Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ

  • Home
  • Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ

Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ Ethio daily is a way to get your Ethiopia-related videos to the people that matter to you. Follow us if you need hot news update

የኢራን ዲፕሎማቶች የኒውክሌር ንግግርን በድጋሚ ለማስጀመር ከአውሮፓ ባለስልጣናት ጋር ተገናኙእስራኤል ሰኔ ላይ በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ከፈፀመች ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ዲ...
26/07/2025

የኢራን ዲፕሎማቶች የኒውክሌር ንግግርን በድጋሚ ለማስጀመር ከአውሮፓ ባለስልጣናት ጋር ተገናኙ

እስራኤል ሰኔ ላይ በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ከፈፀመች ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ዲፕሎማቶች የኒውክሌር ንግግር ለማድረግ ከዩናይትድ ኪንግደም፣ ከጀርመን እና ከፈረንሳይ አቻዎቻቸው ጋር ተገናኙ።
የ12 ቀናት ጦርነት ያስነሳው እና አሜሪካ በበርካታ የኢራን የኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ የቦምብ ጥቃት እንድፈጽም ያደረገው የእስራኤል ጥቃት መከሰቱን ተከትሎ አሜሪካ እና ኢራን ሲያደርጉት የነበረው የኒውክሌር ድርድር በድንገት ተቋርጦ ነበር።
'ኢ3' በመባል የሚታወቁት በድርድሩ ላይ የተሳተፉት ሶስቱ የአውሮፓ ኃያላን ሀገራት፤ አሁን በተጀመረው የኒውክሌር ድርድር ላይ እስከ ነሐሴ ወር መጨረሻ ድረስ ምንም መሻሻል የማይታይ ከሆነ በኢራን ላይ እንደገና ማዕቀብ እንደሚጥሉ አስጠንቅቀዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ካዜም ጋሪባባዲ "ከባድ፣ ግልጽ እና ዝርዝር" ውይይት ማድረጋቸውን እና ምክክሩን ለመቀጠል መስማማታቸውን ተናግረዋል።
ጋሪባባዲ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ፤ በኢራን ላይ ማዕቀብ መጣል የሚለውን ሀሳብ መቀስቀስ "ሙሉ በሙሉ ህገወጥ" እንደሚሆን ተናግረው ነበር።

ከዚህ ቀደም በኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ተጥሎ የነበረው ማዕቀብ የተነሳው፤ በ2015 ቴህራን ከአሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ሩሲያ እና ጀርመን ጋር የኒውክሌር ስምምነት ከፈጸመች በኋላ ነበር።
ይሁን እንጂ አራን የኒውክሌር መሳሪያ ለማምረት ጥረት እያደረገች ነው መባሉን ተከትሎ ለዓመታት የዘለቀ ውጥረት ተፈጥሮ ቆይቷል። ኢራንን ይህንን ክስ አትቀበለውም። በስምምነቱ መሰረት ኢራን የኒውክሌር እንቅስቃሴዋን ለመገደብ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች እንዲገቡ ለመፍቀድ ተስማምታ ነበር።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአውሮፓውያኑ 2018 በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው ወቅት ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር ቦምብ እንዳትሰራ ለመከላከል ያደረገው አስተዋጽኦ እምብዛም ነው በማለት ሀገራቸውን ከስምምነቱ አስወጥተው ነበር።
ሁሉም የአሜሪካ ማዕቀቦች በድጋሚ በኢራን ላይ ጥለዋል።

