Burji united

Burji united unity for devlopment the power of positive thinking must be to life.

Burji zone land scape.
09/02/2024

Burji zone land scape.

His honour ATO Dange Hido
07/02/2024

His honour ATO Dange Hido

በቡርጂ ከፍተኛ የማዕድናት ክምችት መኖሩ ተገለፀ። ፣ ጥር 27/2016 ዓ.ም በቡርጂ ዞን ከፍተኛ የማዕድናት ክምችት መኖሩን በቡርጂ ዞን የሶያማ ዙሪያ ወረዳ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ...
06/02/2024

በቡርጂ ከፍተኛ የማዕድናት ክምችት መኖሩ ተገለፀ።

፣ ጥር 27/2016 ዓ.ም በቡርጂ ዞን ከፍተኛ የማዕድናት ክምችት መኖሩን በቡርጂ ዞን የሶያማ ዙሪያ ወረዳ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ግና ገለፁ።

ኃላፊው እንደገለፁት ጽ/ቤቱ በውሃ እና በማዕድን ዘርፍ በትጋት እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው ማዕድናቱን በአለኝታ ደረጃ ተለይቶ በጥናት ያልተረጋገጡ እና መኖሩን በጥናት የተረጋገጡ በማለት በሁለት መልኩ ከፍለው አብራርተዋል።

በዚህም መሠረት በጥናት ተለይተው የተረጋገጡ ግሪን ሳፋየር፣ የድንጋይ ከሰል፣ ስሞክኳርቲዝ እና ቤንቶናይት ሲሆኑ ግሪን ሳፋየር የተባለውን የጌጣጌጥ ማዕድን "ዎደ" ማህበር እና "ሠላም" የተባሉ ቡድኖች ለሙከራ በሦስት ወር ውስጥ በተደረገ የማምረት ሂደት ከ182 ሺህ 6ዐዐ በላይ ብር መሸጡን ገልፀዋል።

የድንጋይ ከሰል በጥናት ከተረጋገጡት ውስጥ አንዱ ሲሆን ጴጥሮስ እና ጓደኞቹ ማህበር 11 ሄክታር ቦታ ላይ የማምረት ፈቃድ ተሰጦቶት ለመሬት ባለይዞታ ክፍያ ፈጽሞ በሂደት ላይ መኖሩን ተናግረዋል።

በገምዮ አካባቢ ጥራትና ከፍተኛ ክምችት ያለው የቤንቶናይት ማዕድን እንዳለና ግዛቸው የሚባል አንድ ባለሀብት በ2014 ዓ.ም የቤንቶናይት ማዕድን የማምረት ፍቃድ አውጥቶ ወደ ሥራ ስላልገባ ፈቃዱ ተሰርዞ ሌላ ፍቃድ የጠየቀ ስለሌለ እየጠበቀ ይገኛል።

ሌላው ደግሞ በአለኝታ ደረጃ ተለይቶ በጥናት ያልተረጋገጡ ማዕድናት የብረት ማዕድን፣ ክርስታይል ኦፓል፣ አጌት፣ ፊልድስፓር፣ ብሉ ሳፋየር እና ኢመርላንድ ሲሆኑ በቡርጂ ሌሎችም ማዕድናት ሊኖሩ የሚችሉ አመላካች ነገሮች መኖራቸውን አብራርተዋል።

ኃላፊው በማብራሪያቸው ላይ በአካባቢው የሚገኙ ማዕድናትን በጥናት ለማረጋገጥ በቂ በጀት እንደሚጠይቅ ጠቁመው የዞኑና የወረዳው መንግሥት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበው በማዕድን ማምረት ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሀብቶች፣ ድርጅትችና ማህበራት ቡርጂ ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

በአጠቃላይ ከጽ/ቤቱ ከአገኘነው መረጃ መገንዘብ የሚቻለው ጽ/ቤቱ ከሚመለከታቸው የክልል እና የፌዴራሉ አካላት ጋር በጥምረት እየሠራ እንደሆነና ቡርጂ ላይ በአለኝታ የተለዩ ማዕድናት ጥልቅ ጥናት ለማድረግ በቂ በጀት ተመድበው በዘመናዊ መሳሪያ ክምችቱን መለየት እንደሚያስፈልግ መገንዘብ ይቻላል።

በዞኑ በአለኝታ ጥናት ከተገኙት በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ያልተጠቀሱ ከፍተኛ የማዕድን ክምችት ዓይነቶች መኖራቸው ስለተጠቆመ ለማዕድን ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል።

01/02/2024
25/01/2024

የ 4 ኪሎዉን መንግስት መደገፍ የሕልዉናችን ጉዳይ ነዉ!

