የኛ ሚድያ Ours media

የኛ ሚድያ Ours media interst

ዳኒ አልቬስ በክርስቲያኖ ሮናልዶ ላይ ያለው የግል አስተያየት፡- "ንፅፅር የማደርግ ከሆነ... እኔ እንደ ተጫዋች በአጨዋወት ስልት ከሊዮ ሜሲ ይልቅ ወደ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እቀርባለሁ። አሁን...
28/03/2025

ዳኒ አልቬስ በክርስቲያኖ ሮናልዶ ላይ ያለው የግል አስተያየት፡-

"ንፅፅር የማደርግ ከሆነ... እኔ እንደ ተጫዋች በአጨዋወት ስልት ከሊዮ ሜሲ ይልቅ ወደ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እቀርባለሁ። አሁን ባርሳና ማድሪድ ውስጥ አይደለንም ። ምክንያቱም ስለዚህ ጉዳይ ሁል ጊዜ ማውራት ፣ 'አይ ለባርሳ ስለሚጫወት ስለ ማድሪድ ሰው ምንም ጥሩ ነገር መናገር አይችልም!' ያስብል ይሆናል። እኔ ግን መናገር እችላለሁ። እና ክሪስቲያኖ ብዙ ተሰጥኦ ለሌለን ሁሉ በምሳሌነት ይገልፃል ። በትጋት በመስራት ከምርጦች ጋር መወዳደር እንደሚቻል አሳይቶናል። ይህንን በምሳሌነት አሳይቷል፣ እኔም በጣም አከብረዋለሁ። እርስ በርሳችን በምንፎካከርበት ወቅት ይህን ልነግረው እድል አግኝቻለሁ። በትጋት፣ ጥረት በማድረግ ሁሉንም ነገር ያሳካ ወንድ እንዴት አላከብርም?!!! እራሴን ከእርሱ አንፃር ነው የምገልፀው።"

ምንጭ:-World soccer Talk
🇧🇷🤝🇵🇹

አንሄል ዲ ማሪያ🗣️🎤: " በርያል ማድሪድ ቤት ሳለሁ ክርስቲያኖ ሮናልዶን የልደቴ ግብዣ ላይ እንዲመጣ ጠራሁት ። ይመጣል ብዬ አላሰብኩም ነበር ግን እሱ መጣ። ከእኔ ጓደኞች ጋር እንደማንኛው...
26/03/2025

አንሄል ዲ ማሪያ🗣️🎤: " በርያል ማድሪድ ቤት ሳለሁ ክርስቲያኖ ሮናልዶን የልደቴ ግብዣ ላይ እንዲመጣ ጠራሁት ። ይመጣል ብዬ አላሰብኩም ነበር ግን እሱ መጣ። ከእኔ ጓደኞች ጋር እንደማንኛውም ሰው ተቀምጦ ማውራት እና መጫወት ጀመረ። በጣም ተገረምኩ ። በሜዳ ውስጥ ሁሌም አንደኛ መሆን ይፈልጋል ነገር ግን ከሜዳ ውጪ እሱ ፍጹም የተለየ ሰው ነው። ክርስቲያኖ ርናልዶ ይለያል።"

🐐 ቅን ልብ

የኳተሩ አልጀዚራ ጣቢያ የአማራን ህዝብ ቁጥር አሳንሶ 23 ሚሊየን አድርጎ የሰራውን ዜና አስነስተዋል። ጣቢያው ብልፅግና ከሀዲው ስለ አማራ ህዝብ የላከለትን የተሳሳተ መረጃ ባቀረብንለት ቅሬታ...
09/08/2023

የኳተሩ አልጀዚራ ጣቢያ የአማራን ህዝብ ቁጥር አሳንሶ 23 ሚሊየን አድርጎ የሰራውን ዜና አስነስተዋል። ጣቢያው ብልፅግና ከሀዲው ስለ አማራ ህዝብ የላከለትን የተሳሳተ መረጃ ባቀረብንለት ቅሬታ መሰረት አንስቶታል። ከሀዲው ብልፅግና የአማራን ማንነቶች ሁሉ አሳንሶና በጥላቻ የሚልክለትን መረጃ ከአማራ ወገን ሳያጣራ እንደማያቀርብ በላከልን መልዕክ ለማረጋገጥ ችለናል።

ሱሌማን አብደላ

ጥላቻ መጥፎ ነው። በጥላቻ ምክኒያት ነው በዚህ ህዝብ ላይ ጦርነት ያወጅት። ፋኖ ሰቆቃና ግፍ የወለደው የህዝብ ልጅ ነው። ከመጥፋት እጀን አጣጥፌ ከምቀመጥ እየተዋደኩ እኖራለሁ ብሎ የሚዋጋ ሀ...
06/08/2023

