The Ethiopian

The Ethiopian Sharing original Ethiopian music, and cultural stories for a global community. Join 100K+ fans celebrating our heritage through authentic video content.

Business Inquiries: [email protected] The Ethiopian

Sharing original Ethiopian news, music, and cultural stories for a global community.

ዜሌንስኪ ሩሲያ ጦርነቱ እንዳያበቃ 'እያወሳሰበች' ነው አሉ  | የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን አለመቀበሏ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገውን ጥረት እያወሳ...
17/08/2025

ዜሌንስኪ ሩሲያ ጦርነቱ እንዳያበቃ 'እያወሳሰበች' ነው አሉ

| የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን አለመቀበሏ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገውን ጥረት እያወሳሰበ ነው አሉ።

ፕሬዚዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ላይ ላይ በለጠፉት ጽሑፍ "ሩሲያ በርካታ የተኩስ አቁም ጥሪዎችን ውድቅ ስታደርግ እና ግድያውን መቼ እንደምታቆም ገና አለመወሰኗን ተመልክተናል።ይህ ሁኔታውን ያወሳስበዋል" ብለዋል።

ዜሌንስኪ ሰኞ ዕለት ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ተጉዘው የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት የሚያገኙ ሲሆን፣ትራምፕ በበኩላቸው የሰላም ስምምነቱን እንዲቀበል እጠይቀዋለሁ ብለዋል።

ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ከተገናኙ በኋላ በዩክሬን ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ የሚለውን ሃሳባቸውን በመተው፣ ዘላቂ የሰላም ስምምነት ለማድረግ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንቱ የአቋም ለውጥ በማድረግ አርብ የተካሄደውን የመሪዎች ስብሰባ ተከትሎ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ "በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ያለውን አሰቃቂ ጦርነት ለማስቆም ምርጡ መንገድ ነው" ብለዋል። የተኩስ አቁም ስምምነትን ብዙ ጊዜ "አይዘልቅም" ሲሉም ተችተዋል።

ከጉባኤው በኋላ ከትራምፕ ጋር በስልክ ውይይት ያደረጉት ዜሌንስኪ እውነተኛና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጥሪ በማቅረብ "ተኩሱ መቆም" እንዲሁም ግድያ ማብቃት አለበት ብለዋል።

ዜሌንስኪ ይህንን ካሉ በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በሰጡት መግለጫ ከሞስኮ ጋር "እውነተኛ ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላም" ለማግኘት አስፈላጊ ያሏቸውን መስፈርቶች አስፍረዋል።

በተጨማሪም "አስተማማኝ የሆነ የደህንነት ዋስትና" እና በክሬምሊን "ከተያዙ ግዛቶች ታፍነዋል" ያሏቸውን ሕጻናት እንዲመለሱ ጠይቀዋል።

የትራምፕ አስተያየት የዩክሬን እና የሩሲያ ጦርነት እንዲቆም ያላቸው አቋም ላይ ሙሉ በሙሉ ለውጥ ማድረጋቸውን የሚያሳይ ሲሆን፣ አርብ ዕለት ፑቲንን ከማግኘታቸው በፊት "በፍጥነት" የተኩስ አቁም እንዲደረግ እንደሚፈልጉ ተናግረው ነበር።

የዩክሬን ዋና ፍላጎት ስለረዥም ጊዜ ስምምነት ከመነጋገር በፊት አፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረስ ሲሆን ትራምፕ ለአውሮፓ መሪዎች ስለ ስብሰባው ዓላማ ሲያስረዱ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እንደሆነ መናገራቸው ተዘግቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፑቲን ዩክሬን የዶኔትስክ ግዛት አካል ከሆነችው ዶንባስ እንድትወጣ የሚጠይቅ የሰላም ስምምነት ለትራምፕ አቅርበው ነበር ተብሏል።

በምላሹም ሩሲያ በዛፖሪዝህዚሂያ እና ኬርሰን ባሉት አካባቢዎች ወታደሮቿ ባሉበት እንዲቆሙ ለማድረግ አማራጭ ሃሳብ አቅርባለች።

ሩሲያ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ 2014 ክሬሚያን ከዩክሬን በሕገ ወጥ መንገድ ከወሰደች ከስምንት ዓመታት በኋላ በአገሪቱ ላይ ሙሉ ወረራ ፈጽማለች።

