The Ethiopian

The Ethiopian Sharing original Ethiopian music, and cultural stories for a global community. Join 100K+ fans celebrating our heritage through authentic video content.

Business Inquiries: [email protected] The Ethiopian

Sharing original Ethiopian news, music, and cultural stories for a global community.

ከዓመታት ስቃይና ደም መፋሰስ በኋላ የጋዛ ጦርነት አብቅቷል - ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ  | ከዓመታት ስቃይ እና ደም መፋሰስ በኋላ የጋዛ ጦርነት አብቅቷል ሲሉ የአሜሪካው  ፕሬዝዳንት ዶና...
13/10/2025

ከዓመታት ስቃይና ደም መፋሰስ በኋላ የጋዛ ጦርነት አብቅቷል - ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ

| ከዓመታት ስቃይ እና ደም መፋሰስ በኋላ የጋዛ ጦርነት አብቅቷል ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ፡፡

አሜሪካ፣ ቱርኪዬ፣ ግብፅ እና ኳታር በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ የተፈረመው በግብፅ እየተካሄደ በሚገኘው የሻርም ኤል ሼክ የሰላም ጉባኤ ላይ ነው፡፡

ስምምነቱን የሀገራቱ መሪዎች የፈረሙ ሲሆን፤ ሰነዱ ቀጣዩን የጋዛ አስተዳድር በተመለከተ፣ በቀጠናው ዘላቂ ሰላም ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ እና በመልሶ ግንባታ ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በይፋ ከተፈረመ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ ከዓመታት ስቃይ እና ደም መፋሰስ በኋላ የጋዛ ጦርነት አብቅቷል ብለዋል፡፡
ይህ ለውጥ እንዲመጣ ላደረጉ የአረብ እና የሙስሊም አገራትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አሁን በጋዛ የመልሶ ግንባታ ስራ ተጀምሯል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህ ቀን እንዲመጣ በቀጠናው እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች ሲጥሩ፣ ሲመኙ እና ሲጸልዩ ነበር ብለዋል፡፡

ዛሬ የተፈረመው የጋዛ የተኩስ አቅም ስምምነት ሰነድ ታሪካዊ ነው ሲሉም መግለፃቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
በሰላም ውይይቱ ላይ 20 የሚሆኑ የሀገራት ተወካዮች የተሳተፉ ሲሆን፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ የቱርክ፣ የፍልስጤም፣ ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ኳታርና የሌሎች ሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

Via :- አፎምያ ክበበው

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

የዓለም ባንክ የ  #ኢትዮጵያ ድህነት መጠን በ2025 ዓ.ም. ወደ 43 በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል ገለጸ  | የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ያለውን ድህነት በተመለከተ አዲስ ባወጣው ግምገማ፣ በአው...
13/10/2025

የዓለም ባንክ የ #ኢትዮጵያ ድህነት መጠን በ2025 ዓ.ም. ወደ 43 በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል ገለጸ

| የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ያለውን ድህነት በተመለከተ አዲስ ባወጣው ግምገማ፣ በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ዓ.ም. 33 በመቶ የነበረው የድህነት መጠን፣ በተያዘው 2025 ዓ.ም. ወደ 43 በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል አስታወቀ። ይህም የዓመታት ለውጥን ወደ ኋላ የሚቀለብስ ነው ብሏል።

የዓለም ባንክ እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ድህነትን በመቀነስ ረገድ ጉልህ እድገት ካሳየች በኋላ፣ ባለፉት ጥቂት አመታት የተከሰቱ ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች የኑሮ ደረጃ ላይ ተጽዕኖ አድርገዋል። እነዚህ ተግዳሮቶች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የትግራይ ግጭት፣ ከፍተኛ ድርቅ፣ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት መቀዛቀዝ እና የዋጋ ግሽበት ናቸው ብሏል።

በዚህም ምክንያት፣ የድህነት መጠኑ እ.ኤ.አ. በ2016 ከነበረው 33 በመቶ በ2021 ወደ 39 በመቶ ከፍ ማለቱ ገልጿል። በቀጣይ ዓመታትም የበለጠ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የዓለም ባንክ አስታውቋል።

