Hiber Radio

Hiber Radio Hiber Radio , Las Vegas live every Sunday on www.hiberradio.com,Hiber Radio app or by phone 7124328451 and 24/7 you can listen

Hiber Radio , Las Vegas live every Sunday 6;30PM on www.KRLV1340AM.com, 1340 radio Channel or and 24/7 on www.hiberradio.com

ህብር ሬድዮ በአቤኔዘር ኮሙኒኬሽን ሴንተር እየተዘጋጀ ከላስ ቬጋስ ከተማ፣ ዘወትር ዕሁድ በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 6፤30 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት በ1340 ኤ.ኤም የአየር ሞገድ ወይም በድህረ ገጽ በቀጥታ በአይቱን www. KRLV1340AM.com ይደመጣል። በስልክ ለማዳመጥ ለሚቀናችሁ በቀጥታ
በአዲስ ቁጥር 712 432 8451 ያለ ኮድ በቀላሉ ማዳመጥ ይቻላል። (9፡30 በዋሽንግተን ሰዓት ) ህብር ሬዲዮ_የወቅታዊ መረጃ ምንጭ።

07/23/2025

የኦሮሞ ብልጽግና የሚባለው የአብይ ገዳይ ቡድን አፈ ቀላጤዎች አንዱ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ነው። የጀርባው የኦሮሞ ያሉት ውጭ ጉዳይ በሚባለው ጭምር ትልቅ ሚና አለው።

ዲና ይሄው ዛሬ በማርሽ ባንድ ሥጋ ቤት ያስመርቃል ። በአማራ ሕዝብ ላይ የታወጀውን ጦርነት ጨምሮ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በምክር ቤቱ የችግሮች መነሻ እኛው ነን ፣በጦርነት ችግር አይፈታም ሲሉ በአማራ ላይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊታወጅ አይገባም ባሉበት ፓርላማ የተባለው በረት ውስጥ ሲያንጓጥጣቸውና ብጤዎቹን ሲያሳድም ነበር። አብይ ጦርነቱን በአማራ ላይ ካወጀ በኋላ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የጠራው ሕገ ወጥ ስብሰባ ነበር።

ዛሬ ዲና ሙፍቲ በአጀብና በማርሽ ባንድ ሥጋ ቤት ያስመርቃል ።እነዚህ ሰዎች መሬቱ ጠቧቸዋል ጥጋቡንም አልቻሉትም ለማንኛውም ይሄ ማርሽ ባንድ የሚባላው በቅርቡ ደግሞ የቱን ባለሥልጣን ያጅብ ይሆን?

የእማራ ጠሉ ኃይል ጠበቃ እነ ልደቱ እና የአብይ ድንበር የለሽ  አማራ ጥላቻ !!ልደቱ አያሌው የትጥቅ ትግል ስለማልደግፍ ፋኖን አልቀበልም ይላል።ግን ደግሞ በህወሓት ሳንባ ዛሬም ድረስ ይተነ...
07/23/2025

የእማራ ጠሉ ኃይል ጠበቃ እነ ልደቱ እና የአብይ ድንበር የለሽ አማራ ጥላቻ !!

ልደቱ አያሌው የትጥቅ ትግል ስለማልደግፍ ፋኖን አልቀበልም ይላል።ግን ደግሞ በህወሓት ሳንባ ዛሬም ድረስ ይተነፍሳል፣ጉዳይ አስፈጻሚነቱ የአደባባይ ምስጢር ነው፣የአማራን ብሔርተኝነት ሲጠየፍና የጸረ አማራ ኃይሉን ብሔርተኝነት ደግፎ ሲቆም አይተናል (ያው አልደግፍም የሚለው ከአንገት በላይ ነው)

