Ethiopia Rising

Ethiopia Rising ጥላቻ፣ ዘውገኝነት፣ ቂ እና ጽንፈኝነት በፍቅር፣ ይቅርታ እና

 #ለጥንቃቄ ዛሬ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው 40/60 ኮንደሚኒየም 4:30 ሰዓት ላይ በተፈጠረው የእሳት አደጋ በእግዚአብሔር ቸርነት ተርፈናል እሳቱ የተነሳው ከአንደኛ ፎቅ ከነዋሪው በቆሻሻ መ...
09/27/2025

#ለጥንቃቄ
ዛሬ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው 40/60 ኮንደሚኒየም 4:30 ሰዓት ላይ በተፈጠረው የእሳት አደጋ በእግዚአብሔር ቸርነት ተርፈናል እሳቱ የተነሳው ከአንደኛ ፎቅ ከነዋሪው በቆሻሻ መልክ የሚወጡ ሃይላንድ እና አገልግሎት የማይሰጥ የቤት ቁሳቁስ እንደ ሶፋ ወንበሮች አለ አግባብ በተቀመጡ ሲሆን የአደጋውን መነሻ ለፖሊስ እንተወውና ጭሱ እስከ 18ኛ ፎቅ በመውጣት ነዋሪዎች ያፈነ ሲሆን በተለይ ህፃናት እራሳቸውን እስከመሳት አድርሷቸዋል ዛሬ ቀኑ አመት በዓል በመሆኑ ነዋሪዎች ባደረጉት እርብርቦሽ እሳቱን ተቆጥረዋል የእሳት አደጋ እና ፖሊስ አሁን በቦታ በመገኘት ጨርሶ ማጥፋት ስራ ላይ ይገኛሉ።

በተመሳሳይ የጋራ መኖሪያ ኮንዶሚኒየም ተመሳሳይ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ተቀጣጣይነት ያላቸውን እቃዎች በተገቢው መልኩ ቢወገድና ክትትል ቢደረግባቸው ባይ ነኝ በተጨማሪ ይሄ አደጋ ተባብሶ ወይም የተፈጠረው ለሊት ላይ ቢሆን ኖሮ ነዋሪዎቹ የሚወጡበት የአደጋ መውጫ ባለመኖሩ አደጋውን ከባድ ያደረገው ነበር ለወደፊቱ እና በሌሎች የጋራ መኖሪያ ለጥንቃቄ ብዬ አጋራሗችሁ 🙌

09/27/2025
09/27/2025

🚨 እባካችሁ ጓዶች፦

በዚህች እህታችን ላይ የደረሰውን ዝርዝር ከስር ባጋራሁት ቪዲዮ ላይ ሰምቼ/አይች ንዴት አንገብግቦ ሊገድለኝ ነው! 😡 ሀገርን ከሽብር እንዲጠብቅ የተሰጠውን መታወቂያ እና መሳሪያ ተጠቅሞ አንዲትን ንፁህ ዜጋ እንዲህ በአደባባይ የሚያሸብር ውርጋጥ ከየት ነው የመጣብን ጃል?!

NISS አካባቢ ያላችሁ የሀገር መከታዎች ይህን ድርጊት የመመርመር የሞራልም የህግም ግዴታ አለባችሁ። ስማችሁ እና ተቋማችሁ በአንድ ስድ ምክንያት መጥፋት የለበትም። ይህ ሰው በእርግጥም ባልደረባችሁ ከሆነ እባካችሁ ጆሮውን ይዛችሁ ለፍርድ አቅርቡልን 🙏

📍የተጠርጣሪ ስም :- ዳዊት [የአባት ስም አልታወቀም]
📍ዕድሜ፦ 34
📍የስራ መደብ፦ የፀረ-ሽብር ኢንተለጀንስ ኦፊሰር 4 (ቡድን መሪ)
📍ተጨማሪ መረጃ፦ ወለጋ የነበረ/በጉዳት የተዘዋወረ እና የዘጠኝ አመት ወንድ ልጅ ያለው።

[የግርጌ ማስታወሻ፦ እህታችን ደረሰብኝ ያለችውን በደል የምጠራጠርበት ምንም ምክንያት የለኝም። ይህ ሰው የተቋሙ አባልም ሆነ በተቋሙ አባልነት ስም የሚነግድ ወጠጤ፤ ተይዞ የእጁን ማግኘት አለበት]