°°° ❝ለዚህም ነዉ የ 4ኪሎዉን መንግስት እስከችግሮቹ ተቀብለን፣ ሕፀፆችን ለማሻሻል፣ ክፍተቶቹን ለማረምና ለመሙላት ፤ ጅምር ስራዎችን ለማገዝ፤ በሀገር ግንባታ ላይ አሻራችንን ለማሳረፍ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የድርሻችንን ለመወጣት መንቀሳቀስ የሚገባን።

የ 4 ኪሎዉን መንግስት በመጠበቃችን የሕልዉና አደጋን ለመግታት፣ ጅምር ስራዎቻችንን ለማጠናቀቅ፣ የተቋም ግንባታችንን ለማፋጠን፣ ሀገራዊ ሚናችንን ለማሻሻል...ብቻ ሳይሆን ማንነታችንን የማይቀበለንን አክራሪ ኀይል ለመመከትም ጭምር መሆኑ እንደሕዝብ መረሳት የሌለበት አጀንዳችን ሊሆን ይገባል።

አሁን ባለዉ ተጨባጭ እንደኀይማኖት የሕልዉናና የማንነት አደጋ ዉስጥ ከሚከተን እክራሪ ኀይል የምንመክተዉ 4ኪሎ ያለዉን መንግስታችን በተጠንቀቅ በመጠበቅ/በመደገፍ••• ነዉ።❞

ሰላም፣ መረጋጋት፣ እድገት፣ ብልጽግና ለሀገራችን ኢትዮጵያ!

11/01/2024

🌍 የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ ሙሉ ፕሮግራሞች

📅 እለተ ቅዳሜ ጥር 04 / 2016 ዓ/ም

05:00 | 🇨🇮 አይቮሪኮስት ከ ጊኒ ቢሳው 🇬🇼

📅 እለተ እሁድ ጥር 05 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇳🇬 ናይጄሪያ ከ ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇬🇶
02:00 | 🇪🇬 ግብፅ ከ ሞዛምቢክ 🇲🇿
05:00 | 🇬🇭 ጋና ከ ኬፕ ቨርዴ 🇨🇻

📅 እለተ ሰኞ ጥር 06 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇸🇳 ሴኔጋል ከ ጋምቢያ 🇬🇲
02:00 | 🇨🇲 ካሜሮን ከ ጊኒ 🇬🇳
05:00 | 🇩🇿 አልጄሪያ ከ አንጎላ 🇦🇴

📅 እለተ ማክሰኞ ጥር 07 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇧🇫 ቡርኪናፋሶ ከ ሞሪታኒያ 🇲🇷
02:00 | 🇹🇳 ቱኒዚያ ከ ናሚቢያ 🇳🇦
05:00 | 🇲🇱 ማሊ ከ ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦

📅 እለተ ረቡዕ ጥር 08 / 2016 ዓ/ም

02:00 | 🇲🇦 ሞሮኮ ከ ታንዛኒያ 🇹🇿
05:00 | 🇨🇩 ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ከ ዛምቢያ 🇿🇲

📅 እለተ ሐሙስ ጥር 09 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇬🇶 ኢኳቶሪያል ጊኒ ከ ጊኒ ቢሳው 🇬🇼
02:00 | 🇨🇮 አይቮሪኮስት ከ ናይጄሪያ 🇳🇬
05:00 | 🇪🇬 ግብፅ ከ ጋና 🇬🇭

📅 እለተ አርብ ጥር 10 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇨🇻 ኬፕ ቨርዴ ከ ሞዛምቢክ 🇲🇿
02:00 | 🇸🇳 ሴኔጋል ከ ካሜሮን 🇨🇲
05:00 | 🇬🇳 ጊኒ ከ ጋምቢያ 🇬🇲

📅 እለተ ቅዳሜ ጥር 11 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇩🇿 አልጄሪያ ከ ቡርኪናፋሶ 🇧🇫
02:00 | 🇲🇷 ሞሪታኒያ ከ አንጎላ 🇦🇴
05:00 | 🇹🇳 ቱኒዚያ ከ ማሊ 🇲🇱

