Yonas Tade

Yonas Tade ይህ ቻናል መንፈሳዊ መልእክቶች እና ዝማሬዎች ይተላለፉበታል:

07/10/2025

ጊዜ ወንፊት ነው ሁሉን ያጣራል::

07/10/2025

“እውቀት ላብላ እንጂ ልብላ ሲሉበት ድንቁርና ይሆናል”::

07/10/2025

ሰላም ለሁላችን፤- በጌታችን መንግስት ቦታ እንዲኖረን፣ ደግሞም በቀኙ እንዲያቆመን ምን እንደሚያስፈልገን ልብ ብላችሁ ታውቃላችሁ? ሰይጣን በትምህርተ ሃይማኖት ክርክር ጉዳይ ራሳችንን እንድንይዝ አድርጎ ፍቅር አልባ ነፍስ እንዲኖረን ሊያደርገን እንደሚሰራ ልብ በሉ! በጥልና በክርክር ራሰንም በማጽደቅ ረብ የለሽ ፍሬ አልባ ሰው እንደሚያደርገንም ተመልከቱ! ወንጌል ግን እንዲህ ይላል፡- ንጉሱም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላችዋል፤- የአባቴ ብሩካን ኑ! ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ፡፡ ተርቤ አብልታችሁኛልና፣ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፣ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፣ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፣ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፣ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኃልና፡፡ ማቴ 25፤34-36 እግዚአብሔር ያስማረው አማኝ እንዴት በዓለም ላይ ያሉ /ኢየሱሶችን/ድሆችን እንደሚረዳ መነጋገር እንደሚገባው ማሰብ አለበት፡፡ ንጹህ የሆነ ነውር የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፡፡ ወላጆች የሌሏቸውን ልጆች፣ ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው ያዕ 1፤27 እንዳንታለል! ይሄ ብቻ ነው በፊቱ የሚያቆመን ይሄ ብቻ ነው ካመኑ ሰዎች የሚጠበቀው †††
እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም 2013

07/10/2025

ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ
ሉቃ 22:46

07/10/2025

ክፉ ቀን ከፀሎት ውጭ መሻገሪያ ድልድይ የለውምና አብዝተን እንፀልይ

እግዚአብሔርን ማምለክ ከቅንነትና ከእምነት የሚወጣ አገልግሎት ነው። መገለጫውም ፍቅር ነው። ፍቅር ሲባል የራሱን የአምልኮ ክልል ሰዎች ብቻ መውድደና መንከባከብ ሌላውን መናቅና መርሳት እይደለ...
07/06/2025

እግዚአብሔርን ማምለክ ከቅንነትና ከእምነት የሚወጣ አገልግሎት ነው። መገለጫውም ፍቅር ነው። ፍቅር ሲባል የራሱን የአምልኮ ክልል ሰዎች ብቻ መውድደና መንከባከብ ሌላውን መናቅና መርሳት እይደለም። አምነት እውነተኛ መሆኑ የሚረጋገጥበት አንዱና ትልቁ መስፈርት ፍቅር ነው። ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው። ፍቅር ሰውን እንስሳትን ተፈጥሮን ሰማያውያንን እና እግዚአብሔርን መውደድ ነው። ፍቅር ሰፊ ክንፍ ነው። ስባራ ክንፍ አይደለም አንዱን አቅፎ አንዱን የተወ አይደለም። አያስመስልም። እውነተኛ ነው። እውነተኛ በመሆኑ ጥቃት ይደርስበታል። ግን ወርቅ መሬት ቢወድቅ ጸባዩ እንደማይለወጥ አይለወጥም።
እባካችሁ ለሌሎች አካፍሉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

07/06/2025

“ክፉ እመልሳለሁ አትበል፤ እግዚአብሔርን ተማመን፥ እርሱም ያድንሃል።”
ምሳ 20፥22

07/05/2025
07/05/2025

ተወዳጆች
የእስራኤል ልጆች ብርቱ ጠላታቸው ከነበሩት ከምድያም እጅ ጌዴዎን ከታደጋቸው በኃላ እንዲህ አሉት:- "ከምድያም እጅ አድነኸናልና አንተ ልጅህም የልጅ ልጅህም ግዙን አሉት::ጌዴዎንም:- እኔ አልገዛችሁም ልጄም አይገዛችሁም እግዚአብሔር ይገዛችኃል አላቸው" መሳፍንት 8:22 እኛስ ማን ይግዛን? እግዚአብሔር በጽድቅ ይግዛን እርሱ ከገዛንና ለእርሱ ከተገዛን ሁሉ ሰላም ሁሉ መልካም ሁሉ ደህና ይሆናል:: ሃገራችን በሰማይ ነውና አርቀን እናስብ በማስተዋል እንራመድ :: እግዚአብሔር የሌለው ሰው ለክፋቱ ምንም ከልካይ የለበትምና ከእግዚአብሔር ጋር እንሁን ሰዎች እንደ እኔ ካላሰቡ ከሚል ግትር አስተሳሰብ ራሳችንን እንጠብቅ::

ሰላም ለሁላችሁ፦ ላሊበላ እግዚአብሔር እንደሚወደው ያውቅ ነበር፡፡ ስለዚህም ዙፋን ከተቀዳጀ በኃላ ለድሆችና ለችግረኞች በልግስና ይመፀውት ነበር ይላል ስለ ቅዱስ ላሊበላ የተጻፈው ስንክሳር፡፡...
07/05/2025

