Awusa.com

Awusa.com A resource and advocacy center for the art, history, culture, ethnography and current affairs of Afa

የትግራይም ሆነ የኤርትራ  ህዝብ  እንደ ማነኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ጥንትም አሁንም ኢትዮጵያዊ  የኢትዮጵያ 1.3 ሚሊየን ኪ.ሜ² ግዙፍ ምድር  የእሱም ጭምር  ነው ። ኢትዮጵያ የኤርትራ...
07/18/2025

የትግራይም ሆነ የኤርትራ ህዝብ እንደ ማነኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ጥንትም አሁንም ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ 1.3 ሚሊየን ኪ.ሜ² ግዙፍ ምድር የእሱም ጭምር ነው ። ኢትዮጵያ የኤርትራ ክፍለ ሃገርን ጨምሮ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ናት እውነታው ይህ ነው ።

ሲቸገሩ፣ ሲያጡ ፣ ሲደሰቱም ሁሉም የሚመጣው የሚሰደደው ወደ እናት ሀገር ኢትዮጵያ ነው በአለፉት 7ዓመታት ብቻ ወደ እናት ኢትዮጵያ የተሰደዱ ከ 1 ሚሊየን በላይ ኤርትራዊያን በኢትዮጵያ ዜግነት ተቀብለው ይኖራሉ ፣ ከዛ በፊት " ኤርትራዊ ናችሁ ተገንጠሉ" ተብለው ኢትዮጵያ የቀሩትን ቤት ይቁጠረው ፣ ከመላው ኢትዮጵያ የተዳቀለው የኤርትራ ክፍለ ሀገር ህዝብም በፖለቲካ ድራመኞች ጥረት ሀገር ለመሆን ሞክሮ ተነጥሎ ሀገር አልባ የሆነውም ለዚህ ነው።

የትግራይ ክልል ህዝብም ጉዳይ ከዚህ የተለየ አይደለም፤ "ሀገረ ትግራይ" ሚባል ነገር ቅዥት ነው፣ የህውሃትና ሻዕቢያ የደም ነጋዴ ቡድን በነ ስብሃት ዲዛይን ኤርትራን በግድ የገነጠለውና ኤርትራን ሃገር ያረገው ትግራይን የኢትዮጵያ ድምበር አርጎ ለማስገንጠል እንዲመች ነበር ፣ ነገር ግን ከዛ እልቂት በውሃላ እንኳን ትግራይ ሀገር ልትሆን ኤርትራም የተራ ክልል ቁመና መያዝ ተስኗት አረፈችው ።

ህዝብ ህዝብ ነው ፣ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከየትኛውም ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ምዕራብ ፣ምስራቅ ያለ ኢትዮጵያዊ ጋር ተዋልዶ ተዋዶ ነው እየኖረ ያለው። በመሆኑ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተናቦ እነዛን የነ ስብሃትና ኢሳያስ የውጭ ተላላኪ የኢትዮጵያን ታሪክ ያጠቆሩ ባንዶች ስብስብ ላይ ከተነሳ የኢትዮጵያ ችግር 99 ከመቶ ይፈታል።

ህዝባችንን የከፋፈሉት፣ የገነጣጠሉት፣ ለዘመናት ያባሉት የሻዕቢያ ህውሃት 100 ማይሞሉ አስመራና መቀሌ የከተሙ አዛውንቶች ላይ በቋንቋ በሰፈር ሳይከፋፈል ጥላቻን ጥሎ ...ሆ... ብሎ ለመነሳት ከዘመናት መተላለቅ ነፃ ለመሆንና አብሮ ታሪክ ለመቀየር ቁርጡ ግዜ አሁን ነው ።

በተረፈ እኛ ኢትዮጵያዊያን እውነታውንና ማንነታቸውን ከማስረዳት ባለፈ ግን የማይቀር የሆነው ኢትዮጵያ በድራማ የተነጠቀችውን የቀይ ባህር ድምበሯን በቅርቡ ወደ ራሷ ታካልላለች። ...ከዛ ከምፅዋ ወዲያ ሀገር ነኝ ሚል ካለ መንገዱን ስፖንጅ ያርግለት እንለዋለን ።

ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet

በአፋር ክልል ዳሎል ወረዳ ባዳ አድምሩግ የተነሳው እሳት🔥 በከባድ ነፋስ ታግዞ በፍጥነት ብዙ ቤቶች እየተቃጠለ ይገኛል😪
07/17/2025

በአፋር ክልል ዳሎል ወረዳ ባዳ አድምሩግ የተነሳው እሳት🔥 በከባድ ነፋስ ታግዞ በፍጥነት ብዙ ቤቶች እየተቃጠለ ይገኛል😪

በአፋር ክልል አፍዴራ ከተማ  በጣለዉ ከባድ ነፋስ የቀላቀለ ዝናብ የሰዉ ህይወት ጠፋ በአፋር ክልል አፍዴራ ከተማ ትናንት ምሽት በጣለዉ ብርቱ ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰዉ ሕይ...
07/16/2025

በአፋር ክልል አፍዴራ ከተማ በጣለዉ ከባድ ነፋስ የቀላቀለ ዝናብ የሰዉ ህይወት ጠፋ

በአፋር ክልል አፍዴራ ከተማ ትናንት ምሽት በጣለዉ ብርቱ ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰዉ ሕይወት ጠፋ፤ 31 ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደረሰባቸዉ። 25 ሺህ የሚደርሱ ሰዎችም ከቤት ንብረታቸዉ መፈናቀላቸዉ ተመልክቷል። በአደጋዉ የጨዉ ፋብሪካዎች የፈረሱ ሲሆን በከተማዉ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶችም ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የደረሰዉን አደጋ ተከትሎ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ንፋስ የቀላቀለዉ ዝናብ ባስከተለዉ ጎርፍ ተወስደዉ እስካሁን ያልተገኙ ሰዎች መኖራቸዉን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በአደጋዉ ቤታቸዉ የፈረሰባቸዉ የከተማዉ ኗሪዎች በሜዳ ላይ ያለመጠለያ መሆናቸዉ ተገልጿል። የአፋር ክልል አደጋ ስጋት አመራር የሎጀስቲክ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አሊ መሀመድ ሳላህ የደረሰዉ አደጋ ከባድ መሆኑን ዐሳዉቀዋል። አጠቃላይ የጉዳት መጠኑን ለመለየት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል። በአደጋዉ የቴሌኮምና ኤሌትሪክ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ 5 ፍብሪካዎች 3 የሃይማኖት ተቋማት፤ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት፤ የትምህርት ተቋማት፤ ባንኮች የጤና ተቋማትና መኖሪያ ቤቶች ከባድ ዉድመት እንደደረስባቸዉ ተገልጿል።

ምንጭ፤ አፍዴራ ወረዳ አስተዳደር

የኢሳያስ ኤርትራ***********ዛሬ ጠዋት "የኤርትራ ጄኔራሎች" ተብሎ እዚህ ቢሆኑ ወደ ሜቄዶኒያ መላክ የነበረባቸውን ሼባዎች ፎቶ አየሁ። ልብ አይሞት ሆኖባቸው ነው እንጂ እነዚህ "አንድ ...
07/15/2025

የኢሳያስ ኤርትራ
***********
ዛሬ ጠዋት "የኤርትራ ጄኔራሎች" ተብሎ እዚህ ቢሆኑ ወደ ሜቄዶኒያ መላክ የነበረባቸውን ሼባዎች ፎቶ አየሁ። ልብ አይሞት ሆኖባቸው ነው እንጂ እነዚህ "አንድ ጋት በአንድ ሰዓት" የማይራመዱ ጦር መርተው ያዋጋሉ ማለት ዘበት ነው።