ከወረራው በኋላም ዶንባስን እና አብዛኛውን ሉሃንስክን እንዲሁም 70 በመቶ የሚሆነውን የዶኔትስክን ግዛት ተቆጣጥራለች።

ከዚህ ቀደም የትኛውም የሰላም ስምምነት "አንዳንድ የግዛቶች መለዋወጥን ያካትታል" ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝደንት ከጉባኤው በኋላ ለዜሌንስኪ ይህንኑ አቋማቸውን አቅርበዋል ተብሏል።

ከቀናት በፊት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ሩሲያ የሉሃንስክ እና የዶኔትስክ ክልሎችን ያቀፈውን ዶንባስን እንድትቆጣጣር እንደማይፈቅዱ ገልፀው፣ ወደፊት ለምትሰነዝራቸው ጥቃቶች እንደ መንደርደሪያ ሊያገለግሉ ይችላሉ ማለታቸው ይታወሳል።

የቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው የአውሮፓ ዲፕሎማቶች ትራምፕ ሰኞ ዕለት ዜሌንስኪን ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር ተወያይተውባቸው ሊሆን የሚችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲስማሙ ግፊት ሊያደርጉ ይችላሉ።

ሲቢኤስ ምንጮችን ጠቅሶ ትራምፕ ከጉባኤው በኋላ ለአውሮፓ መሪዎች በስልክ እንደተናገሩት ፑቲን "አንዳንድ ለውጦችን" እንደሚያደርጉ መናገራቸውን ነገር ግን ምን እንደሆኑ ሳይገልጹ መቅረታቸውን ዘግቧል።

አርብ የተካሄደውን የመሪዎች ጉባኤ ተከትሎ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ትራምፕ ለዩክሬኑ መሪ ምን ዓይነት ምክር እንደሚሰጡ ተጠይቀው "ተስማማ" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም "ሩሲያ በጣም ትልቅ ኃይል አገር ናት እና እነሱ ግን አይደሉም" ብለዋል።

ትራምፕ ቀደም ሲል ፑቲን ጦርነቱን ለማቆም የማይስማማኡ ከሆነ "በጣም ከባድ ቅጣት" እንደሚጠብቃቸው ዝተው ነበር።

ባለፈው ወር ሞስኮ የተኩስ አቁም ላይ እንድትደርስ አለበለዚያ ግን ሁለተኛ ደረጃ ታሪፎችን ጨምሮ ከባድ አዲስ ማዕቀቦች እንደሚጣሉባት በማስጠንቀቅ ቀነ ገደብ አስቀምጠው ነበር።

አርብ የተካሄደውን የመሪዎች ጉባኤ ተከትሎ ሁለቱም ፕሬዚዳንቶች ስለተደረሰው ስምምነት የተገለፀ ነገር የሌለ ሲሆን ትራምፕ ግን ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል።

ቅዳሜ ዕለት ፑቲን ስብሰባውን "በጣም ጠቃሚ" ሲሉ የገለፁት ሲሆን፣ ለትራምፕ "አቋማችንን ማሳወቅ ችለናል" ብለዋል።

የሩሲያው ፕሬዚዳንት "የቀውሱን መነሻ፣ ስለ አጀማመሩ ለማስረዳት ዕድል ነበረን፤ እርሱን ነው ያደረግነው። የመግባባያችን መሰረት መሆን ያለበት እነዚህን ዋነኛ ምክንያቶች ማስወገድ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

አንድ ከፍተኛ የሩሲያ ዲፕሎማት ለቢቢሲ እንደተናገሩት በአላስካ የተካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ጦርነቱን ለማቆም "ለተጨማሪ ጥረቶች በጣም ጠቃሚ እርምጃ ነው።"

በተባበሩት መንግሥታት የሩሲያ የመጀመሪያ ምክትል ቋሚ ተወካይ ዲሚትሪ ፖሊያንስኪ እንዳሉት ሰላምን የሚፈልግ ማንኛውም ሰው "በውጤቱ ሊረካ ይገባል።"