📅 እለተ እሁድ ጥር 12 / 2016 ዓ/ም

11:00 | 🇲🇦 ሞሮኮ ከ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ 🇨🇩
02:00 | 🇿🇲 ዛምቢያ ከ ታንዛኒያ 🇹🇿
05:00 | 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ ከ ናሚቢያ 🇳🇦

📅 እለተ ሰኞ ጥር 13 / 2016 ዓ/ም

02:00 | 🇬🇶 ኢኳቶሪያል ጊኒ ከ አይቮሪኮስት 🇨🇮
02:00 | 🇬🇼 ጊኒ ቢሳው ከ ናይጄሪያ 🇳🇬
05:00 | 🇨🇻 ኬፕ ቨርዴ ከ ግብፅ 🇪🇬
05:00 | 🇲🇿 ሞዛምቢክ ከ ጋና 🇬🇭

📅 እለተ ማክሰኞ ጥር 14 / 2016 ዓ/ም

02:00 | 🇬🇲 ጋምቢያ ከ ካሜሮን 🇨🇲
02:00 | 🇬🇳 ጊኒ ከ ሴኔጋል 🇸🇳
05:00 | 🇦🇴 አንጎላ ከ ቡርኪናፋሶ 🇧🇫
05:00 | 🇲🇷 ሞሪታኒያ ከ አልጄሪያ 🇩🇿

📅 እለተ ረቡዕ ጥር 15 / 2016 ዓ/ም

02:00 | 🇳🇦 ናሚቢያ ከ ማሊ 🇲🇱
02:00 | 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ ከ ቱኒዚያ 🇹🇳
05:00 | 🇹🇿 ታንዛኒያ ከ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ 🇨🇩
05:00 | 🇿🇲 ዛምቢያ ከ ሞሮኮ 🇲🇦

👉 የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ከቅዳሜ ጥር 18 እስከ ማክሰኞ ጥር 21 ይከናወናሉ።

👉 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች አርብ ጥር 24 እና ቅዳሜ ጥር 25 ይከናወናሉ።

👉 የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ረቡዕ ጥር 29 ይከናወናሉ።

👉 የደረጃ ጨዋታ ቅዳሜ የካቲት 2 ይከናወናል

👉 የፍፃሜ ጨዋታ እሁድ የካቲት 3 ተከናውኖ የአፍሪካ ዋንጫ በ2018 ተመልሶ እንከሚመጣ ድረስ አፍሪካዊያንን እየናፈቀ ይቆያል።



ጥንቃቄ አይለየን    አቶ ዐቢይ ክንፈ የተባሉ ግለሰብ ህዳር 8 ቀን 2016 ዓ/ም ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ከተማ ሰዎችን ለማድረስ በኮንትራት ተስማምተው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- B36969 ...
10/01/2024

ጥንቃቄ አይለየን

አቶ ዐቢይ ክንፈ የተባሉ ግለሰብ ህዳር 8 ቀን 2016 ዓ/ም ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ከተማ ሰዎችን ለማድረስ በኮንትራት ተስማምተው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- B36969 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪያቸውን እየነዱ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው እንቁላል ፋብሪካ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ተነስተውነበር የተጓዙት፡፡

አቶ ዐቢይ ከሄዱበት ሳይመለሱ መቅረታቸው ያሳሰባቸው ቤተሰቦቻቸው ጉዳዩን ለአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳታውቃሉ፤ ፖሊስም አቤቱታውን ተቀብሎ ክትትሉን ይጀምራል፡፡

በተመሳሳይ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ/ም አቶ ዲልፈታ ደንሰቦ የተባለ ግለሰብ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-B 21688 አ.አ የሆነ መኪና እያሽከረከረ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሰዎችን ለማድረስ ከሄደበት ሳይመልስ መቅረቱ ለፖሊስ ሪፖርት ይደረጋል፡፡

አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በተመሳሳይ ሁኔታ የሁለቱ ግለሰቦች መሰወርና የተሽከርካሪዎቹ ደብዛ መጥፋት የአሽከርካሪዎቹን ቤተሰቦችና ፖሊስን በእጅጉ አሳስቧል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጉዳዩን የሚከታተሉ የምርመራና የክትትል ቡድን በማደራጀት ወደ ስራ መግባቱን ተከትሎ የአቶ ዐቢይ ክንፈ አስክሬን ሞጆ ከተማ እንዲሁም የአቶ ዲልፈታ ደንሰቦ አስክሬን ከሞጀ ከተማ 17 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ ተጥሎ መገኘቱን ያረጋግጣል፡፡

