
06/30/2025
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ በሙሉ ጤንነት ላይ ናቸው!
ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በካርል አደባባይ አካባቢ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ቢደርስባቸውም፣ ሚኒስትሩ ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደው ተገቢውን ህክምና አግኝተዋል፡፡ አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ከተወሰነ የእረፍት ጊዜ በኋላ ወደ መደበኛ ስራቸው ይመለሳሉ፡፡
በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ መሰረተ ቢስ መረጃዎችን እንዳትመኑ፣ እውነተኛውን መረጃ ለማወቅ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን መግለጫ ይከታተሉ፡፡