ጥላቻ መጥፎ ነው። በጥላቻ ምክኒያት ነው በዚህ ህዝብ ላይ ጦርነት ያወጅት። ፋኖ ሰቆቃና ግፍ የወለደው የህዝብ ልጅ ነው። ከመጥፋት እጀን አጣጥፌ ከምቀመጥ እየተዋደኩ እኖራለሁ ብሎ የሚዋጋ ሀይል ነው። ብዙዎቸ ጦርነቱን የደገፉት ለአምሓራ ያላቸው ገደብ አልባ ፎቢያቸውን መቆጣጠር ስላቃታቸ “ነው። ሁሉም ብሄሩን ያደራጀው አማራውን በመርገም ነው። የብሄርተኝነታቸው መሰረታዊ ሀውልት የጣሉት አማራ የሚባልን ፍጡር በጥላትነት በመፈረጅ ነው። ታዲያ ዛሬ በሚጠሉት ህዝብ ላይ ጦርነት ሲታወጅላቸው ጊዜው አሁን ነው ብለው አሰፍስፈው የአማራውን ስብራት እየጠበቁ ነው። ግን አይቻል በፍፁም ይሄንን ህዝብ እያረዱ እያሰደዱ እየወረሱ እየሰደቡ መኖሩ አብቅቶበታል። መከላከያ የህዝብና አገር ልጅ ነው
በትንሽ ግሩፕ ጥላቻ ብቻ ተመርቶ በዝህ በተገፋ ህዝብ ላይ ጦርነት እንዲገባ አድርገውታል ግን መስሏቸው ነው እንጅ አይችሉም። የተበደለን የተገፋን የተገደለን ህዝብ በአፈሙዝ መግራት አይቻል።

ስረአቱን በደንብ እናውቀዋለን። የነሱን ሀሳብና ፍላጎት ስለምናውቅ ነው ሀቅ የምንፅፈው። በ5 አመት የስልጣን ዘመናቸው ብቻ የቨፈጨፉት አማራ በሩሲያና በዮክሬን መካከል በሚደረገው ጦርነት ውስጥ የዛን ያህል ሰው አልሞተም። አሁን የነሱን የደም ጥማት ለማርካት ሲባል ከሀቅ አንሸሽም።

ሱሌማን አብደላ

አሁንም ይዋሹናል። ልክ ክሀደት እንደፈፀሙብን ሁሉ የጋራ ግብረሀይል እያሉ በግፍ የገደሏቸውን ዜጎች አፅም እያነደዱ ከአጥንታቸው ብራና ቀለም ፍቀው የተሳሳተ ሀሰተኛ መግለጫ ይሰጣሉ። በመሰረቱ...
02/06/2023

አሁንም ይዋሹናል። ልክ ክሀደት እንደፈፀሙብን ሁሉ የጋራ ግብረሀይል እያሉ በግፍ የገደሏቸውን ዜጎች አፅም እያነደዱ ከአጥንታቸው ብራና ቀለም ፍቀው የተሳሳተ ሀሰተኛ መግለጫ ይሰጣሉ። በመሰረቱ አንድም መሰረታዊ የመረጃ ግብአት አቀባበልን መሰረት ያደረገ አዎንታዊ መግለጫ መስጠት አዩቁም። አሰለጠናቸው የሚሏቸው የፖሊስ አባሎቻቸው እጅግ አረመኔና ኢሰዋዊ እንጅ አንድም የሰለጠነ ሀይል የላቸውም።

መጅሊሱን እንደ ፍየል ማሰሪያ ገመድ ነው የናቁት። እንደተቋም አያከብሩትም። አይፈሩትም። ይህ የዋህ ህዝብ ስንቱን ችሎ የተሸከመውን ስረአታቸው ይፈርስ አይመስላቸውም። በግድ ጦርነት እገጥማለሁ አትበሉ ተው ብለን ስንመክራቸው እናተ ሁሉንም የምታቁት ለምን ስሜታዊ ትሆናላችሁ ይሉናል። የህዝብ ልጅ ነን። ህዝብ የሰቀለን ህዝብ የተቀበለን በህዝብ የተወደድን እንጅ ከስረአታቸው ጋር ውል የለንም። ይህ መንግስት በሰራው ስህተት 238 ዜና ተሰርቶበታል። ይህ በአለማቀፍ ሚዲያ ጉዱ የተዘከዘከው መንግስት አደገኛ ኢስላም ፎቢያ እንዳለው የአለም ሙስሊም ኡለሞች የሰሩበትን ዜና አይተናል።