ፑቲን ከዜለንስኪ ጋር ይገናኙ እንደሆነ ግን ያሉት ነገር የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፈረንሳይን እና ጀርመንን ጨምሮ ለዩክሬን ድጋፋቸውን ለማጠናከር ቃል የገቡ እና "የፈቃደኞች ጥምረት" በመባል የሚታወቁት አገራት ዜሌንስኪ ወደ ዋይት ሐውስ ከመሄዳቸው በፊት እሁድ ከሰዓት በስልክ ለመወያየት ቀጠሮ ይዘዋል።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ፣የጀርመኑ ቻንስለር ፍሬድሪክ ሜርዝ እና የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ሌየንን ጨምሮ የአውሮፓ መሪዎች ቡድን "የሚቀጥለው እርምጃ ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪን ያካተተ ተጨማሪ ውይይት መሆን አለበት" ብለዋል።

መሪዎቹ በአውሮፓ ድጋፍ የሦስትዮሽ ጉባኤ እንዲካሄድ "ለመሰራት ዝግጁ" መሆናቸውን ተናግረዋል ።

አክለውም "በሩሲያ ላይ የሚደርሰውን ጫና ለመደገፍ ዝግጁ ነን" ያሉ ሲሆን "ስለ ግዛቶቿ መወሰን የዩክሬን ጉዳይ ነው። ዓለም አቀፍ ድንበሮች በኃይል መለወጥ የለባቸውም" ብለዋል።

የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም ያደረጉትን ጥረት አድንቀው "ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አቀራርቦናል" ብለዋል።

"ለውጥ ቢኖርም ቀጣዩ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዜሌንስኪ ያካተተ ውይይት መሆን አለበት። በዩክሬን የሚኖር ሰላም ያለእርሱ ተሳትፎ ሊወሰን አይችልም" ብለዋል።

Via :- VOA

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

16/08/2025

ድህነት የሚገዛውን ነገር ካሳየሄኝ ~ ገንዘብ መውደዴን አቆማለው
13ሺ ዶላር በፓሊስ ተዘርፌ ~ የ10 ብር ዳቦ መግዛት ቸገረኝ

Like & Share ~> The Ethiopian

ስምምነት እስኪፈጠር ድረስ ስምምነት የለም’: የትራምፕ እና ፑቲን ንግግር  ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ለማስቆም ውጤት አላስገኘም  | በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው በአሜሪካው ፕሬዝ...
16/08/2025

ስምምነት እስኪፈጠር ድረስ ስምምነት የለም’: የትራምፕ እና ፑቲን ንግግር ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ለማስቆም ውጤት አላስገኘም

| በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መካከል የተደረገው የመሪዎች ስብሰባ፣ ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት በዘለቄታም ሆነ ለአፍታ ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ አለመደረሱን ተዘገበ።

ሆኖም እንደ ሮይተርስ ዘገባ፣ ሁለቱም መሪዎች ወደየአገራቸው ከመመለሳቸው በፊት ንግግሩ ፍሬያማ እንደነበር ገልጸዋል።

አርብ ዕለት በአላስካ ውስጥ በተደረገው የሶስት ሰዓታት ስብሰባ ማብቂያ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት አጭር መግለጫ፣ ሁለቱ መሪዎች በግልፅ ባላብራሩት ጉዳዮች ላይ መሻሻል ማሳየታቸውን ተናግረዋል። ይሁንና ምንም አይነት ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፥ ለጋዜጠኞች ጥያቄም ምላሽ አልሰጡም።
በተለምዶ ብዙ ንግግር የሚያደርጉት ትራምፕ በጋዜጠኞች የተሰነዘሩለትን ጥያቄዎች ሳይመልሱ እንዳለፉም ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።
ሆኖም ግን ትራምፕ “ሰላምን ፍለጋ” በሚል ጽሁፍ ፊት ለፊት ቆመው፣ “አንዳንድ መሻሻሎች አሳይተናል” ብለዋል። አክለውም “ስምምነት እስከሚፈጠር ድረስ ስምምነት የለም” ሲሉ ተናግረዋል።

ውይይቱ በአውሮፓ በ80 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ የሞት አደጋን ያስከተለውን የዩክሬን ጦርነት ማስቆም ትራምፕ ከስብሰባው በፊት ካስቀመጧቸው ግቦች አንዱ ቢሆንም፣ ወዲያውኑ ውጤት ያስገኘ አይመስልም።

ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያ እ.አ.አ. ከ2022 ጀምሮ በዩክሬን ላይ ሙሉ ወረራ ከፈጸመች በኋላ በምዕራባውያን መሪዎች ተገልለው የቆዩ በመሆናቸው፣ ከአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጋር ፊት ለፊት መገናኘታቸው ብቻ እንደ ድል ተቆጥሯል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ትራምፕ ከፑቲን ጋር ባይስማሙም በውይይታቸው 'ለውጥ እንደታየ' ተናገሩ   | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በአላስካ ባደረጉት ውይይት ከስምም...
16/08/2025

ትራምፕ ከፑቲን ጋር ባይስማሙም በውይይታቸው 'ለውጥ እንደታየ' ተናገሩ

| የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በአላስካ ባደረጉት ውይይት ከስምምነት ላይ ባይደርሱም "ለውጥ መታየቱን" ገለጹ።

"ስምምነት ላይ እስከሚደረስ ድረስ ስምምነት የለም። እዚያ ላይ አልደረስንም" ብለዋል።

ለሦስት ሰዓታት ሁለቱ መሪዎች ከተወያዩ በኋላ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። ከጋዜጠኞች ጥያቄ ግን አልተቀበሉም።

ፑቲን የዩክሬንን ጦርነት ለመግታት "በጣም እንደሚፈልጉ" ከመግለጽ ባለፈ ዝርዝር መረጃ አልሰጡም።

በውይይቱ ያልተጋበዙት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ "ስምምነት እንዲፈርሙ" ትራምፕ ጠይቀዋል።

ትራምፕ ሰላም በማስፈን ረገድ ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ማሳየት ቢፈልጉም በአላስካው ውይይት ግን እምብዛም ስምምነት ላይ አለመደረሱ ተገልጿል።

ትራምፕና ፑቲን ሁለት ጊዜ የተጨባበጡ ሲሆን ሞቅ ያለ ሰላምታ ሲለዋወጡም ታይተዋል። በትራምፕ ሊሞዚን ወደ ውይይቱ ሥፍራ በጋራ ሲሄዱም ተስተውሏል።

ዩክሬን ግዛቶቿ በሩሲያ እንዲወሰድ የሚያደርግ ስምምነት ላይ በውይይቱ አለመደረሱ በኪየቭ ደስታን ያጫረ ይመስላል።

ትራምፕ በባለቤታቸው ሜላንያ ትራምፕ በእጅ የተጻፈ ደብዳቤ ለፑቲን ሰጥተዋል።

ስሎቬንያ የተወለዱት ቀዳማዊት እመቤቷ በአላስካው ውይይት አልተገኙም።

ደብዳቤው በጦርነቱ ወቅት ልጆች እየታፈኑ መሆኑን እንደሚጠቅስ ተገልጿል።

የዩክሬን መግንሥት የታገቱ ልጆች ቁጥር 19,500 መሆኑን አስታውቋል።

የታገቱ ሕጻናት ሳይመለሱ የሰላም ስምምነት መፈራረም ተገቢ እንደማይሆን በዩክሬን በኩል ይታመናል።

እአአ በ2023 ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ሕጻናትን በሕገ ወጥ መንገድ በማዘዋወር ክስ ፑቲን እና የሕጻናቶች መብቶች ኮሚሽነራቸው ማሪያ ልቮቫ-ቤሎቫ ላይ የእስር ማዘዣ ማውጣቱ ይታወሳል።

በአላስካ ትራምፕና ፑቲን ሲወያዩ የሩሲያ ድሮን በዩክሬን ጥቃት መፈጸሙን ቀጥሏል።

የሩሲያን ግስጋሴ ለመግታት ዩክሬን ወደ ምሥራቃዊ ግዛት ወታደሮች አሰማርታለች።

ዘለንስኪ እንደሚሉት ፑቲን ሰላም ለማውረድ ቁርጠኛ መሆናቸውን የሚጠቁም ማስረጃ የለም።

ፑቲን ከዘለንስኪ ጋር ለመገናኘት ፈቃደኛ አይደሉም። የዩክሬን ትክክለኛ መሪ ዘለንስኪ ናቸው ብለውም አያምኑም።

ዘለንስኪ ፑቲንን እንደማያምኗቸውና "ተስፋቸው አሜሪካ እንደሆነች" ተናግረዋል።

ትራምፕ በአላስካው ውይይት ሩሲያ የተኩስ አቁም እንድታደርግ ጫና ማሳደር ነበር ግባቸው። ሆኖም ግን ፑቲን በዚህ አልተስማሙም።

ትራምፕ ለፑቲን ቀይ ምንጣፍ አንጥፈው በታላቅ አክብሮት ነው የተቀበሏቸው።

ትራምፕ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስዱ ይዝቱ ነበር። ሆኖም ግን የተኩስ አቁም ጥያቄያቸው ከፑቲን አወንታዊ ምላሽ አላኘም።

