
09/27/2025
#ለጥንቃቄ
ዛሬ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው 40/60 ኮንደሚኒየም 4:30 ሰዓት ላይ በተፈጠረው የእሳት አደጋ በእግዚአብሔር ቸርነት ተርፈናል እሳቱ የተነሳው ከአንደኛ ፎቅ ከነዋሪው በቆሻሻ መልክ የሚወጡ ሃይላንድ እና አገልግሎት የማይሰጥ የቤት ቁሳቁስ እንደ ሶፋ ወንበሮች አለ አግባብ በተቀመጡ ሲሆን የአደጋውን መነሻ ለፖሊስ እንተወውና ጭሱ እስከ 18ኛ ፎቅ በመውጣት ነዋሪዎች ያፈነ ሲሆን በተለይ ህፃናት እራሳቸውን እስከመሳት አድርሷቸዋል ዛሬ ቀኑ አመት በዓል በመሆኑ ነዋሪዎች ባደረጉት እርብርቦሽ እሳቱን ተቆጥረዋል የእሳት አደጋ እና ፖሊስ አሁን በቦታ በመገኘት ጨርሶ ማጥፋት ስራ ላይ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ የጋራ መኖሪያ ኮንዶሚኒየም ተመሳሳይ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ተቀጣጣይነት ያላቸውን እቃዎች በተገቢው መልኩ ቢወገድና ክትትል ቢደረግባቸው ባይ ነኝ በተጨማሪ ይሄ አደጋ ተባብሶ ወይም የተፈጠረው ለሊት ላይ ቢሆን ኖሮ ነዋሪዎቹ የሚወጡበት የአደጋ መውጫ ባለመኖሩ አደጋውን ከባድ ያደረገው ነበር ለወደፊቱ እና በሌሎች የጋራ መኖሪያ ለጥንቃቄ ብዬ አጋራሗችሁ 🙌