ሁለቱም ግለሰቦች የተለያየ የሰውነት ክፍላቸው ላይ በስለት ተወግተው መሞታቸው እና ከአካባቢው የተገኙ ልዩ ልዩ ማስረጃዎች እንደሚያመለክቱት ወንጀሉ የተፈፀመው በተመሳሳይ ቡድን ወይም ግለሰብ ነው፡፡

አዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀሉን ፈፃሚዎች ለማወቅና በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትሉን አጠናክሮ በመጠቀል ባከናወነው ተግባር በሁለቱም ወንጀሎች ቀጥተኛ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎችን እና አንድ በመሸሸግ ወንጀል የተጠረጠረ አንድ ግለሰብን መያዝ ተችሏል፡፡

ወንጀል ፈፃሚዎቹ ትራንስፖርት ፈላጊ መስለው በመቅረብ ሁለቱንም አሽከርካሪዎች በስለት በመውጋት እንደገደሏቸው በምርመራ ተረጋግጧል፡፡

ተጠርጣዎቹ አሽከርካሪዎቹን ከገደሉ በኋላ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- B 21688 አዲስ አበባ የሆነውን ተሽከርካሪ ወደ ወላይታ ሶዶ በመውሰድ በአንደኛው ተጠርጣሪ ወላጆች መኖሪያ ግቢ ደብቀው ተገኝቷል፡፡

ወንጀል የተፈፀመበት መኪና በግቢያቸው የተገኘው የተጠርጣሪው ቤተሰቦች ተሽከርካሪው ውስጥ የፈሰሰውን የሟች ደም በማጠብ ማስረጃ እንዳጠፉ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-B 36969 አ.አ የሆነው ተሽከርካሪ ደግሞ ለአንድ ግለሰብ ተሽጦ ፖሊስ ባደረገው ብርቱ ክትትል ወላይታ አካባቢ ሊገኝ ችሏል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ የክትትል ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ ሞጆ ፣ ከሞጆ ሀዋሳ ፣ ከሀዋሳ ሺንሽቾ እየተመላለሱ ከፍተኛ ውጣ ውረድ በማስተናገድ እና ውጤት ላይ ለመድረስ ጎዳና ተዳዳሪ መስለው መረጃ እና ማስረጃ ለማሰባሰብ ለበርካታ ቀናት ጎዳና ላይ በማደር ነበር ተጠርጣዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋል የቻሉት፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ፣ የብሔራዊ መረጃና መረብ ደህንነት ፣ በኦሮሚያ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ፣ በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከንባታ ጠንባሮ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤትና የወላይታ ዞን መምሪያ አመራሮችና አባላት አንዲሁም ለሺንሽቾ ማህበረሰብ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ጥረት ላደረጉት ያላሰለሰ ድጋፍ አዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል።

የግል የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦች ተገቢውን ጥንቃቄ

04/01/2024

የሁለተኛ ድግሪ በምማር ወቅት ከ #ሱማሌላንድ በዩኤን ዲ ፒ ስኮላር ተሰጥቷቸው ኢትዮጵያ መጥተው ይማሩ የነበሩ ጓደኞች ነበሩኝ። ስለ ሀገራቸው ሲናገሩ በጣም በኩራት ነበር "ሱማሌ" ባልኳቸው ቁጥር "ሱማሌላንድ" እንድል ያርሙኛል። "ዓለም እውቅና አለመስጠቱን አትመልከት በምስራቅ አፍሪካ የህዝብ ምርጫን ዲሞክራሲያዊ ብቻ ሳይሆን ዲጂታል አድርገን በመምራት እንታወቃለን" ይሉኛል።

በቅርቡ ኢትዮጵያና እና ሱማሌላንድ የወደብ ስምምነት ማድረጋቸው ተሰምቷል ታዲያ ስምምነት ማድረጓቸውን ተከትሎ የሚጠበቁ ምልልሶች ጀምረዋል (የሱማሌ "ግዛቴን ከመውረር ለይቼ አላየውም"፤ የአውሮፓ ህብረት "የግዛት ልዋላዊነት እንዳይረሳ"፤ የግብፅ "የሱማሌ የግዛት አንድነት እንዲጠበቅ አለሁ" ፤ ወዘተ)።