አብይ ግን እነ ልደቱ በጠሉት አማራነት ያሳድዳቸዋል፣ለሕወሓት ሰዎች ያለውን ርህራሄ ነፍጓቸዋል

ዴቭ ዳዊት Dave Dawit

ይህንን ጉራማይሌ በታትኖ አቅርቦታል ያንብቡት ያጋሩት(ሼር )ያድርጉት አስተያየት ስጡበት
******************

ያንን ሁሉ ወንጀል የፈፀሙ የወያኔ-ትግሬ ጄነራሎች ንብረት፥ በጦርነቱ ወቅትም ይሁን ከጦርነቱ በኋላ፥ ተጠብቆላቸው የቆየ ሲሆን፥ "የፕሪቶሪያ ስምምነት" የሚባለው ሰነድ ከተፈረመ በኋላ የፋሽስት-ወያኔ የሲቪልና ወታደራዊ ባለስልጣናት ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ንብረቶቻቸውን ከፊሎቹ ሲሸጡ ከፊሎቹ ይዞታቸውን በማጠናከር በተሻለ ዋጋ ወደ ማከራየት ገብተዋል።

ጃዋርም በድምሩ ከ150 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ሁለት ቤቶቹን በአዲስ አበባ እያከራየ ይገኛል።

በአንፃሩ ፥ በፋሽስታዊው የኦሮሙማ ሥርዓት የሚዲያ አፈቀላጤዎቹ ጥምዝ-ሀገጭ ስዩም ተሾመ፣ የኪራይ-አህ*ያ*ው ኤርምያስ ለገሠ እና ጋለሞታይቱ ቤተልሔም ታፈሰ ከተናፈሰው ጥላሸት የመቀባት ዘመቻ በቀር የትጥቅ ትግል ደጋፊ ለመሆኑ አንዳችም ማስረጃ ያልቀረበበት ልደቱ አያሌው፥ ከወላጆቹ በወረሰውና ከልጅነት እስከ ጉልምስና ዕድሜው ያሳደገው የንግድ ንብረቱ ብቻ ሳይሆን የሚኖርበት ቤት ሳይቀር በግላጭና ከዓይን ጥቅሻ በፈጠነ ቅፅበት እንዲወረስበት ተደርጎ፥ በአንድ ሌሊት ስደተኛም፣ ያጣ የነጣ ደሃም ተደርጓል።

ልደቱ ዕድሜውን የፈጀው፥ "የቤት ቀጋ፣ የውጭ አልጋ" በመሆን፣ አጉል ሚዛናዊ ለመባል፥ የአማራ ወገኑን ቁስል ለማሳነስ፥ ፈፅሞ በይዘትም በግብርም የማይስተካከሉ በኦሮሞ ወይም በትግሬ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ እዚህ ግባ የማይባሉ ችግሮችን አግዝፎ በማሳየት በአማራ ህዝብ ላይ የተፈፀመው የተራዘመ፣ ከሁለት በላይ ሥርዓቶችን የተሻገረውን ጄኖሳይድ ለማደብዘዝ ሲጋጋጥ፤ ብርሃኑ ነጋ፣ ኤፍሬም ማዴቦ፣ አንዳርጋቸው ፅጌ......ወዘተ የመሳሰሉ ፀረ-አማራ ቡድኖች በዚህ በአሜሪካ ተደራጅተውና መንጋ አደራጅተው የልደቱ የፖለቲካ ህልውናን ለመግደል ሲዘምቱ፥ የልደቱ መጠቃት ምንጩ በብሔሩ አማራዊ ነው በሚል በርካታ የአማራ ብሔርተኞች ለልደቱ ሲሟገቱና ይህንን ፀረ አማራ ስብስብ በመፋለም ከባድ ዋጋ ቢከፍሉም ቅሉ፥ ልደቱ ግን የአማራ ብሔርተኛ ወንድሞቹ ላይ በተደጋጋሚ ተረከዙን ሲያነሳ፣ ትናጋውንም ለእርግማን ሲያላቅቅ የኖረ ነበር።