ኢራን በበኩሏ በስምምነቱ የተጣለባትን ገደብ በመጣስ ለዚህ የአሜሪካ እርምጃ የአጸፋ ምላሽ ሰጥታለች።
ዩናይትድ ኪንግደም፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ፤ ኢራን እስከ ጥቅምት ባሉት ወራት ውስጥ የኒውክሌር ፕሮግራሟን ለመገደብ ካልተስማማች ከባድ ማዕቀቦችን በድጋሚ እንደሚጥሉ ዝተዋል።
አዲሱ ንግግር አርብ ዕለት ከጀመረ በኋላ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር፤ ኢራን የኒውክሌር ፕሮግራሟን በተመለከተ በቴክኒክ ደረጃ ውይይቶችን እንደገና ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን ጠቁማለች ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ አክለውም ኢራን ስለ ተቋማቷ እና ስለ እንቅስቃሴዎቿ ግልጽ ልትሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።
"የሚወሰዱ ጥንቃቄዎች ምን መሆን አለባቸው የሚለውን በተመለከተ ኢራንን ማዳመጥ አለብን" ብለዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋኢ፤ የኢ3 ሀገራት ስብሰባውን "የቀድሞውን ገንቢ ያልሆነ ፖሊሲያቸውን ለመካስ" ሊጠቀሙበት ይገባል ሲሉ ለሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ሶስቱም ሀገራት ሰኔ ላይ አሜሪካ እና እስራኤል ያደረሱትን ጥቃት በመደገፍ "ለህግ ጥሰት እና ጥቃት" አመክንዮ ሲሰጡ ነበር በማለት የከሰሱት ቃል አቀባዩ፤ ኢራን በአሁኑ በሚካሄደው ውይይት ላይ ይህንን ድርጊት በመቃወም አቋሟን እንደምታሳውቅ ጠቅሰዋል።
የኢራን ፓርላማ ሰኔ ላይ ከእስራኤል እና ከአሜሪካ ጋር የተፈጠረው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ተከትሎ ሀገሪቱ ከተባበሩት መንግስታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ድርጅት ጋር ያላትን ትብብር ማቋረጡ ይታወሳል።

BBC

ሩሲያ ዩክሬን ላይ ሚሳኤል አዘነበች !ሞስኮ ባልስቲክ ሚሳኤሎችን ጨምሮ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ሚሳኤሎችን በመጠቀም በዩክሬን ላይ አዲስ ጥምር ጥቃት መጀመሯ ተነገረ። ሩሲያ በ3ሰአት ው...
26/07/2025

ሩሲያ ዩክሬን ላይ ሚሳኤል አዘነበች !

ሞስኮ ባልስቲክ ሚሳኤሎችን ጨምሮ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ሚሳኤሎችን በመጠቀም በዩክሬን ላይ አዲስ ጥምር ጥቃት መጀመሯ ተነገረ።

ሩሲያ በ3ሰአት ውስጥ 208 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና 27 ሚሳኤሎችን በማስወንጨፍ ባደረገችዉ ጥቃት በዲኒፕሮ፣ ሱሚ እና ካርኪቭ ግዛቶች ላይ ከፍተኛ ጥቃት በማድረስ 14 ሰዎች ቆስለው 2 ሰዎችን መግደላቸውን የክልሉ ባለስልጣናት ገልጸዋል።

ለሶስት ሰአታት በዘለቀው 12 ኢስካንደር-ኤም ባለስቲክ ሚሳኤሎች "/KN-23 8 ኢስካንደር-ኬ የክሩዝ ሚሳኤሎች 208 ድሮኖች በተሳተፉበት የሩሲያ ጥቃት ከ20 በላይ ቦታዎች ጉዳት አድርሰዋል ። ሲል የዩክሬኑ የመንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል ።

ከእነዚህም መካከል የካርኪቭ፣ ኩፒያንስክ እና ቹቪቭ ወረዳዎች በሩሲያ ጥቃት ደርሶባቸዋል፣ በግል ቤቶች፣ በግንባታዎች፣ በመኪናዎች፣ የተመላላሽ ታካሚ ክሊኒክ እና ጂምናዚየም ላይ ጉዳት አድርሷል። ብሏል የዩክሬን ጦር ሃይል ።

የዩክሬን አየር ሃይል እንደገለፀዉ ከሆነ የጥቃቱ ዋና አቅጣጫ የዲኒፕሮፔትሮ ቭስክ ክልል ሲሆን 10 የሩስያ ሚሳኤሎች እና 25 ሰዊ አልባ አውሮፕላኖች በ9 ቦታዎች ላይ ጥቃት በመፈፀማቸዉ ተመዝግበዋል።

የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ዛሬ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ምላሽ እንደሚሰጡ የገለፁ ሲሆን ፕሬዝደንቱ በማህበራዊ ሚዲያቸው ላይ "ዛሬ ለሊት በሱሚ፣ ካርኪቭና ዲንፕሮ ግዛቶች ጨምሮ ከሩሲያ በበርካታ ቦታዎች ጥቃት ተፈፅሞብናል፡፡" ‹‹የዩክሬይን ረጅም ርቀት የሚጓዙ ድሮኖች ለዚህ በቂ መልስ ይሰጣሉ፡፡ ብለዋል ።

ስናሰናዳ ደይሊ ሜል ስካይ ኒዉስ ምንጭነት ተጠቅመናል ።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

" በደረሰዉ ድንገተኛ ቃጠሎ ምክንያት ሆስፒታሉ ሙሉ በሙሉ ስራ አቁሟል " - የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ " የጤና ባለሙያዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተረባርበዉ ተኝተዉ የሚታከሙትንና በፅኑ ...
26/07/2025

" በደረሰዉ ድንገተኛ ቃጠሎ ምክንያት ሆስፒታሉ ሙሉ በሙሉ ስራ አቁሟል " - የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ

" የጤና ባለሙያዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተረባርበዉ ተኝተዉ የሚታከሙትንና በፅኑ ሕሙማን ክፍል የነበሩትን ማትረፍ ችለዋል!! "

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ ከባድ የእሳት አደጋ እንዳጋጠመውና በቃጠሎው ምክንያት የሆስፒታሉ ዋናው የአገልግሎት ሕንፃ ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ሆስፒታሉ አገልግሎት ማቆሙን የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ዋና ሕክምናዎችና የላብራቶሪ ስራዎች ይከናወኑበት የነበረዉ ይህ G+1 ሕንፃ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረና የቀዶ ሕክምናን ጨምሮ ተኝተዉ የሚታከሙና የፅኑ ሕሙማን ክፍሎችን የያዘ የሆስፒታሉ ዋነኛ ሕንፃ እንደነበር ገልጸዋል።

ይኸው ሕንፃ ከቀኑ 8:30 አከባቢ ጀምሮ ለጊዜው መንስኤው ባልታወቀ የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት አስታውቀዋል።

የጤና ባለሙያዎችና የአከባቢው ነዋሪዎች በመረባረብ ተኝተዉ የሚታከሙትንና በፅኑ ሕሙማን ክፍል ውስጥ የነበሩ ታካሚዎችን ማትረፋቸዉን የገለፁት አቶ ፀጋዬ ቁጥርና ሁኔታዉ በደንብ የሚጣራ ቢሆንም የሆስፒታሉ ትልልቅ የሕክምና መሳሪያዎችም ጉዳት ማስተናገዳቸውን ገልፀዋል።

ይህ ቃለ ምልልስ በተካሄደበትም ሰዓት በሁለት የእሳት ማጥፊያ መኪኖች ታግዞ የእሳት ማጥፋት ርብርቡ የቀጠለ ሲሆን እሳቱ ሙሉ በሙሉ አለመጥፋቱን አቶ ፀጋዬ ኤካ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የታላቁ ኢንጂነር ሰባተኛ አመት ዝክር !!( በየኔታ ቲዩብ ታዴ የማመይ ልጅ )እለተ ሐሙስ ሐምሌ 19፣ 2010 ዓ. ም. መሃል አዲስ አበባ በሚገኘው መስቀል አደባባይ  አሳዛኝ መርዶ ሰማን የ...
26/07/2025

የታላቁ ኢንጂነር ሰባተኛ አመት ዝክር !!

( በየኔታ ቲዩብ ታዴ የማመይ ልጅ )

እለተ ሐሙስ ሐምሌ 19፣ 2010 ዓ. ም. መሃል አዲስ አበባ በሚገኘው መስቀል አደባባይ አሳዛኝ መርዶ ሰማን የኢትዮጵያ የወደፊት ተስፋ የሆነዉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በዚሁ አደባባይ ላይ መኪናቸው ውስጥ ሞተው ተገኙ መባሉን ተከትሎ መላዉን ኢትዮጵያ አዘነ ተቆጣ እንባ አራጭቶ አለፈ ትንሽ ቆይቶም ተረሳ ይህ ክስተት ከማንምና ከምንም በላይ የጎዳዉ ኢትዮጵያን ነዉ ።