የሩሲያ ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የሁለቱ መሪዎች ውይይት "እጅግ አመርቂ" ነበር ብለዋል።

ሁለቱ መሪዎች ያደረጉት ውይይት "በጋራ ወደፊት ለመጓዝ" የሚረዳቸው ነው ሲሉም ተደምጠዋል።

ትራምፕ ከፑቲን ጋር ስላደረጉት ውይይት ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የጦር እስረኞች ልውውጥ ሊኖር እንደሚችል ጠቁመዋል።

"50 50 ዕድል ነው ያለው። ማንኛውም ነገር ሊፈጠር ይችላል። ሆኖም ፑቲን ችግሩን መፍታት እንደሚፈልግ አምናለሁ" ብለዋል።

"በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን ዝርዝር ሰጥተውኛል። እናስፈታቸዋለን" ሲሉም ትራምፕ አክለዋል።

እነዚህ እስረኞች በሩሲያ አልያም በዩክሬን ወገን ያሉት ስለመሆናቸው ፕሬዝዳንቱ አልገለጹም።

የዩክሬን ጦርነት ግዛቶችን በማስረከብ የሚገባደድ ይሆናል? በሚል የተጠየቁት ትራምፕ በአብዛኞቹ የውይይት ነጥቦች ከፑቲን ጋር መስማማታቸውን ጠቅሰው "በጣም ጥሩ ውይይት ነው። ወደ ስምምነት እየተቃረብን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ሆኖም ግን ዘለንስኪ ስምምነት መፈረም እንዳለበት ትራምፕ ገልጸዋል። "እምቢ ሊሉ ይችላሉ። ግን ዘለንስኪ ስምምነት መፈረም አለበት" ብለዋል።

ከአውሮፓውያን ደጋፊዎቻቸው ጋር በመሆን ዘለንስኪ ስምምነት እንዲፈርሙ ትራምፕ አሳስበዋል።

በቀጣይ ፑቲን እና ዘለንስኪ የሚገኙበት ውይይት እንደሚካሄድ ትራምፕ ተናግረዋል።

የቀድሞው የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን (ኔቶ) የአሜሪካ አምባሳደር ዳግላስ ሉት ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት በአላስካው ውይይት ትራምፕ "ምንም ያገኙት ነገር የለም"።

"ፑቲን ከዓለም አቀፍ መድረክ ተገልለው ነበር። አሁን ግን ሞቅ ያለ አቀባበል ተደርጎላቸው ከትራምፕ ጋር በውይይቱ ተገኝተዋል። ትራምፕ ግን ከውይይቱ ያገኙት አንዳችም ነገር የለም" ብለዋል።

Via :- BBC

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

ሀሰተኛ የግዢ ደረሰኝ በማዘጋጀትና በማሰራጨት  ከ480 000 000 ብር በላይ  ልያጭበረብሩ የነበሩ አስራ ሁለት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ዋሉ   | መንግስት ሊያጣ የነበረውን ከ480,0...
15/08/2025

ሀሰተኛ የግዢ ደረሰኝ በማዘጋጀትና በማሰራጨት ከ480 000 000 ብር በላይ ልያጭበረብሩ የነበሩ አስራ ሁለት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ዋሉ

| መንግስት ሊያጣ የነበረውን ከ480,000,ዐዐዐ.00 ብር በላይ ማዳን መቻሉንም አስታውቋል።
ሀሰተኛ የግዢ ደረሰኝ ማዘጋጀት፣ ማሰራጨትና መገልገል ወንጀል የተፈፀመው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ልዩ ቦታው ፊስቲቫል ህንፃ ሀያ ሁለት ማዞሪያ አካባቢ እና በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ክልል ልዩ ቦታው አብደላ ህንፃ ልህቀት ህንፃ እንዲሁም ጌጃ ሰፈር በሚገኘው ብሌን ፕላዛ ህንፃ ውስጥ ለንግድ ስራ በሚል ቢሮ ተከራይተው ከ2015 ዓ/ም እስከ 2017 ዓ/ም ባለው ጊዜ ውስጥ ነው።