የኢኮኖሚ ስምምነቶች የጋራ ተጠቃሚነት ከተቻለ ይበልጡን የመጠቀም መርህን የተከተለ ነው። ለምሳሌ፦ ሱማሌላንድ 20ኪ.ሜ ለወደብ የቀረበ የየብስ መሬት ለ50ዓመት መነሻ ኪራይ በመስጠት ከኢትዮጵያ ቀልፍ አጋርነት፤ የሀገርነት እውቅና፤ የመሰረተ ልማት ተጠቃሚነት፤ የመብራት ሃይል አቅርቦት እንዲሁም ከግዙፍ የመንግስት የልማት ተቋማት ድርሻ የማገኘት ድርድር ሊኖራት ይችላል።

ስለዚህ ድርድሩ በመጪው 50 ዓመት የሚመጡ እድሎች እና ስጋቶችን የደመረ የቀነሰ ረዥም እንደሚሆን ግልፅ ነው። ስምምነት በሚደረስባቸው ጉዳዮች በሙሉ ኢትዮጲያም ልታሸንፍ ሱማሌላንድም ልታተርፍ ለቀጣይ 50 ዓመት አቅጣጫ ቀያሪ ውሳኔ ሊያሳልፉ ነው የሚገናኙት።

ወደብ ለኢትዮጵያ ለኢኮኖሚ ወሳኝ ነው። ይበልጥ በቀጣይ ለማደግ ለሚደረግ ፍጥነት ቀላል ድርሻ አይኖረውም። በተመሳሳይ ከእውቅና እስከ የለማ መሰረተ ልማት ተጠቃሚነት ለሱማሌላንድ ግዙፍ በረከት ነው።

ከ1991ጀምሮ የሱማሌላንድ የእውቅና ጥያቄ በዓለም ሀገራት የሚጣጣለው አንድም የሱማሌን መብት ከመግፋት ጋር በማቆራኘት ሲሆን በዋናነት ግን ራስ ገዝ የሆነ ግዛቶችን በቀላሉ የሀገርነት እውቅና በሰጡ ቁጥር ተመሳሳይ እልፍ ተሰነጣጣቂ ሀገራትን ላለመፍጠር ነው።

በኢትዮጵያ እና በሱማሌላንድ መካከል የተደረሰው ስምምነት ማንን ይበልጥ በዘላቂነት ሊጠቅም እንደሚችል ለማወቅ የስምምነቱ (ምን የመስጠት እና ምን የመቀበል) ጭብጥ በደንብ ሲቀርብ ለመወሰን ይቀላል። በመርህ ደረጃ ግን ሁለቱም እጅግ የሚያስፈልጋቸው ጉዳይ ላይ እንደተገጣጠሙ ይሰማኛል።

እንደዚህ አይነት ስምምነት በወደፊቱ በ2070ዎቹ ሳይቀር ሁለቱ ሀገራት ሊኖራቸው የሚችለውን ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ ሳይቀር የሚወስን ነው።

ለሱማሌላንድ የሀገርነት እውቅና ከኢትዮጵያ ሀ ብሎ መጀመር እና በኢትዮጵያ በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ኢኮኖሚያዊ አቅም ከፈጠሩ የልማት ድርጅቶች ድርሻ ማግኘትን ከጨመረ ቀላል ጥምቅ አይኖረውም። ለኢትዮጵያ በተመሳሳይ ለመጪው ጊዜ የጦር መንደር ከማግኘት እስከ ነጠላ ክንፍ የወደብ ጥገኝነት (ጅቡቲ) ላይ ለተንጠለጠለው ኢኮኖሚ ሰፊ አማራጭ ማግኘቱ ቀላል ፋይዳ አይኖረውም።
Economist View

ሰበር ዜና! እንኳን ደስ አለን! አላችሁ! ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች!ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች። ጠቅላይ ሚኒ...
01/01/2024

ሰበር ዜና! እንኳን ደስ አለን! አላችሁ!
ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች!