የታላቁ ሰዉ ለሃገሪቱ በርካታ የግድብና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በ ኃላፊነት ለሰሩ ለ32 ዓመታት ሃገራቸዉን ያገለገሉ በተለይ ግድብ ግንባታ ጉልበታቸዉን፤ ጊዜያቸዉን፤ ገንዘባቸዉን እንደዉም ቤተሰባቸዉን ሁሉ በመተዉ ቀን ከለሊት ሲለፉ የነበሩ፤ ለሃገራቸዉ ሲሉ የተሰዉት ራሳቸዉን መስእዋትነት እስከመስጠት የደረሱት ኢንጅነር ስመኛዉ ክብር ይገባቸዋል ሁሌም ልንዘክራቸዉ ይገባል በሚል እነሆ ለዛሬው ከበዛዉ ታሪካቸው ጥቂቱን ለማነሳሳት ወደድን ።

ከአባታቸው አቶ በቀለ አይናለም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘነቡ አብተው መስከረም 3 ቀን 1957 ዓ.ም. በቀድሞው ጎንደር ልፍለ ሀገር ጠዳ ወረዳ ልዩ ስሙ ማክሰኚት ከተባለ ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንፍራንዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወልዲያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከታተላቸውን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምኅንድስና ማግኘታቸው የሕይወት ታሪካቸው ይጠቁማል።

ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ በተባለው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የታላቁ ኅዳሴ ግድብ እስከ ዕለተ-ሞታቸው በኃላፊነት ሲመሩ ቆይተዋል።

የ53 አመቱ አቶ ስመኘው ህይወታቸው እስካለፈበት ዕለት ድረስ 32 ዓመታት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንና በኢትዮጵያ ኃይል ህዝብና መንግስትን አገልግለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ኮተቤ ማሰልጠኛ ከ1978 እስከ 1991 ኢንስትራክተር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ ከ1991 እስከ 1992 ደግሞ በዋናው መስሪያ ቤት የኢንጂነሪንግ ድፓርትመንት ክፍል መሃንዲስ ሆነው ሰርተዋል፡፡

ኢንጅነር ስመኘው አገሪቱ የጀመረችውን የኃይል ልማቱ ዘርፍ በመቀላቀል ከ1992 1993 የጊቤ አንድ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ካውንተር ፓርት ኢንጅነር፣ከ1997 እስከ 2002 የጊቤ ሁለት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አስተባባሪና እና ስራ አስኪያጅ ፣እንዲሁም ከ2003 እስከ እስከ ሀምሌ 19፣ 2010 ድረስ ደግሞ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ሆነው ነብሳቸው እስኪያልፍ ድረስ በማገልገል ላይ የነበሩ እጅግ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሙህር ነበሩ።

ሰው ከቤተሰብ ርቀው፣ እንደ ሌሎች አባቶች ከልጆቻቸው ጋር ሳይጫወቱ፣ ቀዝቀዝ ባለ አየር ሳይናፍሱ አደራቸውን ለመወጣት ኳተኑ። በኢትዮጵያውያን ታምኖ ጎድሎ መገኜት ከባድ ነበርና የራሳቸውን ደስታ ወደ ጎን ትተው የአገርን ደስታ ለማስቀደም ደከሙ፡፡ ከሙያ አጋሮቻቸውና ከኢትዮጵያውያን ጋር ሆነው ከመሠረት አንስተው ሥራውን ከፍ አደረጉ፡፡

ዳሩ ግን የጀመሩትን መቋጨት አልቻሉም፡፡ ሥራውን ጨርሰው ይሞገሱበታል በተባለው አደባባይ ላይ ሕይወታቸው አልፎ ተገኙና ኢትዮጵያዊያን ደነገጡ፡፡ ሀዘኑም ከፍ አለ፡፡ ከሁሉም ግን ከጉባ በረሃ ተመልሰው ፍቅር እስኪሰጧቸው ሲጠባበቁ ለነበሩ ቤተሰቦቻቸው ሐዘኑ ከባድ ነበር፡፡ በሀሩር ሥር የተደበቀን መብራት ፈንጥቀው በጨለማ ውስጥ የኖረውን የኢትዮጵያዊ ለማስደሰት የጀመሩት ውጥን መስቀል አደባባይ ላይ ተቋጨ፡፡ ለኢትዮጵያውያንም የተጀመረ ሥራ፣ የጎመራ ፍቅር፣ የተባ አንድነት፣ ከፍ ያለ መተሳሰብ ትተው እንዲጨርሱት በመንፈስ አበርትተው በአንደበታቸው ሳይሰናበቱ ላይመለሱ አሸለቡ፡፡