ተጠርጣሪዎቹ የተለያዩ የጎዳና ተዳዳሪዎችን እና በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ሰዎችን በመመልመልና በገንዘብ በመደለል ግለሰቦቹ ሀሰተኛ ስም ተጠቅመው የቀበሌ መታወቂያ፣ ዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ፣ መንጃ ፈቃድ እና የቁጠባ ሂሳብና የባንክ ደብተር እንዲሁም የውክልና ሰነዶችን አዘጋጅቶ የንግድ ፈቃድ በማውጣት ከተለያዩ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አቅራቢ ድርጅቶች ጋር የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ በማውጣት፣ የእጅ በእጅ የሽያጭ ደረሸኝ በማሳተም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ልደታ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሚል ሀሰተኛ ክብ ማህተም እና በዚሁ መስሪያ ቤት የሚታወቅ የመረጃ ኦፊሰር ስም የያዘ ቲተር በማዘጋጀት ሀሰተኛ ደረሰኞችን ለተለያዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች እያዘጋጁ ሲያሰራጩ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል።

ፖሊስም በተጠርጣሪዎቹ ላይ መረጃን መሠረት ያደረገ ተከታታይነት ያለው ጥናትና የክትትል ስራ በመስራት በወንጀሉ የተሳተፉ አስራ ሁለት ግለሰቦችን ይዞ ምርመራ እያጣራባቸው እንደሚገኝም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ገቢዎችና ሸማቾች ወንጀል ምርመራ ዳይሮክቶሬት ገልጿል።
በተያዙት ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማስፋት ሂደት ላይ ሲገለገሉባቸው የነበረ ኮምፕዩተር፣ ፕሪንተሮች፣ ስካነር፣ ሀርድ ዲስክ፣ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን እና ህገ-ወጥ ክብ ማህተም እንዲሁም ተዘጋጅተው ለግለሰቦች ሊሰራጩ የነበረ ሀሰተኛ የግዢ ደረሰኞች መያዙን የገለፀው ፖሊስ፤ መንግስት ሊያጣ የነበረውን አራት መቶ ሰማንያ ሚሊየን አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አራት ብር የማዳን ስራ መሰራቱን ከምርመራ ዳይሬክቶሬቱ የተገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ ሶስት የምርመራ መዛግብትን በማደራጀት ለሚመለከተው አቃቤ ህግ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

እንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች የሀገርን ምጣኔ ሀብት በእጅጉ የሚጎዳ ሲሆን የንግዱ ማህበረሰብም ህጋዊ መንገድን በመከተል፣ ለሚገዙት እና ለሚሸጡት እቃ ህጋዊ ደረሰኝ አረጋግጦ የመቀበልና የመስጠት ልምድ ሊኖረው ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።

Via :- ኢንስፔክተር እመቤት ኃብታሙ

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

15/08/2025
15/08/2025
የሲኖትራክ ተሸከርካሪ የጥራት ጉድለት ሳይሻሻል ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል -  የጉምሩክ ኮሚሽን  | የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ያለበትን የጥራት እና የቴክኒክ ችግር እስኪያሻሽል ድረስ ...
15/08/2025

የሲኖትራክ ተሸከርካሪ የጥራት ጉድለት ሳይሻሻል ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል - የጉምሩክ ኮሚሽን

| የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ያለበትን የጥራት እና የቴክኒክ ችግር እስኪያሻሽል ድረስ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል።

የጥራት ጉድለቱ በየጊዜው የሰው ሕይወት ብሎም ንብረት እንዲጠፋ ምክንያት በመሆኑ፤ አምራች ድርጅቱ ማሻሻያ እስከሚያደርግ ድረስ ተሸከርካሪው ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መከልከሉን ነው የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ዘሪሁን አሰፋ ለኢቢሲ ዶትስትሪም የተናገሩት።
ክልከላው ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉንም ገልፀዋል።