09/27/2025
ሕዳሴ እያንዳንዱ አፍሪካዊ ሊጎበኘው የሚገባ ፕሮጀክት ነው - አሜሪካዊው ምሁር ላውረንስ ፍሪማን*******ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሰው ልጅ ተፈጥሮን ተጠቅሞ ለተሻለ ነገር ማዋል እንደ...
09/11/2025

ሕዳሴ እያንዳንዱ አፍሪካዊ ሊጎበኘው የሚገባ ፕሮጀክት ነው - አሜሪካዊው ምሁር ላውረንስ ፍሪማን
*******

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሰው ልጅ ተፈጥሮን ተጠቅሞ ለተሻለ ነገር ማዋል እንደሚችል ያሳየ ጥበብ ነው ሲሉ አሜሪካዊው የፖለቲካ ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን ገልጸዋል።

እስካሁን ግድቡን የጎበኙ አፍሪካውያን በጣም ጥቂት መሆናቸውን አንስተው፤ አፍሪካውያንም ሆነ አውሮፓውያን ሕዳሴውን መጎብኘት እንዳለባቸውም ነው የተናገሩት።

የአፍሪካ ሕብረት እንዲሁም መላው አፍሪካውያን አይተው ሊደነቁበት እና ለሌላ የልማት ሥራ ሊነሳሱበት የሚገባ ፕሮጀክት መሆኑንም ላውረንስ ፍሪማን አመላክተዋል።

እኔ ሁለት ጊዜ ግድቡን ለመጎብኘት በመቻሌ ዕድለኛ እንደሆንኩ ይሰማኛል ያሉት የፖለቲካ ተንታኙ፤ ሌሎችም ጎብኝተው በየዘርፋቸው ሊደግሙት የሚገባ የስኬት ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል።

እያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር የኢትዮጵያን ሞዴል በመከተል የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ፣ የማምረቻውን ዘርፍ የሚያሳድግ፣ መስኖን የሚያስፋፋ እና ድህነትን የሚያስወግድ የኃይል አቅርቦትን መገንባት ይኖርበታል ሲሉም ተናግረዋል።

የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የዚህን ግድብ ስኬት የሚያንኳስሱበት ምንም ምክንያት እንደሌላቸው ጠቁመው፤ ይህ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የውሃ ሃብት አጠቃቀም ለማሳደግ እንደሚረዳም ነው ያነሱት።

ግድቡ የመቶ ሚሊዮኖችን አፍሪካውያንን የኑሮ ደረጃ እንዴት ማሳደግ እና ድህነትን እንዴት መቀነስ እንደሚቻል ያመላከተ፤ በተጨማሪም የናይል ተፋሰስ ሀገራትን አዲስ ራዕይ ያመላከተ ግድብ ነው ሲሉም አሜሪካዊው ምሁር ላውረንስ ፍሪማን ተናግረዋል።

በጌትነት ተስፋማርያም

‹‹በህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ተደስተናል››ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ(ሀሚቲ)  የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ዋና አዛዥ የሆኑትና በቅርቡ የተመሰረተው ‹‹ሱዳን ፋውንዲንግ አሊያንስ›› የተሰኘው...
09/11/2025

‹‹በህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ተደስተናል››ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ(ሀሚቲ)

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ዋና አዛዥ የሆኑትና በቅርቡ የተመሰረተው ‹‹ሱዳን ፋውንዲንግ አሊያንስ›› የተሰኘው ትይዩ መንግስት ሊቀመንበር ሌተና ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ማክሰኞ ዕለት በተመረቀው የህዳሴ ግድብ ደስታ እንደተሰማቸው አስታወቁ፡፡

በሱዳን ፋውንዲንግ አሊያንስ ስም ዛሬ ባሰራጩት መግለጫ ‹‹የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ለአገሪቱ እድገት ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያ በራስ መተማመንና ዘላቂ ልማት ምልክትም በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንፈልጋለን›› ያሉ ሲሆን ፕሮጀክቱ የተፈጥሮ ሀብትን የመጠቀም ብሄራዊ ፍላጎትን እንደሚያንፀባርቅ አስታውቀዋል፡፡

መግለጫቸው ሲቀጥልም ‹‹ታላቁ የህዳሴ ግድብ በሁሉም የአባይ ተፋሰስ አገራት መካከል ያለብዝበዛና ያለመድልኦ ትብብር እንዲፈጠር ድልድይ ሆኖ እንደሚያገለግል ተስፋ አለን›› ያለ ሲሆን ግድቡ አፍሪካዊያን ስኬታማ ፕሮጀክትን ሰርተው የማጠናቀቅ አቅም እንዳላቸው ያሳየ መሆኑንም አስረድቷል፡፡