የኢትዮጵያውያን ተስፋ በስሎ ሳያዩት፣ አብርቶ ሳይመለከቱት በጎን የሀገር ፍቅር፣ በጎን ደግሞ የቤተሰብ ፍቅር እንዳቃጠላቸው፤ በላይ የጉባ በረሃ እንደገረፋቸው ወደማይቀርበት ተሰናበቱ፡፡

ኢንጂነር ስመኘው ለዘመናት የተመኘነውንና የተመኙትን ፈፅመው ባያሳዩንም የማይደፈር ደፍረው፣ ያልተጀመረ አስጀምረው አጋምሰው የድካማቸውን ፍሬ ሳያዩ እስከወዲያኛው ተለዩን ።

የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲነሳ የእሳቸው ስም፣ የእሳቸው ስም ሲነሳም የህዳሴው ግድብ በመነሳቱ የሚታወቁት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ስመኘው በቀለ (ኢንጂነር)፣ ሐሙስ ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ማለዳ በመስቀል አደባባይ ሞተው መገኘትና የአማሟታቸዉ ሁኔታ ሚስጥር ሳይፈታ ሰባት አመት ሞላው ።

ታላቅ ጀግና ናቸዉና መቼም አንረሳቸዉም 🙏🙏

ቀይ ባህርን ከዚህ በኋላ እኔ እጠብቀዋለሁ !/ ግሪክ/ግሪክ ማጂክ ባህር እና ኢተርንቲቲ ሲ የተባሉ የጭነት መርከቦች በሀዉቲ ጥቃት በቀይባህር መስጠማቸዉን ተከትሎ የቀጠናውን ደህንነት ለማስከ...
26/07/2025

ቀይ ባህርን ከዚህ በኋላ እኔ እጠብቀዋለሁ !/ ግሪክ/

ግሪክ ማጂክ ባህር እና ኢተርንቲቲ ሲ የተባሉ የጭነት መርከቦች በሀዉቲ ጥቃት በቀይባህር መስጠማቸዉን ተከትሎ የቀጠናውን ደህንነት ለማስከበርና መርከቦችን ለመጠበቅ የማዳኛ መርከብ በቀይ ባህር ላይ እንደምታሰማራ ገለፀች ።

በዚህ ወር የየመን የሁቲ ታጣቂዎች በሁለት የግሪክ መርከቦች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን ተከትሎ ግሪክ በባህር ላይ አደጋዎችን ለመርዳት እና የባህር ላይ ተሳፋሪዎችን እና አለምአቀፍ መርከቦችን ለመጠበቅ የማዳኛ መርከብ በቀይ ባህር ላይ እንደምታሰማራ የመርከብ ሚኒስትሯ ገልፀዋል ።

እንደ ዘገባዉ ከሆነ ሁቲዎች ከፍልስጤማውያን ጋር ያላቸውን አጋርነት የሚያሳይ ነው ሲሉ በሚገልፁትና ከእስራኤል ጋር ግኑኝነት አላቸዉ በሚል በዚህ ወር ብቻ ሁለት የላይቤሪያ ባንዲራ ያደረጉ፣ በግሪክ የሚመሩ ማጂክ ባህር እና ኢተርንቲቲ ሲ የተባሉ የጭነት መርከቦች በየመን ማስጠሙን ተከትሎ ግሪክ ይህን ዉሳኔ ለመወሰን እንተገደደች ተገልጿል ።

የመርከብ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሲሊስ ኪኪሊያስ “ግዙፉ” ተብሎ የሚጠራው እና በሄለኒክ የቱግቦት ባለቤቶች ማህበር የቀረበው የማዳኛ መርከብ “የግሪክ ንብረት የሆኑ መርከቦችን እና የግሪክ መርከበኞችን ይደግፋሉ ፣ ይጠብቃሉ እና ይረዱታል” ብለዋል ።