ሰላም ለሁላችሁ፦ ላሊበላ እግዚአብሔር እንደሚወደው ያውቅ ነበር፡፡ ስለዚህም ዙፋን ከተቀዳጀ በኃላ ለድሆችና ለችግረኞች በልግስና ይመፀውት ነበር ይላል ስለ ቅዱስ ላሊበላ የተጻፈው ስንክሳር፡፡ የቀደሙ የኢትዮጵያ አባቶች በፀጋው ያምኑ ነበር፡፡ ሰው እግዚአብሔር እንደሚወደው የሚያውቀው በክርስቶስ የተሰጠውን ፍቅርና ፀጋ በሚገባ ሲረዳ ነው፡፡ ይህ የህይወቱን ሰረገላ የሚስበው ፈረስ ማለት ነው፡፡ ወደ በጎ ስራ የሚያንደረድረን የሲዖልን አሳት ከመፍራት በላይ በጌታ መወደዳችን ነው፡፡ የንጉስ ላሊበላ ህይወት ይህን ይናገራል፡፡ ጌታዬ በሞቱ ከወደደኝ እኔስ በምድሬ የሚገኙ ድሆችነ ለምን እንጀራ አላጠግባቸውም? ብሎ በረታ፡፡ ከማስፈራራት ይልቅ ፍቅር የበለጠ ኃይል ይሰጣል፡፡ የእግዚአብሔር ሰራተኞች ሆይ ጌታችን ሰዎቸን እንዴት እንደወደደ አብዘተን ልንነግራቸው ይገባል፡፡ መስቀሉን በደንብ ማብራራት አለብን፡፡ ያኔ የምናገለግላቸው ሰዎች ህይወታቸው እየተቀየረ ይመጣል፡፡ ያኔ እግዚአብሔርን እየወደዱት ይመጣሉ፡፡ ያኔ ወደው ትዕዛዙን ይጠብቃሉ፡፡ ያኔ ብትወዱኝስ ትዕዛዜን ጠብቁ ተብሎ እንደተጻፈ ይሆንላቸዋል፡፡ ዮሐ 14:15 እሳት ፈርቶ ጥሩ ሰው ከመሆን እግዚአብሔርን ወዶና ፈርቶ ታማኝ መሆን ይሻላልና፡፡
እባካችሁ ለሌሎች ያካፍሉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

07/05/2025

ሰዎች ሲያከብሩ አምላክ ሲጠሉ ሰይጣን ማለታቸው የተለመደ ነው:: ሁለቱም ተገቢ አይደለም ሰውን ሰው ማለት ብቻ ከመሳት እና ከመሳሳት ይጠብቃል::

የአባቴን ሥራ እሠራለሁ!!አንድ ክርስቲያን ሃይማኖት የሌለው ጎረቤት ነበረው። ጎረቤቱም ሁልጊዜ ግቢ ይጥለዋል። ክርስቲያኑም የራሱንና የጎረቤቱን ቆሻሻ አንስቶ ይጥላል። አንድ ቀንም ቆሻሻ ሲወ...
07/04/2025

የአባቴን ሥራ እሠራለሁ!!

አንድ ክርስቲያን ሃይማኖት የሌለው ጎረቤት ነበረው። ጎረቤቱም ሁልጊዜ ግቢ ይጥለዋል። ክርስቲያኑም የራሱንና የጎረቤቱን ቆሻሻ አንስቶ ይጥላል። አንድ ቀንም ቆሻሻ ሲወረወርበት ጓደኛው መጣ። "አንተ መልሰህ ለምን አትወረውርበትም?" አለው። ክርስትያኑ ግን፦"እርሱ የአባቱን ሥራ ይሥራ፣ እኔም የአባቴን ሥራ እሠራለሁ" አለው ይባላል።

ሁሉም የራሱ ቆሻሻ አለው። አንዱ ጠርጎ ይጥላል፣ ሌላው ወደ ጎረቤቱ ይጥላል። የሰይጣን ስራው መቆሸሽና ማቆሸሽ ነው። የእግዚአብሔር ሥራ ግን ማንፃትና ማፅዳት ነው። የአባታቸው ስራ መሳደብና መንቀፍ ከሆነ ፣ የአባታችን ሥራ መጸለይና ማፍቀር ነው። የአባታቸው ሥራ መግደልና ማጥፋት ከሆነ፣ የአባታችን ሥራ ማዳንና መርዳት ነው። የአባታቸው ሥራ ሐሜትና ስም ማጥፋት ከሆነ፣ የአባታችን ሥራ ቃሉን መስበክና የክርስቶስን ውበት ለዓለም መግለጥ ነው። የአባታቸው ሥራ ንቀትና ትዕቢት ከሆነ፣ የአባታችን ሥራ ማክበርና ለሰው ዋጋ መስጠት ነው።
ቆሻሻን ቢጥሉም የወረወሩትን መልሰን አንወረውርም። ክብራችን አይደለም።

እንደ አባታችን እየኖርን እግዚአብሔርን የምናከብረው በምድር ነው። በሰማይ በጎ መስራት የለም፣ በሰማይ ያለው የበጎ ነገር ሽልማት ነው። እግዚአብሔርን ባልተሰጠን በመግባት አናከብረውም። ድርሻችንን በመወጣት እናከብረዋለን። እኔ የአባቴን እሰራለሁ!!!

እናንተስ?
bisrat gebriel

Address

Atlanta, GA

Telephone

+14047865011

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yonas Tade posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yonas Tade:

Share