የዋጋ ግሽበት በከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያደረሰ ሲሆን፣ አብዛኛው የገጠር ቤተሰቦችም ቢሆኑ ውስን በሆነ የገበያ ተሳትፎ ምክንያት ከምግብ ዋጋ ጭማሪ ተጠቃሚ አለመሆናቸውም ተገልጿል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ተማሪዎች በመረጡት ዩኒቨርሲቲ መማር እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ  | በተማሪዎች የማይመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች 'ለሌሎች አገልግሎቶች' ይውላሉ ተብሏልበሚቀጥሉት ዓመታት ተማሪዎች በመ...
13/10/2025

ተማሪዎች በመረጡት ዩኒቨርሲቲ መማር እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

| በተማሪዎች የማይመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች 'ለሌሎች አገልግሎቶች' ይውላሉ ተብሏል

በሚቀጥሉት ዓመታት ተማሪዎች በመረጡት ዩኒቨርሲቲ መማር እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ፡፡ “በተማሪዎች መመረጥ ያልቻሉ ዩኒቨርሲቲዎችም ለሌሎች አገልግሎቶች ሊውሉ ይችላሉ” ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

በተማሪዎች ለማይመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች እንደመንግሥት በቢሊየን የሚቆጠር በጀት መስጠት ተገቢ አይሆንም ያሉት ሚኒስትሩ፤ “እንደ ከዚህ ቀደሙ አንዴ ዩኒቨርሲቲ ተከፍቷልና በዚሁ ይቀጥላል የሚባል አሰራር አይኖርም” ብለዋል።

በመሆኑም ዩኒቨርሲቲዎች ለራሳቸው ሲሉ የመማር ማስተማር ሥርዓታቸው ጥራት ያለው እንዲሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

በአፋር ክልል ባራሕሌ ወረዳ በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ደረሰ  | በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።የወረ...
12/10/2025

በአፋር ክልል ባራሕሌ ወረዳ በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ደረሰ

| በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አሊ ሁሴን በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች መፍረሳቸውን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

በአደጋው እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ማለፉን ገልጸው÷ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ አስረድተዋል።
በመሬት መንቀጥቀጡ 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤቶቻቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና ያለመጠለያ መቅረታቸውን ጠቁመዋል።
ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

Via :- በአሊ ሹምባሕሪ

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ሰንደቅ ዓላማ - የሀገራዊ አንድነት እና ነፃነት መገለጫ ታላቅ የብሔራዊ ኩራት አርማ!    | ሰንደቅ ዓላማ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ የታተመ የሀገራዊ አንድነት እና ነፃነት መገለጫ ታላቅ...
12/10/2025

ሰንደቅ ዓላማ - የሀገራዊ አንድነት እና ነፃነት መገለጫ ታላቅ የብሔራዊ ኩራት አርማ!

| ሰንደቅ ዓላማ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ የታተመ የሀገራዊ አንድነት እና ነፃነት መገለጫ ታላቅ የብሔራዊ ኩራት አርማ ነው።

ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር መንግሥት እና ሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የፖለቲካ ሥልጣን፣ ነፃነት፣ ዕድገት እና ማኅበረሰባዊ ትሥሥር መፍጠሪያ መሣሪያ ነው።
ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪ ቃል ይከበራል።

የአንድነታችን እና የኅብረታችን ማሳያ፣ ጀግኖች አያቶቻችን ወራሪዎችን አሸንፈው ለመላው የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ የሕይዎት መሥዋዕትን ከፍለው ለአዲሱ ትውልድ አስረክበዋል።
ይህንኑ መሠረት በማድረግ ሰንደቅ ዓላማ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ቦታ ተሰጥቶት የሚከበር ታላቅ ሀገራዊ በዓል ነው።

በመሆኑም የሀገራችንን ሰንደቅ ዓላማ ክብር እና ተገቢውን ከፍታ አስጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን እና የግዛት አንድነትን ማስቀጠል፤ ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በማጽናት የሀገራችንን የዕድገት ከፍታ ማረጋገጥ ከአሁኑ ትውልድ የሚጠበቅ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ነው።
የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በተለያየ መልኩ በየዓመቱ እየተከበረ 18 ዓመታትን አስቆጥሯል።

የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀንም በፌዴራል፣ በክልሎች አና በሁለቱም የከተማ አስተዳደር ከተሞች ከሰንደቅ ዓላማ መርሆዎች ጋር ተገናዝቦ እና የኢትጵያን ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራትና ማንሰራራት በሚያረጋግጡ ውይይቶች ታጅቦ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪነት በመላው ሀገሪቱ ይከበራል።

የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል መከበሩ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን እና ሉዓላዊነታችን በማስጠበቅ የኢትጵያን የከፍታ ብሥራት እና ሕዳሴ ለማረጋገጥ ለሀገር ክብር እና ጥቅም ሁሉም ዜጋ የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት በሰንደቅ ዓላማ ፊት ዳግም ቃሉን የሚያድስበት ዕለት ይሆናል።

በፌዴራል የመንግሥት ተቋማት፣ በክልሎች እና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች፣ በመከላከያ ሠራዊት ካምፖች እንዲሁም በኤምባሲዎች እና የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች በተመሳሳይ ሰዓት ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል እና በሰንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ የመፈፀም ሥነ-ሥርዓት እንዲሁም በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

በሰሜን_ወሎ ዞን በቅርቡ በተካሄደው ውጊያ በርካታ ሰዎች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን አለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ  | ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በ  #አማራ ክልል...
11/10/2025

በሰሜን_ወሎ ዞን በቅርቡ በተካሄደው ውጊያ በርካታ ሰዎች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን አለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ

| ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በ #አማራ ክልል፣ በተለይም በሰሜን ወሎ ዞን፣ በመንግሥት ኃይሎችና በአማራ ፋኖ ታጣቂ ቡድን መካከል በተካሄደው ግጭት ሳቢያ በርካታ ሰዎች መሞታቸውንና መቁሰላቸውን አስታወቀ።

ኮሚቴው በመስከረም ወር ላይ “ድንገተኛ ግጭት መባባስ” መከሰቱን ተከትሎ በአካባቢው ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ በእጅጉ ማሽቆልቆሉን ገልጿል። ይህም “የበርካታ ሰዎች ሞት፣ የተዋጊዎች መማረክና ሌሎች ከባድ ሰብዓዊ ችግሮችን” አስከትሏል ብሏል።

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በላሊበላ የቡድን መሪ የሆኑት ማርቲን ታልማን፤ በግጭት ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው የቁልመስክ እና የሙጃ አካባቢዎች መመለሳቸውን ገልጸው፤ “ባለፉት ቅርብ ቀናት ውስጥ በሰሜን ወሎ ዞን ብዙ ሰዎች ተገድለዋል ወይም ቆስለዋል” ብለዋል።

“የአካባቢው የጤና ሠራተኞች ውስን በሆኑ መሳሪያዎች ታግዘው የቆሰሉ ተዋጊዎችንና ንጹሐን ዜጎችን አክመዋል። አሥራ ስድስት በጽኑ የቆሰሉ ምርከኞች አስቸኳይ ቀዶ ሕክምና ያስፈልጋቸዋል ከነዚህ ውስጥ አምስቱ ደግሞ ሕይወታቸውን ለማዳን በሰዓታት ውስጥ ህክምና ማግኘት ይኖርባቸዋል” ሲሉም ገልጸዋል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ወደ ጋዛ እየተመለሱ ነው  | የጋዛ ተፈናቃዮች ወደየቀያቸው እየተመለሱ ያሉት የእሥራኤል የመጀመሪያ ዙር የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ነው። የተፈናቃዮች መመ...
10/10/2025

በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ወደ ጋዛ እየተመለሱ ነው

| የጋዛ ተፈናቃዮች ወደየቀያቸው እየተመለሱ ያሉት የእሥራኤል የመጀመሪያ ዙር የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ነው።

የተፈናቃዮች መመለስ ተከትሎ ከ600 በላይ የሚሆኑ ተሽከርካሪዎችም የእርዳታ ቁሳቁስ ጭነው ወደ ጋዛ እያመሩ እንደሆነ ተዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሀማስ በሕይወት ያሉ 20 የእሥራኤል ታጋቾችን በ72 ሰዓታት ውስጥ ይለቃል በሚል እሥራኤል እየተጠባበቀች ትገኛለች።
የተኩስ አቁም ስምምነቱን ተከትሎ ጀርመን 34 ሚሉዮን ዶላር ለጋዛ ስደተኞች መቋቋሚያና መልሶ ግንባታ እርዳታ አድርጋለች።