ግሪክ በቀይ ባህር ለማሰማራት ያሰበችው ጂያንት መርከብ በ14 የግሪክ መርከበኞች ልዩ ባለሙያተኛ የሚተዳደር ሲሆን 16,000 የፈረስ ጉልበት ያላቸው አራት ሞተሮች ያሉት በፍለጋ እና በማዳን ስራዎች የባህር ብክለትን ለመከላከል ፣እንዲሁም የእሳት አደጋ መቋቋም የሚችልና እጅግ አስከፊ በሆነ የአየር ሁኔታ ውስጥ በመርከብ መጓዝ እንደሚችል የመርከብ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ታዴ የማመይ ልጅ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አውሮፓ በስደት ላይ ጠንካራ ርምጃ መውሰድ እንዳለባት አሳሰቡ። ለአምስት ቀናት ጉብኝት ትናንት አመሻሽ ስኮትላንድ የደረሱት ዶናልድ ትራምፕ  ለጋዜጠኞች ...
26/07/2025

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አውሮፓ በስደት ላይ ጠንካራ ርምጃ መውሰድ እንዳለባት አሳሰቡ።

ለአምስት ቀናት ጉብኝት ትናንት አመሻሽ ስኮትላንድ የደረሱት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ስደት “አውሮፓን እየገደለ ነው” ብለዋል።ስለሆነም አውሮፓ በስደት ላይ “የተሻለ እርምጃ መውሰድ አለባት ” ሲሉ ገልፀዋል።የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ብሪታንያ ባደረጉት ጉዞ ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋርም ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።ትራምፕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በስደት ላይ እርምጃች ብትወስዱ ይሻላችኋል፤ ያለዚያ ከአሁን በኋላ አውሮፓ የሚባል አህጉር አይኖራችሁም ሲሉ ተደምጠዋል። ስደት “ወረራ” ነው ያሉት ትራምፕ፤ወደ ስኮትላንድ ካመሩባቸው ጉዳዮች አንዱ ግን ፤በእናታቸው የትውልድ ቦታ በስኮትላንድ አዲስ የጎልፍ መጫወቻ ለመክፈት ነው።የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍሬዲሪሽ ሜርዝ በአሜሪካ ባደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝትም የትራምፕን አያት የትውልድ ሰርተፊኬት ለፕሬዚዳንቱ በስጦታ ማበርከታቸው ይታወሳል።ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ስልጣን ከመጡ ካለፈው ጥር ወዲህ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን እንዲታሰሩ እና ከአሜሪካ እንዲባረሩ ያደረጉ ሲሆን፤ለተለያዩ ሀገራት ዜጎችም የጉዞ እገዳ ጥለዋል።

DW

በአማራ ክልል ወረታ አካባቢ አንዲት ሴት የትራፊክ ፖሊስ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ሹፌርን ስትማታ የሚያሳይ ቪዲዬ ዛሬ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል
26/07/2025

በአማራ ክልል ወረታ አካባቢ አንዲት ሴት የትራፊክ ፖሊስ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ሹፌርን ስትማታ የሚያሳይ ቪዲዬ ዛሬ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል

26/07/2025

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ድንቅ ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው ሐምሌ 19፡፡

ቅድስት ኢየሉጣ የሮም ግዛት በሆነው አንጌቤን በሚባል ሀገር በክርስትና ሃይማኖት በበጎ ምግባር፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር ጸንታ ትኖር የነበረች ደግ ሴት ነበርች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስንም በስርዓት ነበር ያሳደገችው፡፡

በሐዋርያት ሥራ 14:21 “ወደ እግዚአብሔር መንግስት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” ተብሎ እደተጻፈ፣ ሰማዕታት ከአላውያን ነገስታት፣ ከአላውያን መኳንንት ዘንድ ስለ ሚያገኛቸው መከራ ሳይፈሩ ስለ ክርስቶስ አምላክነት መስክረው የክብር አክሊል ተቀዳጅተዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል ገና በሶስት ዓመቱ ሰማዕትነትን የተቀበለው ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ይገኙበታል፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ በዘመኑ የነበረውን አረማዊ አስተዳዳሪ እለእስክንድሮስን በመፍራት ከልጇ ጋር ወደ ጠርሴስ ብትሰደድም መኰንኑ እነርሱ የሚገኙበት ሀገር ገብቶ ክርስቲያኖችን እያሳደደ መግደል ጀመረ፡፡

