08/23/2026
አንድ ወደ ላጤ ለገና በዓል ሰው ሁሉ ቤት ዶሮና በግ ሲገዛ አይቶ እርሱም ቅርጫ ገባና ስጋውን በዘንቢል ይዞ ወደ ቤት ተመለሰ፡፡ ለጥብስ የሚሆን ይመርጥ ዘንድ ሙዳ ሥጋውን ጎትቶ መክተፊያ ላይ አስቀምጦ ቢላዋ ሊዋስ አከራዩ ቤት በሄደበት ድመት ገብታ ሥጋውን ጎትታ ትወጣለች፡፡ ሲደርስ ድምቷን ተመልክቶ በንዴት ይከተላት ጀመር፡፡ ድመቷም ሙዳዋን ላለማጣት ፈጥና ጢሻ ውስጥ ገባች፡፡ በንዴት ስሩ እንደተገተረ ወደ ቤት ሲመለስ ቤቱ ባልታወቀ ሁኔታ ተደርምሶ ጣሪያው ቤቱ ላይ ወድቆ ተመለከተ፡፡ በዚያ ሰዓት ቤት ውስጥ ሆኖ ቢሆን ሟች እንደነበር ተረዳ፡፡ እግዚአብሔር ሊያተርፈው ትንሽ ድመት እንደላከለት ሲመለከት ተመስገን ብሎ ወደ ልቡ ተመለሰ፡፡ ተወዳጆች ሆይ፡ -በአስቸጋሪ ህይወታችሁ ውስጥ እግዚአብሔር የሚያመጣውን ትርፍ ታያላችሁና አትቸኩሉ፡፡ ኑሃሚን በብዙ ኪሳራዋ ውስጥ ቆንጆዋን ሩትን አትርፋለች፡፡ ጎደለኝ፣ አልተሳካም፣ መከራ በዛብኝ፣ ተፈተንኩ፣ ትግልና ተግዳሮት በዛብኝ የምትሉ ሆይ አምላካችሁ በዚህ ውስጥ የሚሰጣችሁ ውብ ስጦታ አለ፡፡ የሚሆነውን አታውቁም እና ዝም በሉ፡፡ ኑሃሚን በረከቷን ሩትን ይዛ ቤተልሔም ስትደርስ እግዚአብሔር አስመረረኝ እያለች ጌታዋን ትወቅስ ነበር፡፡ ለማኝ ሆና የምትቀር መስሏት ነበር፡፡ ይህን ያለችው እርሷ እንጂ እግዚአብሔር አልነበረም፡፡ ቆይቶ ሩት ጸሐይ ሆና ወጣችላት፡፡ የትልቅና የሃብታም ቤተሰብ አያት ለመሆን በቃች፡፡ እግዚአብሔር እንደዚህ ነው፡፡
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም