚዛን አማን ፦ ግንቦት 22/2018ዓ.ም (ቤ.ሸ.ቴ)

በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ አስፈላጊ የሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን እንደወሰዱ ገልፀዋል።

የተረከቡትን የምርጫ ቁሳቁስ በየጣቢያቸው የደረሰ መሆኑን አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅቶች ከወዲሁ እየተከናወኑ እንደሚገኝ ሀላፊዎቹ ጨምረው ገልፀዋል።

በሚዛን ተፈሪ የምርጫ ክልል 139 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኝ እና ለሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁሶች መሠራጨታቸውን ከሚዛን ተፈሪ የምርጫ ክልል ጽ/ቤት ሀላፊ ከሆኑት ከአቶ ይማም እሸቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ብዙአየሁ አሣሣኸኝ

በተመሳሳይም በሚዛን ከተማ ዙሪያ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ተሟልቶ መግባቱም ታውቋል።

አቶ ዓለሙ አዶ የቀጠና 01 ጋቸብ ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪ ሲሆኑ ለምርጫ ማስፈጸሚያ የተላኩ ቁሳቁሶችን መረከባቸውን ገልጸዋል።

ብዙአየሁ አሳሳኸኝ

በካርዳችን የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎችሚዛን- አማን ፣ ግንቦት 22፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦ በምርጫው ቀን ማልደው በመነሳት የሚበጃቸውን ፓርቲ በ...
30/05/2026

በካርዳችን የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች

ሚዛን- አማን ፣ ግንቦት 22፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦ በምርጫው ቀን ማልደው በመነሳት የሚበጃቸውን ፓርቲ በካርዳቸው ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች በአምስት ዓመት አንዴ የሚገኘውን የመምረጥ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ሕገ መንግስታዊና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል።

ለዚህም የወሰዱትን የመራጭነት ካርድ በምርጫው እለት ድምጻቸውን በመስጠት እንደሚጠቀሙበት አረጋግጠዋል።

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ቀኒቶ ገብረማርያም እና ወይዘሮ ብሩክታዊት በቀለ እንደገለጹት፤ ምርጫ በአንድ ሀገር የዴሞክራሲያዊ ሥርአት ከሚጎለብትባቸው መንገዶች አንዱና ዋነኛው ነው።

በመሆኑም ይህን ዕድል ለመጠቀም የድምጽ መስጫውን እለት እየጠበቅን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በምርጫው እለት ለሀገርና ለህዝብ በተሻለ ይሰራል ብለን ላሰብነው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻችንን እንሰጣለን ያሉት ደግሞ አቶ ከተማ ትሌንቲ እና አሰፋ አርቧብ ናቸው።

ወጣት አይተነው ታፈሰም የምርጫ ካርድ የወሰድኩት ለመምረጥ ስለሆነ ካርዴን ሳላባክን ድምጼን በመስጠት ሕገ መንግስታዊ መብቴን እጠቀማለሁ ብሏል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መርሀግብር መሰረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፊታችን ሰኞ ግንቦት 24/2018ዓም ይካሄዳል።

በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የምርጫ ካርድ ያወጡ መራጮችም ይሆነኛል፤ የተሻለ ሀሳብ አለው ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት ቀኑን በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ENA


‎በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተሉ
‎📌Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61580291218857
‎📌Tiktok https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
‎📌Telegram https://t.me/benchshekotelevision
‎📌 youtubehttps://www.youtube.com/-Mizan-Aman


30/05/2026

ድንቅ ምድር ፣ውብ ተፈጥሮ ፣ የአካባቢው የቱሪዝም መዳረሻ ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ኦጀምታ ፍልውሃ
ካሜራ ግርማ ከበደ

Woynten Vngsubs 22/2018 M.B. sokam 12:00 satn benc' nonam benc' Cako telebzhin yakarasnsuc nu yitsis dabub telebzhin beq...
30/05/2026

Woynten Vngsubs 22/2018 M.B. sokam 12:00 satn benc' nonam benc' Cako telebzhin yakarasnsuc nu yitsis dabub telebzhin beqi nu dabmde

ዛሬ ምሽት ከ12:00_1:00 በደ.ሬ.ቴ.ድ በቤንችኛ ቋንቋ የሚተላለፈውን ዝግጅት ትከታተሉ ዘንድ ጋበዝናችሁ ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ነዉ።
30/05/2026

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ነዉ።

የምርጫ ቁሳቁስ በማሻ ምርጫ ክልል ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዘ ነው ሚዛን አማን ግንቦት 22/2018(ቤሸቴ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ  ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን የማሻ ምርጫ ክልል  ለ7...
30/05/2026

የምርጫ ቁሳቁስ በማሻ ምርጫ ክልል ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዘ ነው

ሚዛን አማን ግንቦት 22/2018(ቤሸቴ)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን የማሻ ምርጫ ክልል ለ7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶችን ወደየ ምርጫ ጣቢያዎች የማድረስ ተግባር እየተናወነ ይገኛል።

የየምርጫ ጣቢያዎች የስራ አስፈጻሚዎችም ቁሳቁሶችን በቦታዉ ተገኝተዉ እያጓጓዙ መሆናቸዉ ተመላክቷል ።

የማሻ ምርጫ ክልል የስራ አስፈጻሚ አካላትም የምርጫ ቁሳቁስ ዝግጁ የሚደረግበትና በአሰራር ስነ ስርዓቱ ዙሪያ ግንዛቤ ሰጥቷል ።

በዚሁ ወቅትም የምርጫ ቁሳቁሶችን አስቀድሞ ወደየ ምርጫ ጣቢያዎች የማድረስ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል ሲል ማሻ ኤፍ ኤም ዘግቧል።

#መልካም እሴትን እንገነባለን #

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተሉ

📌Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61580291218857
‎📌Tiktok https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1...
‎📌Telegram https://t.me/benchshekotelevision
📌 youtube
https://www.youtube.com/-Mizan-Aman

Address

Mizan-Aman, South West
Dwa

Opening Hours

Monday 6am - 6pm
6pm - 6am
Tuesday 6am - 6pm
Wednesday 6pm - 6am
Thursday 6am - 8:01pm
Friday 6am - 8pm
Saturday 6am - 8pm
Sunday 6am - 8pm

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bench Sheko Tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category