ጨምሮም ‹‹ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኢትዮጵያን ሀይልና የማደግ ፍላጎት የሚጨምር ብቻም ሳይሆን በቀጣናውና በመላው አፍሪካ ትብብርን፣ አብሮ መስራትንና መቀናጀትን የሚያስተዋውቅ ሆኖ አግኝተነዋል›› ሲል አስታውቋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በፖርት ሱዳን የሚገኘው በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው መንግስት ግን እስካሁን የግድቡን መመረቅ በተመለከተ ያለው ነገር አለመኖሩ ታውቋል።
Via Zehaesha

ህመሟ ሳይበግራት ሀገሯን ከፍ ያደረገቸው አትሌት 👏👏👏ሩጫ ለኢትዮጵያ ሁሉ ነገር ነው፤ ምን ያህል እንዳከበርነው ቢያጠያይቅም የብዙ መልኮቻችንን የገለጠ  ነው። እንደ ህዝብ ምን ያህል የፀናን...
09/11/2025

ህመሟ ሳይበግራት ሀገሯን ከፍ ያደረገቸው አትሌት 👏👏👏

ሩጫ ለኢትዮጵያ ሁሉ ነገር ነው፤ ምን ያህል እንዳከበርነው ቢያጠያይቅም የብዙ መልኮቻችንን የገለጠ ነው። እንደ ህዝብ ምን ያህል የፀናን ፣ ፈተናን የመወጣት አቅማችን እና ገድል የመስራት ቁርጠኝነታችንን በስፖርቱ ዘርፍ በተለይም ደግሞ በሩጫ በተለያየ መድረኮች ገልፀን አሳይተናል።

ከአበበ ቢቂላ እስከ ሀይሌ ገብረ ስላሴ ከደራርቱ ቱሉ እስከ ጥሩነሽ ዲባባ የጀግንነት መልኮቻችንን የተገለጡበት መድረኮች ብዙ ናቸው፡፡

እኤአ 2007 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ደምቀው የመታየት ቅድመ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ነበረች።

ሦስት ወርቅ አንድ ብር በማምጣት ከአለም አገራተኛ ከአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችው ኬንያን ተከትላ በማጠናቀቅ ግምቱን እውን አድርጋለች።

በኦሳካ ከተገኙት ሦስት ወርቆች ጥሩነሽ ዲባባ ያሳካችው የ10ሺ ሜትሩ የተለየ ትርጉም የተሰጠው ፅናት ካለ ምንም ነገር ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ የሆነ ነው።

ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ግምቶች ሁሉ ኢትዮጵያዊቷ እንቁ ላይ ያተኮሩ ነበሩ ፤ በርካቶች ድል እንደሚቀናት አልተጠራጠሩም።

በወቅቱ 22ኛ አመቷን ለመድፈን ሁለት ወር የቀራት ጥሩነሽ ዲባባ ብቃቷን ለዓለም ያስተዋወቀችው ኦሳካ ከመድረሷ ሦስት ዓመታት በፊት ነበር።

ብዙዎች ባዩት ነገር ተደምመው ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በአትሌትክሱ ዘርፍ ካስጠሯት አትሌቶች በተጨማሪ ሌላ ጀግና እንዳፈራች መስክረዋል።

ገና ከጅምሩ አሸናፊነቷ የታወጀላት ጥሩነሽ ዲባባ፤ ውድድሩን ከጀመረች በኃላ ክፉኛ የሆድ ህመም አጋጠማት። ሆዷን እያሻሸች ስትሮጥ በተደጋጋሚ የካሜራ እያታ ውስጥ ገብታም ነበር።

ህመሟን ችላ በመሮጥ ላይ የነበረችው ጥሩነሽ ዙሩ እየከረረ ሲመጣ አቅም ያጣች ትመስል ነበረ። አጋጣሚው ውድድሩን ሲከታተሉ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ስሜት በእጅጉ ተፈታተነ፡፡

ወበቃማ በነበረው የአየር ሁኔታ ውሀ ፍለጋ ከመስመሯ ስትወጣ ከተወዳዳሪዎቹ 30 ሜትር የሚጠጋ ራቀች፤ ያኔ ህመሙ የከፋ ደረጃ እንደደረሰ ብዙዎች ገመቱ ፤ ተስፋም ቆረጡ።