ነገሩ ወዲህ ነው። ኢሳያስ "ኤርትራ" የምትባል አገር ይሆናል ብሎ ባላሰበው ሁኔታና አጋጣሚ እጁ ላይ ዱብ ያለችበት ሰው ነው። Thanks to የመንግሥቱ ኃ/ማርያምና ጀሌዎቹ ድንቁርናና እብሪት። በዚህ ምክንያት የኤርትራን "አገርነት" እሱ ሳይሞት ማስረገጥ ይፈልጋል። ከነድክመቷም "አገር" ናት የሚለውን የኤርትራ Identity መፍጠርና ራሱን የኤርትራ አባት ለማስባል ያልማል።

ለዚህ ደግሞ ያበቃው አራዳው መሌ ነው። መሌ "የትግራይ ነጻ አውጪ" እያለ ለ17 ዓመታት ሲዋጋ ኖሮ ነገሩን "ብሪሊያንትሊ" ሲያስበው
- የዓለም የፖለቲካ ሁኔታ በፊት ከነበረው መቀየሩን
- ደርግ መንኮታኮቱን
- ምዕራባዊያን ከተራ ነጻ አውጪ በላይ እያዩት መሆኑን
- 4 ኪሎ ለመግባት ብዙም እንቅፋት እንደሌለበት
ወዘተ ....አየና ሐሳብ ቀየረ።

ከትግራይ ነጻ አውጪ ወደ ኢትዮጵያ ነጻ አውጪ።

ለመሌ ይህንን ለውጥ ለማደናቀፍ እንቅፋት የሚሆንበት አንድ ሰው ኢሳያስ ነበር። በወቅቱ ጠንካራ ሠራዊትና መሣሪያ የነበረው እሱ ነውና።

መሌ ለዚህም ዘዴ አላጣም። ኢሳያስ ለ30 ዓመት ተዋጋሁለት የሚለውን የኤርትራን ነጻነት እውቅና መስጠትና ለዚያ ተባባሪ መስሎ መገኘት። ቀን እስኪያልፍ። ኤርትራ ነጻ ወጣች። መሌም ተሽቀዳድሞ እውቅና ሰጠ።

ቀኑ ደረሰ!

"የዓይናቸው ቀለም ደስ ካላለን..." አለ መሌ ትከሻ ለትከሻ ለመለካካት መድረሱን ሲያውቅ። ኢሳያስ መሸወዱን ያወቀው ይኼኔ ነበር። ከዚያን ቀን ጀምሮ የኤርትራን አገርነት ሁሌም አደጋ ውስጥ እንደሆነ ገባው። ጠንካራ ኢትዮጵያ የተመሰረተች ቀን ኤርትራ እንደምትገብር ተረዳ።

ወይኔ ኢሳያስ!!

በተጨማሪም ከዚያ ቀደም ከጣሊያን ቅኝ ግዛት በኋላ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትዋሃድ ያደረጉ ጠንካራ ግለሰቦች ጉያው ውስጥ እንዳሉ ያውቃል። ቀን ያገኙ ዕለት ብድግ ማለታቸው እንደማይቀርም ጭምር። ሰዎቹ ዛሬ ድምጻቸው ቢታፈንም "ቀላል ሰዎች" እንዳልሆኑ በደንብ ይረዳል። እነዚህ ሰዎች ዐቢይ የሔደ ጊዜ ብቅ ብቅ ብለው ነበር። "እኛ እኮ አንድ ነን" እያሉ ።

መለስ ሞቶ ዐቢይ ሲመጣ እንደ ኢሳያስ ደስተኛ ሰው አልነበረም። በማዕቀብ አስሮ መከራውን ሲያበላው የከረመው መለስ ሔዶለት ከሰውና ከዓለም ጋር እንዲገናኝ ያደረገው ዐቢይ ሲመጣ ለምን አይደሰት።
ግን ምን ዋጋ አለው ዐቢይም ሸወደው። "ጠላቴ" ከሚላቸው ተረፈ ወያኔዎች ጋር ካዋጋው በኋላ እጥፍ አለበት።