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት መተግበር መጀመሩን የእስራኤል ጦር አስታወቀ  | የእስራኤል ጦር ከሃማስ ጋር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ከሰሜናዊ እና ከምዕራብ የጋዛ ክፍሎች ...
10/10/2025

የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት መተግበር መጀመሩን የእስራኤል ጦር አስታወቀ

| የእስራኤል ጦር ከሃማስ ጋር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ከሰሜናዊ እና ከምዕራብ የጋዛ ክፍሎች ለቅቆ እየወጣ መሆኑ ተዘግቧል፡፡

የእስራኤል የጸጥታ ሃይሎች ከጋዛ እየወጡ መሆኑን ተከትሎ በርካታ ፍልስጤማውያን ወደ ሰሜናዊ ጋዛ መመለስ ጀምረዋል።
ሃማስ በበኩሉ በቀጣዮቹ 72 ሰዓታት ውስጥ የእስራኤል ታጋቾችን ለማስረከብ ሂደቶችን የጀመረ መሆኑ የታወቀ ሲሆን፤ በዓለም ዓቀፉ የቀይ መስቀል ማኅበር በኩል ታጋቾችን እንደሚያስረክብ ይጠበቃል፡፡

በእስራኤል በኩል ከ1 ሺ 950 በላይ እስረኞችን እንደምትፈታ የታወቀ ሲሆን፤ ከዛሬ ጀምሮ 600 የሚሆኑ ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ መኪኖች ወደ ጋዛ እንደሚገቡ የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡

Via :- ሃብተሚካኤል ክፍሉ

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ ተወሰነ  |  በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ ሆነው ወደ ሀገር እንዲገቡ ተወስኗል አለ...
10/10/2025

በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ ተወሰነ

| በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ ሆነው ወደ ሀገር እንዲገቡ ተወስኗል አለ የገንዘብ ሚኒስቴር፡፡

ሚኒስቴሩ ለፋና ዲጂታል እንዳስታወቀው ÷ ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት መሆኑ ቢታወቅም ለዘመናት የዚህ የተፈጥሮ ሃብት ተጠቃሚ ሳትሆን ቆይታለች፡፡

ይህንን ሁኔታ ለመለወጥ መንግስት ሲያደርግ የቆየው እልህ አስጨራሽ ጥረት ተሳክቶ በቅርቡ በካሉብ አካባቢ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል ኢንዱስትሪ ተመርቆ የተፈጥሮ ጋዝ የማምረት ስራ በይፋ ተጀምሯል።
ይህን ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ቤንዚን እና ናፍታ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን የተፈጥሮ ጋዝ በሚጠቀሙት ተሽከርካሪዎች መተካት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

የተፈጥሮ ጋዝ የሚያመነጨው በካይ አየር እጅግ በጣም ዝቅተኛ የሆነ፣ ለተለያየ የሀይል ምንጭ አገልግሎት ሊውል የሚችል፣ በሀይል አጠቃቀም ረገድ ውጤታማነት እንዳለው የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ የተፈጥሮ ጋዝ በኢትዮጵያ የሚመረት በመሆኑ ለነዳጅ ግዥ የሚወጣውን የውጭ ምንዛሪ ያስቀራል።

በመሆኑ መንግስት የተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀምን ለማበረታታት ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅ፣ የፈሳሽ ጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ሆነው ወደ ሀገር እንዲገቡ መፈቀዱን አስታውቋል፡፡

ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸው እንዲሁም በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና ናፍታ የሚሰሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግም አሳስቧል፡፡

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

“ትክክለኛ መረጃዎችን ማቅረብ የማይችል የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በቦታው ላይ መቀጠል አይችልም” ~  ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ  | ስለመምህራን፣ ተማሪዎች፣ ምሩቃን ያሉበትን ደረጃና ሌሎች አስፈላ...
10/10/2025

“ትክክለኛ መረጃዎችን ማቅረብ የማይችል የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በቦታው ላይ መቀጠል አይችልም” ~ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ

| ስለመምህራን፣ ተማሪዎች፣ ምሩቃን ያሉበትን ደረጃና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን በትክክለል ማቅረብ የማይችል የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በቦታው ላይ መቀጠል እንደማይችል የትምህርት ሚኒስቴር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ገለፁ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት በዛሬው ዕለት ያካሄደ ሲሆን፤ በዚህም የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ ስምምነቱ ከዚህ ቀደም እንደነበሩ ሪፎርሞች በቀላል የሚታይ ሳይሆን ተቆጥሮ የሚመዘን ነው፡፡
ይህ ስምምነት በዋናነት መረጃን መሰረት ያደረገ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዚህም “ካሁን በኋላ ከዩኒቨርሲቲዎች የሚገኝ መረጃ እንዳለፈው ጊዜ በቀላል የሚጣል ባለመሆኑ እያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ እውነትና ትርጉም ያለው መረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል” ብለዋል፡፡

“ይህን መረጃ ማቅረብ የማይችል የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በቦታው ላይ መቀጠል አይችልም” ሲሉም አስጠንቅቀዋል።
“በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ከዩኒቨርሲቲዎች የሚገኘው መረጃ ትክክለኛና የተሟላ ካልሆነ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች ተሸክመን የምንሄድበት ምንም ምክንያት የለንም”ሲሉም ጠቁመዋል፡፡

በዚህም “ስለመምህራን፣ ተማሪዎች፣ ምሩቃን ያሉበትን ደረጃና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን በትክክል ማግኘት ካልቻልን ለእኛ በቂ ምክንያት ሆኖልን አመራሮችን እንቀይራለን” ብለዋል፡፡

Via :- ቃልኪዳን አሳዬ

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ  |  ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኅብረት በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስ...
09/10/2025

ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ

| ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኅብረት በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱን ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ እና የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌየን ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በምግብ ሥርዓት፣ በጤና በመሰረተ ልማት እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ነው፡፡

በስምምነቱ መሰረት ኅብረቱ በኢትዮጵያ ለዘላቂ ልማት፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለመሬት አስተዳደርና ሌሎች ሥራዎች የሚውል 105 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ አድርጓል።
ከስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነቱ አስቀድሞ ፕሬዚዳንት ታዬ እና ኡርሱላ ቮን ደር ሌየን በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ በዚህ ወቅት ፥ የአውሮፓ ኅብረት "ግሎባል ጌትዌይ" መርሐ ግብር በኢትዮጵያ እና በኅብረቱ መካከል የጋራ ስትራቴጂያዊ ራዕይ ለመቅረፅና አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር በትክክለኛው ወቅት ይፋ መደረጉን አንስተዋል፡፡

ስምምነቱ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በማሳደግ በፈረንጆቹ 2016 ለተፈረመው የስትራቴጂያዊ ትብብር ስምምነት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ልዩ ሽልማት ተበረከተለት  | ፖርቹጋላዊው የአምስት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊ ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፖርቹጋል እግርኳስ ፌዴሬሽን ልዩ ሽልማት ተበርክቶለታል። ክርስቲያኖ...
08/10/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ልዩ ሽልማት ተበረከተለት

| ፖርቹጋላዊው የአምስት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊ ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፖርቹጋል እግርኳስ ፌዴሬሽን ልዩ ሽልማት ተበርክቶለታል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፖርቹጋል እግርኳስ ፌዴሬሽን የ " Prestige Award " ( የምንግዜም ምርጡ ተጨዋች ) በመባል የክብር ሽልማት ተሰጥቶታል።
ከሽልማቱ በኋላ አስተያየቱን የሰጠው ሮናልዶ “ ብዙ ሽልማቶች አሉኝ ነገርግን ይሄኛው የተለየ ነው ማለት አለብኝ “ ሲል ተደምጧል።

“ ይሄ የእግርኳስ ህይወቴ የመጨረሻ ሽልማት ከሆነ ብዬ አስብኩ እና ትንሽ ስሜታዊ አደረገኝ “ ሲል ሮናልዶ ተናግሯል።
ሮናልዶ አክሎም “ ለተወሰኑ አመታት መጫወቴን መቀጠል እፈልጋለሁ ነገርግን ለብዙ አመታት አይደለም “ ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

Indirizzo

Turin

Notifiche

Lasciando la tua email puoi essere il primo a sapere quando The Ethiopian pubblica notizie e promozioni. Il tuo indirizzo email non verrà utilizzato per nessun altro scopo e potrai annullare l'iscrizione in qualsiasi momento.

Condividi