የንጉሡ ወታደሮችም እግዚአብሔርን እንዲክዱ፣ ለጣዖት እንዲሰግዱ ቅድስት ኢየሉጣንና ቅዱስ ቂርቆስን አስፈራሯቸው፡፡ ቅዱሳኑ ግን በክሕደት ለመወሰድ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ በዚህም ምክንያት ጽኑ መከራ አደረሱባቸው፡፡ በጋሉ ብረቶች በመቸንከርና መላ ሰውነታቸውን በመብሳት፣ በዓይንና በአፍንጫቸው ውስጥ ጨውና ሰናፍጭ በመጨመር አሰቃዩዋቸው፡፡ በዚህ ሁሉ መከራቸው ውስጥ ግን አምላካችን እግዚአብሔር ስቃያቸው እንዳይሰማቸው ያጸናቸው ነበር፡፡ ንጉሱ ጸጉራቸውን ከነቆዳቸው በመላጨት በእሳት አቃጠላቸው፡፡ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስም ገና በሶስት ዓመቱ የሚደርስበትን ይህን መከራ በእግዚአብሔር ቸርነት ተቋቁሞ ከእናቱ ጋር በተጋድሎው ቀጠለ፡፡ በፍጹም እምነትና የሃይማኖት ፍቅር “እኔ ክርስቲያን ነኝ” እያለ ደጋግሞ ያናገር ነበር፡፡

ንጉሱም ህፃን ሳለ ይህን ያህል መጽናቱ እያስገረመው ሊያስፈራራውና ለጣኦታቱ እንዲሰግድ ሊያሳምነው ይሞክር ነበር፡፡ ሰውነታቸውን ከላይ እስከ ታች በችንካር ሲቸነክሯቸው ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል አዳናቸው፣ በመጋዝ ሰንጥቀው በብረት ምጣድ ሲቆሏቸው እግዚአብሔር ከሞት አስነሳቸውና ዳግም በገዢዎች ፊት ቆመው ስለ ክብሩ መሰከሩ፡፡ አሁንም ቀኑን ሙሉ በልዩ ልዩ የሥቃይ መሣሪያዎች ቢያስጨንቃቸውም የእግዚአብሔር ኃይልና የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት አልተለያቸውም ነበርና ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም፡፡ እንደ ገናም በመጋዝ ሰንጥቀው በብረት ምጣድ በቆሏቸው ጊዜ ጌታችን ከሞት አነሣቸውና በመኰንኑ ፊት ድንቅ ተአምራትን አደረጉ፡፡ በዚህ የተበሳጨው ንጉስም በፍጹም ተአምራት መኮንኑ ያደረገውን ጫማ ወደ በሬነት የቀየረውንና “እኔ ክርስቲያን ነኝ” እያለ የሚናገረውን ቅዱስ ሕጻን ምላሱን አስቆረጠው፡፡ እግዚአብሔር ግን በቸርነቱ አድኖለታል፡፡

በመጨረሻም በፈላ ውሃ የተሞላ ትልቅ ጋን ውስጥ ሊጨምራቸው ሲዘጋጁ እናቱ ቅስት ኢየሉጣ ፈራች፡፡ ይሁንና ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ “እናቴ ሆይ አትፍሪ ሶስቱን ሕጻናት ያደነ አምላክ ያድነናል” እያለ ያጽናናት ነበር፡፡ በዚህ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ እቶኑን ወደ ቀዝቃዛ ውሃ ቀይሮታል፡፡ ከዚህ በኋላም ብዙ ዓለማዊ ክብር እንደሚሰጧቸው ቃል ቢገቡላቸውም፣ ከክብሮች ሁሉ የሚበልጠውን የመንግስተ ሰማያት ክብር በመምረጥ በብዙ ተጋድሎና በጽኑ መከራ ውስጥ ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ቆይተው ጥር 15 ቀን በመንፈቀ ሌሊት አንገታቸውን ተቈርጠው በሰማዕትነት አርፈዋል፡፡ ዓለምን ንቀዋት የእግዚአብሔርን መንግስት አስቀድመዋል፡፡ ዛሬም በየገዳማቱ ዓለምን ንቀው የሚኖሩ መነኮሳትና ገዳማውያን በጸሎታቸው ኃይል ያደርጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