ኢሳያስ ከዚህኛው ሽወዳ አንድ ነገር ያተረፈው እንደ መሌ ይኼኛው በማዕቀብ እንዳያስረው ማድረጉ ነው። ቢያንስ ወደ ግብጽና ኳታር ለመሔድ ዛሬ ዛሬ አይቸገርም። በዚህም በተቻለው መጠን ኢትዮጵያ ድኩም አገር የምትሆንበት መንገድ ይፈልጋል።

ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ

እነዚህ መቄዶኒያ መግባት ያለባቸው "ጄኔራሎች" ተኩሰው ባያዋጉም ለኢሳያስ ኤርትራ የአገርነት ምልክት ናቸው።የኤርትራ ሰዎች እነሱን ሲያዩ ኤርትራ የምትባል አገር እንዳለቻቸው ያስባሉ። "የምን ጦር ባይዋጉበትም ያስፈራሩበታል" አይደል ነገሩ። እንደ አገርማ ምን አገኙ? ከስደት ውጪ

መደምደሚያ

ባለፈው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር "ኤርትራውያን ኢትዮጵያ እንደ አገራቸው ናት" ብሎ ነበር።
ነገረኛ አባባል ነው። ኢሳያስን የሚያስደነግጥ። የኢትዮጵያ "የባሕር በር ያስፈልገኛል" ወሬ ደግሞ ሌላ እንቅልፍ የሚነሳ ጉዳይ ነው።

ገብር ብያለሁ ...ገብር!!
😂😂😂

በተከታታይ ቀናት መንግስት ያደረገላቸዉን የሰላም ጥሪ ተቀብለዉ ለገቡ 467 በላይ ለሚሆኑ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ለነበሩ ታጣቂዎች አቀባበል ተደረገላቸዉ።በሰሜን ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ ወ...
07/14/2025

በተከታታይ ቀናት መንግስት ያደረገላቸዉን የሰላም ጥሪ ተቀብለዉ ለገቡ 467 በላይ ለሚሆኑ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ለነበሩ ታጣቂዎች አቀባበል ተደረገላቸዉ።

በሰሜን ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ ወረሞ ዋጂቱ ንዑስ ወረዳ ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች በተከታታይ ቀናት የመንግስት የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ 467 በላይ ለሚሆኑ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ሀምሌ 06/2017 ዓ/ም አቀባበል ተደርጓል።

የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ማቲዎስ ማደቦ እንደተናገሩት የትም ፣መቸም ቢሆን ሰላም አሸናፊ ነው ለሰላም ቅድሚያ በመሥጠት መንግስት ያቀረበው የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ቀደመ ሰላማዊ ህይት መመለስ መቻላችሁ ብልህነት ነው ብለዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፖርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤሊያስ አበበ እንደተናገሩት ትናንት በጥፋት እና በተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ ዛሬ ላይ የሰላም ጥሪ የተቀበሉ እና ወደ ቀደመ ሰላማዊ ህይዎታቸው የተመለሱ ወንድሞቻችን የተገኘውን አንፃራዊ ሰላም ለማስቀጠል በየ ደረጃው ከሚገኘው የአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጥምረት በመሥራት የሰላም ባለቤት መሆን ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ ካሳለፍናቸው አስከፊ የሰላም እጦት ችግሮች ትምህርት በመውሰድ ለሰላም ቅድሚያ በመሥጠት የአካባቢው ማህበረሰብ ያጠውን ሰላም መልሶ እንዲያገኘ ላስቻለን እና ጫካ የነበሩ ወንድሞቻችንን በፍቅር ለተቀበሉ ጥምር ጦር ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በተደረገው የሰላም ጥሪ ከ467 በላይ የሚሆኑ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው አቀባበል የተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል። አክለውም በቀጣይ ተከታታይ ቀናቶች አጫጭር የአስተሳስብ እና አቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ ገልፀዋል።

