
15/07/2025
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት መካከለኛ ዘመን የጤን ልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓመት ጤቋሚ ዕቅድ ምክክር መድረክ በአርባ ከተማ እየተካሄደ ነው
አርባምንጭ ሀምሌ 08፣2017ዓ.ም (ኤፍኤም 90.9)
ጤናማ ፣ምርታማና የበለፀገ ህብረተሰብ ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የእለቱ የክብር ዕንግዳ አቶ ጥላሁን ከበደ የዘጎችን ጤና ለሻሻል ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰሩ ካሉ አበይት ተግባራት መካከል የጤና ስርዓት ተቋም ፣አገልግሎት አሰጣጥ፣ታዓማኝ የመረጃ አሰጣጥና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ በማሻሻል ውጤታማ ስራዎች መሰራቱን በመግለጽጉባኤውን ከፍተዋል ።
በቀጣይም ጉባኤው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርጉ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
በመርሀ ግብሩም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደን ጨምሮ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ፣ የክልል ፣የዞንና የወረዳ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት እየታደሙ ይገኛሉ ።
ዘጋቢ ፡ ማስረሻ ዘውዴ