በዚህም ከተጠቀሰው ዕለት ጀምሮ ምንም ዓይነት የማስገቢያ ፈቃድ እንዳልተሰጠ አረጋግጠዋል።

Via :- በአፎምያ ክበበው

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

የዛሬው የትራምፕ እና ፑቲን ስብሰባ ለምን በጣም አስፈላጊ ነው?  | ብዙ የተነገረለት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ስብሰባ ዛሬ ነው። ስብሰ...
15/08/2025

የዛሬው የትራምፕ እና ፑቲን ስብሰባ ለምን በጣም አስፈላጊ ነው?

| ብዙ የተነገረለት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ስብሰባ ዛሬ ነው። ስብሰባው በዩናይትድ ስቴትስ አላስካ አንኮሬጅ ውስጥ በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 11፡30 ላይ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ነው። ሆኖም ተንታኞች በሁለቱ የዓለም መሪዎች ውይይት የሩሲያ እና ዩክሬን የተኩስ አቁም ስምምነት ይፈረማል የሚለውን ነገር በተመለከተ ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል።

በደህንነት ስጋቶች እና በጊዜ እጥረት ምክንያት የትራምፕ እና ፑቲን ስብሰባ የአሜሪካ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ይካሄዳል። መላው ስብሰባ በሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ የመሪዎች ውይይት ትራምፕ ለሩሲያ የተኩስ አቁም የመጨረሻ ጊዜ ከሰጡ ከሳምንት በኋላ የመጣ ነው።

ትራምፕ ውይይቱ በጥሩ ሁኔታ ከሄደ ብዙም ሳይቆይ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ሶስትዮሽ ስብሰባ ሊኖር እንደሚችል ጠቁመዋል።
ሆኖም ዘለንስኪ ዩክሬን ወደዚህ ንግግር ባለመጋበዟ በንዴት ምላሽ ሰጥተዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ 'ያለእኛ የተደረገ ማንኛውም የሰላም ስምምነት ለፑቲን ድል ማለት ነው' ብለዋል።

የአውሮፓ መሪዎች የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በሞስኮ ላይ ጫና እንዲጨምሩ ለማድረግ እየጣሩ ሲሆን ይህም በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለእነሱ ተቀባይነት ባለው መንገድ እንዲያቆም ለማድረግ ነው። ትራምፕ ሩሲያ ጦርነቱን ለማቆም ካልተስማማች ከባድ መዘዞች እንደሚገጥማት አስቀድመው አስታውቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያ ተንታኞች አሁን ስብሰባውን ለፑቲን ድል ብለውታል። እንደ የዜና ወኪል ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የሩሲያ መንግስት ባለስልጣናት እና ተንታኞች የመሪዎች ጉባኤውን ማስታወቂያ አድንቀዋል።

ከፑቲን ጋር ቅርበት ያላቸው ዲፕሎማት ዩሪ ኡሻኮቭ እንደተናገሩት አላስካ እና የአርክቲክ ክልል የሀገሮቻችንን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚያጣምሩ እና ትላልቅ የጋራ ተጠቃሚነት ያላቸውን ፕሮጀክቶች ለመተግበር እድል ይፈጥራሉ ብለዋል።

በአጠቃላይ፣ የአላስካው ስብሰባ ለሰላም ንግግሮች እድል ሊፈጥር ቢችልም፣ ስብሰባው በዩክሬን ጦርነት የወደፊት እጣ ፈንታ እና በአለም አቀፍ የኃይል ሚዛን ላይ ዘላቂ ተፅእኖ ሊኖረው እንደሚችል ይታመናል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

በአማራ ክልል መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች በኦሮሚያ ክልል ላላቸው መሬት ግብር ካልከፈሉ “ይወረሳል" መባላቸውን ተናገሩ  | ተፈናቃዮቹ "ዱቄት እየለመንን እየኖርን ግብር መክፈል እን...
15/08/2025