የኦሮሙማው ሥርዓት የአማራ ተወላጆችን ቤትና ንብረት አፍርሶ በአንድ ሌሊት የጎዳና ተዳዳሪ አድርጎ ሲያበቃ፥ "ህጋዊ ደሃ አደረግናቸው" ብሎ የተሳለቀበት ፋሽስታዊ ድርጊት፥ በተራ ተርታው አማራዊ ላይ ብቻ ተፈፅሞ የሚቆም የመሰለው ልደቱ አያሌውን የመሰለ በአስር ሚሊየኖች የሚቆጠረው የአማራ ልሂቅ፥ ዛሬ ሀገርም፣ ቤትም ንብረትም አልባ እየሆነ፣ የዚህ ምክንያት ደግሞ ፖለቲካዊ አመለካከቱ ወይም ከሥርዓቱ ተፃራሪ ሆኖ መቆሙ ሳይሆን፥ ብሔራዊ አማራዊ ማንነቱ መሆኑ በተግባር እየታየ ነው።

አሳዛኙ ነገር፥ ከሊቀ ጳጳስ እስከ ፖለቲከኛ፣ ከባለሀብት እስከ ቴክኖክራት በዚህ አስከፊ ሥርዓት ተበዝብዞ፣ ተዋርዶና ተገድዶ የተሰደደው የአማራ ልሂቅ፥ ዛሬም የመበዝበዙ የመዋረዱና የመሳደዱ ምክንያት ብሔራዊ አማራዊ ማንነቱ መሆኑን ለማመንም ይሁን ዕውቅና ለመስጠት የሚተናነቀው፣ ይልቁንም፥ ሰሚም አድማጭም የሌለውን ለመፍትሔም የማያበቃውን የተለመደው "ኢትዮጵያ፣ በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ" የሚል ማላዘን ውስጥ እየዳከረ መገኘቱ ነው‼‼‼

ቃየንን በግፍ የፈሰሰው የወንድሙ አቤል ደም ተቅበዝባዥ እንዳደረገችው፣ ካምንም "ያፌት ይስፋ፣ በሴም ድንኳንም እግዚአብሔር ይግባ" ለተባሉት ወንድሞቹ ተገዢ እንዲሆን ያደረገው በአባቱ መነወር ያደረገው ሳቅ ፥ የአማራ ልሂቅም በግፍ ስለፈሰሰ ወገኑ ደም፣ በአመፃ ስለተበዘበዘው የአማራ ህዝብ መራቆት እያሳየ ላለው ዳተኝነት፣ የችግሩን ምንጭ በትክክል አማራዊ ከመሆን የብሔር ጥቃት አውጥቶ በሁሉም ህዝብ ላይ የተፈፀመ ተራ መንግስታዊ ጭቆና አስመስሎ ለሚሰራው በራስ ወገን ላይ ክህደት፥ እንደ ቃየን ባይቅበዘበዝ፣ እንደ ካምም ተገዢ ባይሆን ነበር የሚገርመኝ‼‼‼

አሁንም ቢሆን በህዝባችሁ ላይ ስለሚደርሰውና እየደረሰ ስላለው መከራ፥ የችግሩን ምንጭና ምንነት፥ ጭምብልና ዐይነ-ርግብ ሳታለብሱ በስሙ "በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለ ሁለገብ የዘር ፍጅት" ብላችሁ ጥሩት‼‼‼ መንግሥት መር ጄኖሳይድ በህዝባችን ላይ እየተፈፀመ፣ እናንተም የመመዝበራችሁ፣ የመሳደዳችሁ ምክንያት አማራዊ ስለሆናችሁ ብቻ እንደሆነ እውነቱን መስክሩ‼ ይህ የምስክርነት ጥሪ ለብፁዕ ወቅዱስ ሊቀጳጳስ አቡነ ጴጥሮስም ጭምር ነው‼