ለነሱ ይህ አደገኛ ሁኔታቸው መሆኑን አያቁም።
ስልጣን ከተረከቡ ጀምሮ አንድ ነጥብ 2 ሚሊየን አየገሪቱን ዜጋ አስገድለዋል። ልክ የኩዌትን ህዝብ ቁጥር ጨርሰዋል። 10 አመት የተደረገው የሶሪያ ጦርነትን በእጥፍ በልጠው ተገኝተዋል። ሙስናቸው አለምን ያስንቃል። የስልጣን መዋቅራቸው እጅግ ያፀየፈ ነው። ይህንን ጊደሎ ተሸክሞ የኖረ ህዝብ ላይ ጥይት ሲተኩሱ አያፍሩም። አይፈሩም። ለምን ከተባለ ንቀት አላቸው። ስለዚህ ልክ ማስገባት ያለበት ህዝቡ ነው።

ደም ለምደዋል። ገለው መዋሸት ውሸት ማቀነባበር ሱሳቸው ነው። 5 አመት አታለሉን አምስት አመት ገደሉን ረሀብ ጦርነት ዝርፊያ ማፈናቀላቸው ሁሉ ጆኖሳይድ ነው። በደም የሰከረ ስረአት ለማንም አይጠቅምም። ከአዲስ አበባ 400 km እርቀት ላይ በአማፂ እየተቆ ዋና ከተማ ላይ የተቀመጠን ሰላማዊ ህዝብ ጥሌቶቸ ናቸው የሚል ስረአት ነው አሁን ያለው። እያበዱ የሚስቁ በሰው ደም ውስኪ የሚራጩ በደሀ ኢኮኖሚ የሚንደላቀቁ አንድም ለአገር ሰላም የማያስብ ለሚመሩት ህዝብ የማይራሩ አደረጃጀቶችን ይዘው ነው እናበልፅጋችሁ የሚሉን።

ሱሌማን አብደላ

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞን በመስጂድ ጊቢ ማሰማት ለሞት የሚያበቃ ወንጀል ነውን?🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን።🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵ዛሬ በአንዋር መስጂድ የጸጥታ አካላት በምዕ...
02/06/2023

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞን በመስጂድ ጊቢ ማሰማት ለሞት የሚያበቃ ወንጀል ነውን?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን።
🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵

ዛሬ በአንዋር መስጂድ የጸጥታ አካላት በምዕመናን ላይ የወሰዱት ድርጊት እጅግ አሳዛኝና አስደንጋጭ ነው። በሸገር ከተማ የተፈጠመውን መስጂዶችን በጅምላ የማፍረስ ደርጊት ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ሲያስቆጣ መክረሙ ይታወቃል። መስጂዶቹ እንዳይፈርሱና ለፈረሱትም ምትክ ቦታ እንዲሰጥ የፌዴራል፣ የኦሮሚያና የአዲስ አበባ መጅሊሶች ባለፉት ሳምንታት ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል። ጥረቶች ተስፋ ሲያሳዩና መልሰው ሲባባሱ ቆይተው ሁኔታዎች ወደ አደባባይ ተቃውሞ ተቀይረዋል። የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባለፈው ሳምንት ጁሙዓና ዛሬ ምዕመናንን ገድለውብናል፣ አቁስለውብናል። በርካቶችንም አስረዋል።

መንግሥት «እያካሄድኩት ነው» ባለው የጸጥታ ተቋማት የሪፎርም ሥራ ግርግሮች ሲከሰቱ ሰው ሳይሞት በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በጸጥታ አካላት አዳዲስ ኪህሎቶችና ዲሲፕሊን ሁኔታዎችን ማረጋጋት የሚያስችል ሁኔታዎች ተፈጥርዋል ተብሎ ከዚህ ቀደም ተነግሮን ነበር። እኔን ጨምሮ በርካታ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች፣ አመራሮችና ታዋቂ ሰዎች የተገኙበት ጉብኝት ከዚህ ቀደም ወደ ፌዴራል ፖሊስ ተቋማት አድርገን ነበር። በጉብኝታችን ወቅት አድማ ብተና ልክ እንደ አደጉት አገራት ሰው ላይ ሞትና የከፋ አደጋዎች ሳይደርሱ የአድማ ብተና ስራ ለመስራት የሚያስችል አቅምና ቴክኖሎጂ እንደተገነባ ተገልጾልን ነበር።

ነገር ግን ባለፈው ሳምንትና ዛሬ በአንዋር መስጂድ የሆነው ግን ከዚህ በተቃራኒው ነው። የጸጥታ አካላት በቀጥታ ምእመኑ ላይ በመተኮስ ወደ ግድያ ነው የገቡት። እንደተባለው ሁከት ፈጣሪ አካላት ካሉ ውሃ በመርጨትና ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከላከል ሲቻል ወደ ግድያ የሚገባበት ምክንያት ምንድን ነው?