በመርሀግብሩ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ፣ የብልፅግና ፖርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤሊያስ አበበ፣ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ማቲዎስ ማደቦ ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰይድ ኢብራሂም ጨምሮ ሌሎች የዞን፣ የወረዳ እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ተገኝተዋል።

በዛሬው ዕለት ብቻ ከተለያየ የእዝ ሰንሰለት 108 የትግራይ ሰራዊት አባላት ወደ ሓራ መሬት ተቀላቅለዋል። የትግራይ ወጣት ከባለፈው እርባና ቢስ ጦርነት ትምህርት ወስዶ ከመሞት ይልቅ መኖርን ...
07/13/2025

በዛሬው ዕለት ብቻ ከተለያየ የእዝ ሰንሰለት 108 የትግራይ ሰራዊት አባላት ወደ ሓራ መሬት ተቀላቅለዋል።

የትግራይ ወጣት ከባለፈው እርባና ቢስ ጦርነት ትምህርት ወስዶ ከመሞት ይልቅ መኖርን መርጦ እየሸሸው ይገኛል።

አስደሳች ዜና - የቀይባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ደማቅ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ አካሄደ! በዛሬው እለት በሰመራ_ሎግያ ከንቲባ ሎግያ ከተማ ደማቅ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ ያካሄደው የቀይባህር አፋር...
07/13/2025

አስደሳች ዜና - የቀይባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ደማቅ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ አካሄደ!

በዛሬው እለት በሰመራ_ሎግያ ከንቲባ ሎግያ ከተማ ደማቅ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ ያካሄደው የቀይባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ለለፈው 26 ዓመታት ከአምባገነኑ እሰያስ አፍወርቂ ጭቆናዊ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት መራር ትግል እያደረገ መምጣቱን የገለፁት የድርጅቱ ዋና ሊቀመንበር ክቡር አቶ እብራህም ሀሩን መለው የአፋር ሕዝብና የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪ አስተላለፉ።

ሀምሌ 06/2017 ሎግያ
Ibn Mohammed


አሜሪካ፣ ሩሲያ እና ፈረንሳይ የኢትዮጵያን ህጋዊ የባህር በር ጥያቄ በይፋ ደግፈዋል። እስራኤልና ቱርክ አሰብ የኢትዮጵያ ሐቅ ስለመሆኑ ለዓለም ለመመስከር ዝግጁ ነን ብለዋል። ወዳጃችን የተባበ...
07/13/2025

አሜሪካ፣ ሩሲያ እና ፈረንሳይ የኢትዮጵያን ህጋዊ የባህር በር ጥያቄ በይፋ ደግፈዋል። እስራኤልና ቱርክ አሰብ የኢትዮጵያ ሐቅ ስለመሆኑ ለዓለም ለመመስከር ዝግጁ ነን ብለዋል። ወዳጃችን የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስ ሳይመሽ ወደ ቀይ ባህር እንመርሽ ስትል ሳውዲት አረቢያ “ቅድሚያ ለድርድር” በሚል ጅዳ ላይ በዙር የሚካሄድ ድርድር አሰናድታለች...

የ “One-China Policy” አራማጇ ቻይና አሰብን መጠቅለል ለኢትዮጵያ የተፈቀደ ነው ስትል እንግሊዝ ጉዳዩን እያጤንኩት ነው ብላለች...

By any means necessary ኢትዮጵያ ወደ ህጋዊ ይዞታዋ ቀይ ባህር ትመለሳለች።



ይኸው ነው !!