በሀዋሳ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አንድ ግለሰብ በ3 ዓመት እስራት ተቀጣበሀዋሳ ከተማ አየተከበረ ባለው ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አን...
26/07/2025

በሀዋሳ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አንድ ግለሰብ በ3 ዓመት እስራት ተቀጣ

በሀዋሳ ከተማ አየተከበረ ባለው ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በተቋቋመ ጊዜያዊ ችሎት አንድ ግለሰብ በሦስት ዓመት እስራት ተቀጣ።

ግለሰቡ ዛሬ ማለዳ ስልክ ነጥቆ ሊያመልጥ ሲል በቁጥጥር ስር መዋሉን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ኃላፊ ኢንስፔክተር ሽመልስ ብሩ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

ከንግስ በዓል ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጸጥታና ህገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልና ህግን ለማስከበር ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ጊዜያዊ የምድብ ችሎት ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በዚህም የተቋቋመው ጊዜያዊ ችሎት ግለሰቡ የፈጸመውን ወንጀል አጣርቶ የሦስት ዓመት እስራት እንደተፈረደበት ማወቅ ተችሏል።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ፌደራል ፖሊስ እና የክልል ፖሊስ በጋራ በመሆን ከአንድ ማዕከል በተሰጠ አቅጣጫ የፀጥታ ማስከበር ስራውን እየሰሩ መሆናቸውን ኢንስፔክተር ሽመልስ አስረድተዋል።

ጊዜያዊ ችሎቱም ከሌሎች አካባቢዎች የመጡ እንግዶችን ታሳቢ አድርጎ ፍትህን ለማፋጠን የተቋቋመ ስለመሆኑም ተገልጿል።

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና...
26/07/2025

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!

ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡ ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ እነሆም በፍታ የለበሰውን፣ ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ አምላካቸው ክርስቶስን አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ሐምሌ 19 ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ አዳናቸው። ቅድስት ኢየሉጣ ልጇ እንዳይገደል ለራሷም ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇ ወደ ጌታችን ሲጸልይላት ፍርሃቱ ርቆላታል፡፡ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤልም ከሰማይ ወርዶ የሚንተከተከውን ውሃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው አርባብ፣ አጋእዝት ወይም ጌቶች በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከበታቹም የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉ፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም በቈላስያስ 1÷16 በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምድር ያለውን የሚታየውንምና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” በማለት ነገደ መላዕክትን ይዘረዝራቸዋል፡፡ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ መላዕክት ማን ፈጠረን ብለው ግራ ሲጋቡ ቅዱስ ገብርኤል ፈጣሪ ነኝ ያለውን ሳጥናኤልን በመቃወም “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን ፈጥሮ አይጥለንምና አስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” በማለት አረጋግቷቸዋል፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ቪክቶር ጂዮከርስ ወደ አርሰናል ያደረገው ዝውውር ላይ  የ10ሚ.ዩሮ ተጨማሪ ክፍያዎች ዝርዝር🔸 በየ20 ጨዋታዎች (45'+)፡ €1.25M፣ እስከ €5M 🔸 ባገባቸው በየ20 ጎል   €500k እ...
25/07/2025

ቪክቶር ጂዮከርስ ወደ አርሰናል ያደረገው ዝውውር ላይ የ10ሚ.ዩሮ ተጨማሪ ክፍያዎች ዝርዝር

🔸 በየ20 ጨዋታዎች (45'+)፡ €1.25M፣ እስከ €5M

🔸 ባገባቸው በየ20 ጎል €500k እስከ €1M ገደብ።

🔸 በየወቅቱ ለቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ማጣሪያ፡ €1ሚ

(ምንጭ፡ ቤን ጃኮብስ)

Address

MD

Telephone

+12404687690

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Daily ኢትዮ ዴይሊ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share