ሌላው ሙሉ የአዲስ አበባ ከተማ የአንዋር መስጂድና አካባቢውን ጨምሮ አብዛኛውን የአዲስ አበባን ክፍል የፌዴራል ፖሊስ በካሜራ 24 /7(ዘወትር ለ24 ሰዓት) እንደሚቃኝ ይታወቃል። ይኽንን በጉብኝታችን ጊዜ ጭምር ሚክሲኮ ከሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ዋና ማዕከል ላይቭ ሲከታተሉ አሳይተውናል። ሂደቱንም በቪዲዮ እንደሚቀረጹ ና በማስረጃነት እንደሚያዝ በርካታ የአደባባይ ወንጀል ናሙና ቪዲዮዎችን አሳይተውናል። ይህ ማለት በየትኛውም የአዲስ አበባ ክፍል ግርግር ከተነሳ የግርግሩ ጀማሪ ማን እንደሆነና እንዴት እንደተጀመረ በትክክል መለየት ይችላሉ። በዚህም መሰረትም ግርግሩ የተነሳበትን ቦታና ማንነት ለይቶ የጸጥታ ማስከበርና ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር የማዋል ሥራ ከመስራት ይልቅ እየተመለከትን ያለነው ግን መላው ምዕመን ላይ መሳሪያ የመተኮስ አካሄድ ነው ።

የፌዴራል መጅሊስ ባደረገው ጥሪ መሰረት በዛሬው እለት የተቃውሞ አንቅስቃሴ በአንዋር መስጂድ እንዳልነበር ብዙዎች መስክረዋል። የጸጥታ ተቋሙ ተቃውሞ ነበረ ካለም ማስረጃ ይፋ ማድረግ አለበት። እንደው ተቃውሞ ነበረ አልያም ፖሊስ ሁሌም ቶክስ ለመክፈት «ድንጋይ ተወርዉሮብኝ ነው።» በማለት እንደው ጥቂት ሰዎች ድንጋይ ወርዉረው የነበሩ ቢሆኑ እንኳን ወርዋሪዎቹን በሚቀርጹት ቪዲዮ ለይተው በሕግ መጠየቅ እየተቻለ ነፁሓንን ሙስሊሞችን ጨምሮ በሺህ የሚቆጠረውን በመስጂዱ የሰገደውን ምዕመናንን እንዲሁም በዜናው ተደናግጦ የሚሸበረውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝበ ሙስሊምንና ሌሎች ኢትዮጵያውንን ማሸበር መች ወንጀል ሆኖ ያስጠይቅ ይሆን? በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞን በመስጂድ ጊቢ ማሰማት ለሞት የሚያበቃ ወንጀል ነውን?

ፖሊስ ሌሎችን ወንጅሎና ራሱን ንጹህ አድርጎ መግለጫ ስላወጣ አንዳች የማጣራት ሂደት ሳይደረግ ለጊዜው ተድበስብሶ ቢቀር እነኳ እውነታው ዘላለም ተደብቆ አይቀርም።

በመስጂዱ ጊቢ ውስጥ የነበረ ምዕመን ድምጹን ቢያሰማ እንኳ፣ ሕዝቡ ላይ በጅምላ መተኮስና ከመስጂድ እንዳይወጣ ፣ የሞቱና የቆሰሉና ሰዎች በአምቡላንስ እንዳይነሱ ለረጅም ሰዓታት መከልከል በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለው የወንጀል ድርጊት ነው።

31/05/2023

ዛሬ ከምሺቱ 4 ሰአት የኢሮፓ ሊግ ፍፃᎂ ጨዋታ ይካሄዳል
Sevilla vs Roma
ጆዜ ቢያሸንፉ ምኞቴ ነው
ሰለጆዜ በፍቅር ይልቃል እድህ ይታወሳሉ

ከወለድኩኝ 4ተኛ ቀኔ ነው። 5ኛ ቀኔን ልጀምር ስል እላየ ላየ ላይ ቤቴን አፈረሱብኝ። አራስ ነኝ ስላቸው ባልሽን ጠይቂው እኛ ባልሽ አደለንም አሉኝ። የት ልሂድ ልጀን ፀሀይና ብርድ ይገልብኛ...
30/05/2023

ከወለድኩኝ 4ተኛ ቀኔ ነው። 5ኛ ቀኔን ልጀምር ስል እላየ ላየ ላይ ቤቴን አፈረሱብኝ። አራስ ነኝ ስላቸው ባልሽን ጠይቂው እኛ ባልሽ አደለንም አሉኝ። የት ልሂድ ልጀን ፀሀይና ብርድ ይገልብኛል ስላቸው ጥላ አለበት የትም ሂጅ አሉኝ፣ አለች አንዲት እናት። እንዲህ አይነት ግፍ በራስ ዜጋ ላይ መፈፀም እጅግ አረመኔና የለየለት የህዝብ ጥላቻ ነው።

ሱሌማን አብደላ

Address

Jeddah
22233

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኛ ሚድያ Ours media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share