09/13/2025
"አባትነት"
=======
=======
አባቴ የጉልበት ሰራተኛ ነው፤አዘውትሮ የሚለብሳቸው ውስን ልብሶች ብቻ ነበሩት፤እኔን ግን ምንም ሳያጓድል አቀማጥሎ አሳድጎኛል፤በለስ ቀንቶት ያገኘውን ገንዘብ በሙሉ አንድም ሳይቀንስ ለእናቴ ይሰጣትና "የዛሬ ዘመን ልጆች መከፋታቸውን የሚሸሽጉት በሆዳቸው ነው" እስካለሁ ምንም እንዳይጎድልባቸው ብሎ ወደ ሰርክ ስራው ያቀናል፤አባቴን ዘወትር ሰበብ እየፈጠርኩ ገንዘብ እጠይቀዋለሁ፤ገንዘብ ከመጠየቅ በስተቀር አንድም ቀን ግን ስለስራው ጠይቄው አላውቅም ፤ዛሬም አንደወትሮው ወደ ስራ ከመሔዱ በፊት ለትምህርት ቤት ፕሮግራም ትንሽ ብር እንደምፈልግ ነገርኩት፤ትንሽ አሰብ አደረገና "ልጄ ለምን ነገ አልሰጥክም አለኝ?" ዛሬ ካልሆነ ሞቼ እገኛለሁ አልኩት፤ትንሽ አሰብ አደረገና ያልኩትን ብር ሳያጓድል ቦርሳውን አራቁቶ ሰጠኝና በርትተህ ተማር ብሎኝ ሔደ ፤የሚያሳዝነው ግን አባቴ ያን ቀን ጨምሮ ለተከታታይ ቀናት በታክሲ ሁለት ሰአት የሚፈጀውን መንገድ ወደ ስራ ሲመላለስ የነበረው በእግሩ ነበር፤ምክንያቱም ለእኔ የሰጠኝ የትራንስፖርቱን ብር ነበርና፤ከዚያን ቀን ጀምሮ አባቴን አምስት ሳንቲም ጠይቄው አላውቅም፤ከዚህ ይልቅ ሙሉ ትኩረቴን ትምህርቴ ላይ አደረግኩ።
=======================================
ማስታወሻ፦ክብር በአስቸጋሪ የህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ እያለፉ ለልጆቻቸው መስዕዋትነት ለሚከፍሉ ወላጆች ይሁን።
=======================================