Hana Seifu

Hana Seifu Informazioni di contatto, mappa e indicazioni stradali, modulo di contatto, orari di apertura, servizi, valutazioni, foto, video e annunci di Hana Seifu, Sito Web di notizie e media, Via Celine, Rome.
(2)

ሸህ ያህያ ይማም በታጣቂዎች ተገደሉ‼በአማራ ክልል የባቲ ወረዳ ባለውለታ፣ የሃይማኖት አባት እና ታዋቂ የሀገር ሽማግሌ የነበሩት ሸህ ያህያ ይማም በታጣቂዎች በግፍ መገደላቸው ተሰማ።ሸህ ያህያ...
14/07/2026

ሸህ ያህያ ይማም በታጣቂዎች ተገደሉ‼

በአማራ ክልል የባቲ ወረዳ ባለውለታ፣ የሃይማኖት አባት እና ታዋቂ የሀገር ሽማግሌ የነበሩት ሸህ ያህያ ይማም በታጣቂዎች በግፍ መገደላቸው ተሰማ።

ሸህ ያህያ ይማም ማህበረሰቡን በፍቅር፣ በእርቅና በመቻቻል በማገልገል፣ የተጣሉትን በማስታረቅ እና ወጣቶችን በመልካም ስነ-ምግባር በመምራት የሚታወቁ ትልቅ የሰላም አባት ነበሩ።

ይህ በንጹህ የሀገር ባለውለታ ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ በሰብዓዊ ሕሊናም ሆነ በሕግ ፈጽሞ የማይቀበል ወንጀል በመሆኑ በፅኑ ተወግዟል።ለቤተሰቦቻቸው፣ መጽናናትን እንመኛለሁ።

ነገ እሁድ ዝግ መንገዶች! #እንድታውቁትከለሊት 11:30 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።ነገ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስተባባሪነት የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላ...
12/07/2026

ነገ እሁድ ዝግ መንገዶች!

#እንድታውቁት

ከለሊት 11:30 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።

ነገ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስተባባሪነት የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ይደረጋል።

ውድድሩ መነሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ ለገሀር፣ ሜክሲኮ አደባባይ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ብሔራዊ ቴአትር፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ ንግድ ባንክ፣ ጋንዲ ሆስፒታል ፣ ጊዮን ሆቴል በማድረግ መስቀል አደባባይ ፍጻሜውን ያነኛል።

ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ፦

- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ)
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
- ከAU መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ)
- ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት)
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን መታጠፊያ)
- ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ)
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ)
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ)
- ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ)
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ ላይ)
- ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ)
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ)
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ)
- ከAU መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ)
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
- ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
- ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
- ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
- ከአገር አስተዳደር መብራት ወደ ብሔራዊ ቲያትር (አገር አስተዳደር መብራት)
- ከንግድ ማተሚያ ወደ ኦርማ ጋራዥ (ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ) ... እሁድ ከለሊቱ 11:30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ፕሮግራሙ ፍፃሜ ድረስ እንደሚዘጋ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳውቋል።

በተገለፁት መስመሮች ላይ መኪና ለአጭርም ይሁን ለረጅም ጊዜ ማቆም ተከልክሏል።

ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ/ም

08/07/2026

በአዲስ አበባ የምትኖሩ ተከራዮችና አከራዮች ሁላችሁም ይህንን ሰበር መረጃ በአስቸኳይ ስሙ! የቤት ኪራይ ጭማሪው ጣሪያ በይፋ ተወስኗል።

የቀድሞዋ  ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል...
25/06/2026

የቀድሞዋ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼

የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል። በቀጠናው ባላቸው ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ልምድ የተመረጡት ሳህለወርቅ፣ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ ለማካሄድ ኃላፊነታቸውን በዚህኛው ወር (ጁን) ማብቂያ ላይ በይፋ ይረከባሉ ተብሏል።

አፈሳው ደርግን ያስንቃል-ጄኔራሉ‼️«በትግራይ የወጣው አዋጅ አንድ መንግስት ወደ ፋሽሽትነት ካልተቀየረ በቀር አያወጣውም»‼️👉“የነ ደብረፅዮን ቡድን በትግራይ ክልል እየተከተሉት ያሉት ስልት ...
24/06/2026

አፈሳው ደርግን ያስንቃል-ጄኔራሉ‼️
«በትግራይ የወጣው አዋጅ አንድ መንግስት ወደ ፋሽሽትነት ካልተቀየረ በቀር አያወጣውም»‼️
👉“የነ ደብረፅዮን ቡድን በትግራይ ክልል እየተከተሉት ያሉት ስልት ሻዕብያ እና ደርግን የሚያስንቅ አፈና ነው‼️”-ጀነራል ገ/ፃድቃን
«አንዲት ላም የወለደችው ጥጃዋ ድንገት ሲሞት ነገር ግን ወተቷን ማለብ ስትፈልግ የሟችዋ ጥጃ ቆዳ ገለባ ሞልተህ ለእናቲቱ ታሳያታለህ። ይህ የምታደርገው ለሟ ወተት እንድትሰጥህ ነው። ከዚያ በኃላ ታልባታለህ። 'ዓርሲ' ይባላል፤ ሁሉም ሰው ያውቀዋል። በትግራይም እየሆነ ያለው ተመሳሳይ ነው። የፖለቲካና የወታደራዊ መሪዎች፣ በወታደራዊ መሪዎች ጫና የቀድሞዋ ህወሓት ለህዝቡ ያሳዩትና ህዝቡን ይበዘብዙታል፣ ትግራይም ያልቧታል። አልቧታልም። ስንት ወንጀል ፈጽመዋል። በወንጀላቸው መቀጠልና መጠየቅም ይፈራሉ»

ጋዜጠኛ «ይህን በማድረግ በስልጣን መቀጠል ይችላሉ?»
«ደርግ እንዳልቀጠለ ሁሉ እነዚህም አይቀጥሉም»

‹‹በ4 አቅጣጫ የከበበንን ጠላት ብቻውን አስቀርተንዋል›› ጀነራል ጆን መዲድየሕወሓት ጀነራሎች እና ወታደራዊ መኮንኖች የሚያሰሙት ዛቻ እና ፉክራ ቀጥሏል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት ድቤ ድለ...
24/06/2026

‹‹በ4 አቅጣጫ የከበበንን ጠላት ብቻውን አስቀርተንዋል›› ጀነራል ጆን መዲድ

የሕወሓት ጀነራሎች እና ወታደራዊ መኮንኖች የሚያሰሙት ዛቻ እና ፉክራ ቀጥሏል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት ድቤ ድለቃቸው ጆሮውን ቢነፍጋቸውም በግድ በጦር ሜዳ ሊማግዱት በየአደባባዩ የ‹እናሸንፋለን› ፉከራ እያሰሙ ነው፡፡

ከትግራይ ጦር አዛዦች መሀል አንዱ የሆኑት ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) በዎይን ሚዲያ በኩል የተለመደ ክስ እና የእናሸንፋለን ፉከራ አሰምቷል፡፡ ጀነራሉ፣ ‹‹በአራት አቅጣጫ የከበበንን ጠላት አሰላለፍ በጣጥሰን፣ ብልጽግናን ብቻውን አስቀርተንዋል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ትናንት ተባብረው የዘመቱብንን ኃይሎችን በታትንን፣ በቀጠናው አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት የጦር አዛዡ፤ አልተቋጨም ያሉትን ህልውና ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል፡፡“ጠላቶቻችን ብዙ ነገር እያሰቡ ነው፤ ብዙ ነገር ደግሞ ይፈርስባቸዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡

ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ አዲስ የኃይል አሰላለፍ እንዲፈጠር አድርገናል የሚሉት ጀነራሉ፤ ‹‹በ2013 ከጎረቤት ሀገራት እሰከ ሀገር ውስጥ ኃይሎች አስተባብሮ የዘመተብንን ጠላት ብቻውን አስቀርተን፣ የራሳችን አሰላለፍ ፈጥረናል›› ብለዋል፡፡ “በዚያን ጊዜ ተፈጥሮ የነበረውን እኛን የማጥፋት አሰላለፍ በትነን፣ ከሀገር ውስጥ እና በምስራቅ አፍሪካ አዳዲስ የአሰላለፍ ለውጦች መፍጠር ችለናል›› ነው ያሉት። ጆን መዲድ አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት ጽምዶን ነው፡፡ በትግራይ ሴቶች ገላ ላይ የጦር ወንጀል ከፈጸመው የሻብያ ኃይል ጋር አብረው መሰለፋቸውን እንደ ስኬት መጥቀሳቸው አስተዛዛቢ ሆኗል፡፡

ጀነራሉ ይቀጥሉና፣ “ይህ አሰላለፍ የትግራይ ህዝብ ለህልውናው በከፈለው ዋጋ የተፈጠረ አዲስ አሰላለፍ ነው” ሲሉም፣ ከጦርነቱ መቆም በኋላ የተፈጠሩ የጎራ ለውጦችን ባለቤትነት ለህወሓት ሰጥተዋል፡፡

በጦርነቱ “ህልውናችንን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን አካባቢያችን በህልውናችን ላይ የሚፈጥረውን ተፅዕኖና ህልውናችንን ለማጥፋት የሚያደርጉትን መሰባሰብ በስኬት በትነናል” ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ደግሞ ፈጥረነዋል ያሉትን የጠላት አሰላለፍ ለውጦች፣ ተጠቅመው መመከት ላሉት ትግል ትልቅ አቅም ፈጥሮልናል ብለዋል።

22/06/2026

ጦርነቱ ተጀመረ
ህውሀት ጥቃት ከፍቷል

21/06/2026

ምርጫው በድጋሜ ይቆጠራል

19/06/2026

ወገኖቻችን አደጋ ላይ ናቸው

18/06/2026

የህውሀት ጦር ተንቀሳቀሰ

Indirizzo

Via Celine
Rome

Sito Web

Notifiche

Lasciando la tua email puoi essere il primo a sapere quando Hana Seifu pubblica notizie e promozioni. Il tuo indirizzo email non verrà utilizzato per nessun altro scopo e potrai annullare l'iscrizione in qualsiasi momento.

Scelte rapide

Condividi