Getnete Alemw

በነ ሻዕቢያ መንደር የህዝብ ማዕበል ሊውጠን ተቃርቧል የሚለው ፍራቻው  ጥግ ደርሷል። ሳዋና አደዋ ላይ አዛውንቶቹ ሻዕቢያና ተላላኪዎቻቸው  አለን ያሉትን በእገታ የያዟቸውን ታጣቂዎች  በዛሬ ...
07/12/2025

በነ ሻዕቢያ መንደር የህዝብ ማዕበል ሊውጠን ተቃርቧል የሚለው ፍራቻው ጥግ ደርሷል። ሳዋና አደዋ ላይ አዛውንቶቹ ሻዕቢያና ተላላኪዎቻቸው አለን ያሉትን በእገታ የያዟቸውን ታጣቂዎች በዛሬ እለት አስመርቀዋል።

100 የማይሞሉትን አዛውንቶቹን እነ ኢሳያስ ለ50 ዓመታት በኢትዮጵያዊያን ላይ ህዝቡን በብሔር ከፋፍለው አጨፋጭፈው በሰሩት ግፍ እርስ በእርስ መጋደል ያንገሸገሸው። ከአስመራ እስከ መንደፍራ ከመቀሌ እስከ ሞያሌ ያለ የህዝብ ማዕበል ሊውጣቸው መዘጋጀቱን ማን በነገራቸው ።

ይህ ትውልድ ከእነዚህ የማይሞቱ አዛውንቶች የዘመናት ደም መቃባት ሴራ እራሱን ነፃ ሊያወጣ ተዘጋጅቷል። በሁሉም አቅጣጫ እየመጣን ነው !

ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet

በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበሰመራ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን...
07/10/2025

በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

ሰመራ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አወል አብዱ የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸው፤ በዚህም ከዕቅድ በላይ 6 ቢሊዮን 40 ሚሊዮን 398 ሺህ 943 ብር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ወይም 46 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።

ገቢው የተሰበሰበው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክሰና ታክሰ ካልሆኑ የገቢ አርዕስት መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል።

ለበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ ክንውን ተከታታይነት ያለውና በየደረጃው ያሉ የአመራርና የዘርፉ ባለሙያዎች ቁርጠኝነት የታከለበት ስራ በመከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በበጀት ዓመቱ ደረሰኝ ካለመቁረጥ ጀምሮ በህገ ወጥነት የተሳተፉ ከ1ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ የእርምት እርምጃ መወሰዱን አቶ አወል ጠቁመዋል።

አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ጥሰቶችን በማረም ህገ ወጥነትን ወደ ህጋዊነት የመመለስ ስራዎች መከናወናቸውንም አክለዋል።

ክልሉ ካለው እምቅ አቅም ጋር የተመጣጠነ ገቢ ለመሰብሰብ በተጀመረው አዲስ በጀት ዓመት ትኩረት መሰጠቱን አስረድተዋል።



#ኢዜአ

07/10/2025

አንድ ቀበሌ አስተዳድረው፤ ፔሮል ላይ ፈርመው አያውቁም።
(አብይ አህመድ)
አንድ ቢሮ ይዤ ሳላገለግል ማለፌ ነው የሚቆጨኝ።
(ልደቱ አያሌው)

የኢትዮ-ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት 7 ቢ.  ብር ገቢ ማስመዝገቡ ተገለጸ የኢትዮ-ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት 7 ቢሊዮን  ብር ገቢማመዝገቡን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡  ...
07/07/2025

የኢትዮ-ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት 7 ቢ. ብር ገቢ ማስመዝገቡ ተገለጸ

የኢትዮ-ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት 7 ቢሊዮን ብር ገቢማመዝገቡን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ይህም ኢትዮጵያውያንና ጂቡቲያውያን የድርጅቱን ሙሉ ሥራ ተረክበው ማስተዳደር በጀመሩ 11 ወራት የተመዘገበ ውጤት መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አቶ ዓለሙ ስሜ ተናግረዋል፡፡

የበጀት ዓመቱን መዝጊያ አስመልክቶ ሚኒስትሩ ባቀረቡት ዓመታዊ ሪፖርት፣ በተለያዩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅቶች በድምሩ 13.7 ቢሊየን ብር መገኘቱን ገልጸዋል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

Address

Chicago, IL

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awusa.com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share