12/28/2025
ከአያ ሙሌ ጋር ቅኔ የሚዘራረፉም ነበሩ፡፡ ወሰን የሚባል ልጅ እና አያ ሙሌ የሚከተለውን ቅኔ ተዘራርፈው ነበር
መታከትና መመከት
የሞኝ አዋጅ መለከት
በጊዜ ኩሉ መታከቱ
ክብሩ ሞቱ ለሠማዕቱ
ወ በጊዜ ለኩሉ እንዲል ቃሉ
ሰምተው የተስማሙት ያውቃሉ
አልሞት አይቶት ቢመረው
ራሱን ሰቅሎት አረፈው
ማን በማን ላይ
እሱ ጣና እኔ አባይ
የወዲያውን ቅጠል ቢመኘው
ሰው አምላክ መሆን አሰኘው
እሱ የቸረኝን ከመጣብኝ ከልካይ
እፋለመዋለሁ እኔስ ምኔ ብካይ
ይሄን ቅኔ በተዘራረፉበት ሰዐት አርቲስት ሳምሶን ወርቁ "በቃ ይበቃል" ብሏቸው መዘራረፉን አቁመው ነበር፡፡
***
የባለቅኔው ኑዛዜ