በአማራ ክልል መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች በኦሮሚያ ክልል ላላቸው መሬት ግብር ካልከፈሉ “ይወረሳል" መባላቸውን ተናገሩ

| ተፈናቃዮቹ "ዱቄት እየለመንን እየኖርን ግብር መክፈል እንዴት እንችላለን?" ሲሉ ጠይቀዋል

ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ እና ከምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ ተፈናቅለው በአማራ ክልል ጃራ እና ቻይና መጠለያ ጣቢያዎች ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች "ተገደን ጥለነው ለመጣነው መሬት” “ግብር ካልከፈላችሁ ይወረሳል" ተባልን ሲሉ ቅሬታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን ከተማ በሚገኘው ቻይና ካምፕ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃይ፤ ከቀበሌ ኃላፊዎች ተደውሎላቸው የመሬት ግብር የማይከፍሉ ከሆነ “ንብረታቸው እንደሚወረስባቸው እና ወደ መሬት አስተዳደር እንደሚገባ” እንደተነገራቸው ገልጸዋል።
ከምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ተፈናቅለው በጃራ መጠለያ ተጠልለው የሚገኙ ሌላ ተፈናቃይ፤ ምንም እንኳ ኪረሙ በሚኖር የአጎታቸው ልጅ በኩል የመሬት ግብሩ ቢከፈልላቸውም "አሁን ላይ መሬታቸውን ሌላ ሰው ነው እያረሰ መሆኑን" ተናግረዋል።

የኪረሙ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አለባቸው ዋይሳ ለአዲስ ስታንዳርድ በሰጡት መላሽ፤ "መሬት ይወረሳል አልተባለም" ሲሉ አስተባብለዋል። አክለውም "የግብር ክፍያው ከቀዬአቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ተጠልለው ለሚገኙ ሰዎች አልተጠየቀም እንደዛ የሚል አመራር ካለ እናጣራለን" ብለዋል።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

የአሜሪካ ሴናተር ቴድ ክሩዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ  #ሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ ያቀረቡትን ጥሪ የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች አደነቁ  | የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋ...
15/08/2025

የአሜሪካ ሴናተር ቴድ ክሩዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ #ሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ ያቀረቡትን ጥሪ የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች አደነቁ

| የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች የአሜሪካ ሴናተር ቴድ ክሩዝ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ እንደ እውቅና እንዲሰጡ ያቀረቡትን ጥሪ በደስታ ተቀብለዋል። ጥሪውም ለብዙ አስርት አመታት ሲታገሉለት ለነበረው እውቅና ትልቅ ድጋፍ እንደሆነ ገልጸዋል።

የሴኔቱ የአፍሪካ እና ግሎባል ጤና ፖሊሲ ንዑስ ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ በጻፉት ደብዳቤ፣ ሶማሊላንድን “ለአሜሪካ ወሳኝ የደህንነት እና የዲፕሎማሲ አጋር” በማለት ያሞካሹ ሲሆን፣ “እውቅና እንዲሰጣትም” አሳስበዋል።

በደብዳቤያቸው፣ ሶማሊላንድ በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ አቀማመጥ፣ ጠንካራ የጦር ሃይል እና ለፀረ-ሽብርተኝነትና ፀረ-ወንበዴ ዘመቻዎች ያበረከተችውን አስተዋጽኦ ጠቅሰዋል። በተጨማሪም “ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ እና ከመሳሰሉ ተቀናቃኞች ከፍተኛ ጫና ቢደርስባትም” ሶማሊላንድ “ከአሜሪካ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኗን” ገልጸዋል።

የሴናተር ክሩዝ ደብዳቤ የቀረበው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሀመድ አብዲላሂ ኢሮ ወደ አሜሪካ ሊያደርጉት ባቀዱት ጉዞ ዋዜማ ላይ ነው። በዚህ ሳምንት፣ ሚኒስትሩ አብዲራህማን ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንቱ ወደ አሜሪካ በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋዊ ጉዞ ያደርጋሉ።

Via :- AS

Like & Share ~> The Ethiopian

Tiktok:- https://www.tiktok.com/
Instagram :- https://www.instagram.com/theethiopian9
Youtube :- https://www.youtube.com/

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ፎለው (Follow) ያድርጉ :: እናመሰግናለን !!!

Indirizzo

Turin

Notifiche

Lasciando la tua email puoi essere il primo a sapere quando The Ethiopian pubblica notizie e promozioni. Il tuo indirizzo email non verrà utilizzato per nessun altro scopo e potrai annullare l'iscrizione in qualsiasi momento.

Condividi