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የሆነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆን ችላለች።

ኢትዮጵያ የውጪ ብድር ዕዳ መክፈል ያለመቻል አመክንዮ እና ስጋት ምንድን ነው? የተሰጣት የብድር መክፈል ደረጃ ከCC ወደ C የመውረዱ ቀጣይ ጫና ምንድን ነው?የዓለም አቀፉ የዕዳ ጫና ዝርዝር...
29/12/2023

ኢትዮጵያ የውጪ ብድር ዕዳ መክፈል ያለመቻል አመክንዮ እና ስጋት ምንድን ነው? የተሰጣት የብድር መክፈል ደረጃ ከCC ወደ C የመውረዱ ቀጣይ ጫና ምንድን ነው?

የዓለም አቀፉ የዕዳ ጫና ዝርዝር በሚያወጣው ፊች የተሰጣት ደረጃ ከCC ወደ C የመውረዱ ጫና ምንድን ነው?

የዓለም ሀገራት የውጪ ዕዳ የመክፈል አቅም ደረጃ (ከAAA እስከ D) እንዴት ይመደባሉ?

የኢትዮጵያ መንግስት የውጪ ዕዳ ባለመክፈል የሚፈጠርን ጫና ለመቋቋም ምን አይነት ተገማች እርምጃዎች ሊወስድ ይችላል?

በጥልቀት ያለውን ትንታኔ እና መረጃ ከሚከተለው https://youtu.be/OsbhuVpYosw ቪዲዮ ማየት ትችላላችሁ።

የዓለም ሀገራት የዕዳ ክፍያ ሁኔታ ደረጃን እና በየደረጃው ያለውን ትርጓሜ መመልከት ለመትፈልጉ https://t.me/WaseAlpha ላይ pdf አስቀምጫለሁ።

ኢትዮጵያ ተቀምጦ ከአማዞን ዕቃ መግዛት ይቻላል? ዶላር የተጫነበት ኤቲኤም ካርድስ ከየት ይገኛል?-----------------------------------------------------------...
26/12/2023

ኢትዮጵያ ተቀምጦ ከአማዞን ዕቃ መግዛት ይቻላል? ዶላር የተጫነበት ኤቲኤም ካርድስ ከየት ይገኛል?
-------------------------------------------------------------------------------------------------------------
ተማሪዎች ከውጭ የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ጋር የተያያዘ ክፍያ መፈጸም ይፈልጋሉ። ውጭ ዘመድ ከሌላቸው እንዴት ይከፍላሉ?
ባሕር ማዶ ጉዞ ሲታሰብ የሆቴል አደራ (Hotel Reservation) ክፍያ ያስፈልጋል። ክፍያው ያለ ካርድ እንዴት ይፈጸም?
አገር ቤት የበረራ ትኬት ቅርንጫፍ ቢሮ የሌላቸው አየር መንገዶች አሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ በጭራሽ የሚዳሰስ ቢሮም የላቸውም። ትኬት የሚሸጡት በበይነ መረብ ነው። ከጥሬ ገንዘብ ክፍያ ጋር ፍቺ ከፈጸሙ ቆይተዋል። ኢትዮጵያ ያለ ዜጋ እንዴት ይክፈል?
የተመሰከረለት የሒሳብ አዋቂ ለመሆን የትምህርትና የፈተና ክፍያ በበይነ መረብ ነው የሚካሄደው። የባንክ ሠራተኞች ሳይቀሩ በዚህ ይቸገራሉ።
የውጭ ምንዛሬ እጥረት በሚያንገላታት ኢትዮጵያ ብዙ ሰዎች ከአገር ሲወጡ ራስ ምታት የሚሆንባቸው የዶላር ጉዳይ ነው።
በተለምዶ ክቡ ባንክ የሚባለው የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በ2ኛው ወለል የዶላር ጠያቂዎችን ሰልፍ በየዕለቱ ማየት ብርቅ አይደለም። ለዓመታት ሰልፉ እየረዘመ እንጂ እያጠረ አልሄደም።
ለውጭ አገር አፋጣኝ ሕክምና 30ሺ ዶላር የጠየቀ ታማሚ፣ ለዚያውም በሐኪሞች ቦርድ የተፈረመበትን ደብዳቤ አቅርቦ፣ ከጠየቀው ገንዘብ አንድ እጅን እንኳ አያገኝም።
ባንኮች የዶላር ጥያቄ የሚያቀርቡላቸው ደንበኞችን ዓይን ይሸሻሉ። ጨክነው ከሰጡም ቆንጥረው ነው።
https://bbc.in/48yTs2b

21/12/2023

Address

Soyama, Burji Manyatta
Eastern

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Burji united posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category