"ኦሮሚያ" በሚባለው ግዛት ውስጥ ጦርነት አለ፣ ሰዎችም ይገደላሉ፤ የሚገደሉት ግን በሁለት የኦሮሞ ልሂቃን ጎራ በስልጣን ሽሚያ ግብግብ በተፈጠረ ጦርነት እንጂ ሰለባዎች የሚገደሉት ኦሮሞ በመሆናቸው አይደለም። የትግሬን ጉዳይ ደጋግሜ ገልጬዋለሁ። መድገም ካስፈለገ እነሆ፦ በ rising power (ፋሽስታዊው ኦሮሙማ) እና በ established power (ፋሽስት ወያኔ) መካከል በተፈጠረ የስልጣን ማማን የመቀማማት ሂደት ውስጥ ፥ ሁለቱ ፋሽስታዊ ኃይሎች የቱሳይሳይድ-ቅርቃር ውስጥ ገቡ። ከዚህ ቅርቃር የመውጫው መንገድ ደግሞ ወይ የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት መነሻ እንደሆነው በጀርመንና እንግሊዝ መካከል እንደተደረገው የመተላለቅ ጦርነት ማድረግ ነው፣ አልያም በድህረ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት እንግሊዝ የዓለም አዛዥ ናዛዥነት ቦታዋን ለአሜሪካ በሠላም አስረክባ የአሜሪካ ታህት-አጋር (Junior Partner) ሆና የቀጠለችበትን መንገድ መምረጥ ነበር። ወያኔ የመጀመሪያውን በመምረጡ ያየነውን አይነት ጦርነት አስተናገደ። ያ ጦርነት በየትኛውም መመዘኛ ቢለካ War of Submission እንጂ War of Total Annihilation or Genocidal War አልነበረም‼‼‼

በአማራ ህዝብ ላይ የተፈፀመውና እየተፈፀመ ያለው ግን ደሃ አርሶ አደርን ከብቦ በአንድ መንደር በማረድ (በወለጋ፣ በመተከል፣ በምዕራብ ሸዋ፣ በሐረር፣ በሻሸመኔ......ወዘተ) የተፈፀመ፣ የዕለት ጉርሱን ለማግኘት አልያም ለህክምና ከአማራ ክልል በህዝብ ማመላለሻ የተጫነን ሙሉ ህዝብ አግቶ በመውሰድ መጨፍጨፍ (ባለፉት ሰባት አመታት 68 አውቶብስ ህዝብ የዚህ ድርጊት ሰለባ ሆኗል። አንድ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በአማካይ 50 ሰው ይጭናል ብንል እንኳ ፥ በዚህ መልኩ ተጨፍጭፈው የተገደሉ አማራዊያን ቁጥር 3,400 ይደርሳል) አጣዬ፣ ምድረ-ገኝ (ከኦሮሞ ወረራ በኋላ "ከሚሴ") እና መተከል ላይ የተፈፀሙ ዘግናኝ ወረራዎችና የዘር ፍጅቶች እልፍ ናቸው።

Bloody ከሆነው ጄኖሳይድ ባልተናነሰ መልኩም፥ አማራን ከንግዱ ዓለም፣ ከቤተክህነት፣ ከቢሮክራሲው ጠራርጎ ለማስወጣት የተሰራውና እየተሰራ የሚገኘው Systematic and Systemic genocide ፥ ናዚዎች በ1935 በህግ ካፀደቁት አይሁድን ከጀርመን ሲስተም የማስወጣት አካሄድ በይዘቱም በመጠኑም እጅግ የከፋ ነው‼

የአማራን ህዝብ አመናምኖ በማጥፋት የሚቀረውን እንጥፍጣፊም የአፍሪካ ጂፕሲ ለማድረግ በሰፊው እየተሰራበት ባለበት በዚህ የጨለማ ወቅት፥ የተጠቃውና እየተጠቃ ያለው አማራና አማራዊነት ነው ብሎ የማይመሰክር የአማራ ልሂቅ፥ እሱ ከጠላቶቻችን ወገን ነው‼

ዴቭ ዳዊት።

Address

Las Vegas, NV

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hiber Radio posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share