ያለችበትን ርቀት የተረዱት ተመልካቶች በየትኛው ተዓምር ነው ከዚህ ተነስታ ልታሸንፍ የምትችለው? ወርቁ ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ ማድረግ የሚችለው ማነው? የሀገሬው ስፖርት ወዳድ ሌሎች አትሌቶችን ማማተር ጀመረ።

የጥሩነሽ ታላቅ እህት እጅጋየሁ ዲባባ፣ አሃዛ ኪሮስ እና መስታወት ቱፋ ሌሎች ኢትዮጵያን የወከሉ አትሌቶች ቢሆኑም ወርቅ የማሳካት ቁመና ላይ አልነበሩም ተብሎ በብዙዎች ይገመት ነበር።

መስታወት ቱፋ ወበቁን መቋቋም ተስኗት በውድድር መቀጠል አልቻለችም። የእህቷን ህመም እያየች ስትሮጥ የነበረችው እጅጋየሁ እና አሃዛ ኪሮስ በጥሩነሽ ደረጃ የሚታይ ብቅት አላቸው ብሎ መቀበል አዳጋች ነው፡፡

ጥሩነሽ ዲባባ ለእርሷ ብቻ ሳይሆን በስፖርቱ ታሪክ ትልቅ ሙገሳ የሚያሰጥ ድል ለማግኘት ዳግም ተነሳች፤ እጅ መስጠት የኢትዮጵያውያን መገለጫ አይደለም፤ ህመም ወደ ኋላ ቢጎትታትም ተስፋ መቁረጥ የሚባል ነገር ወደ ውስጧ አልገባም።

ፈተናን ተቋቁሞ ድል ማድረግ እንደሚቻል ቀደምቶቿ ያስተማሯት ኢትዮጵያዊት ናትና፡፡ ምንም እንኳን ለብዙዎች የማይቻል ቢመስልም ቀስ በቀስ መጠጋት ጀመረች። ወደፊት ቀረበች መቅረብ ብቻ አይደለም መገስገሷን ቀጠለች።

የጥሩነሽን መምጣት የተገነዘበችው ለቱርክ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኤልባን አቢ ለገሰ አቅሟ በፈቀደ ልክ ዙሩን አከረረች፤ ነገር ግን አልተሳካላትም።

አሁን ላይ የጥሩነሽ ህመም በድል አድራጊነት ስሜት ተተክቷል፤ እግሮቿን ስታምዘገዝግ ላየ ከህመም ጋር እየታገለች መሆኗን ይጠራጠራል።

ውድድሩ ሊጠናቀቅ አንድ ዙር ሲቀረው የጥሩዬ እግሮች እንደተለመደው ማርሻቸውን ቀየሩ። ሀገር በድጋሚ ስሟ በወርቅ አሸበረቀ ባንዲራዋም ከፍ ብሎ ተውለበለበ።

ለትውልድ የሚተላለፍ አንፀባራቂ ድል አሳካች። ከውድድሩ መጠናቀቅ በኋላ ጀግኒት ይህ ሩጫ ሀገሬን ወክዬ የማልሮጠው ቢሆን አትጠራጠሩ አቋርጠው ነበር ስትልም ተናገረች።

የገጠመኝ የሆድ ህመም ከባድ ነበር፤ የቀጠልኩት ሀገሬን ወክዬ በመምጣቴ ብቻ ነው፤ መቀጠል ብቻ ሳይሆን ውድድሩን ጨርሼ ድል የማድረግ ቁርጠኝነት ያገኘሁት የሀገሬን ሰንደቅ በመያዜ ነው ስትልም ገለፃለች፡፡

"በርግጥ በማወራው ልክ ቀላል አልነበረም ትላለች ጥሩነሽ፤ እራሴን በስክሪን ተመልክቼ ከተወዳዳሪዎቹ የነበረኝን ርቀት ሳስብ ውስጤ ማቋረጥን እንደ አማራጭ አይቶም ነበር፤ ነገር ግን ሃገሬን እያሰብኩ በብርታት ቀጠልኩ።

የወከለችኝ እኮ ሀገሬ ናት፤ ወርቁን በማምጣቴ በጣም ደስተኛ ነኝ፤ እስካሁን ከገጠሙኝ ውድድሮች በጣም ፈታኙ ውድድር ይህ ነው" በማለት ፅናት ፣ ወኔ ፣ አልበገር ባይነት፣ ለፈተና እጅ አለመስጠትን፣ በአጠቃላይ ለብዙ ነገር ምሳሌ የሚሆነውን ድል ያስገኘችው ጥሩነሽ ዲባባ ከውድድሩ በኋላ ሀሳቧን በዚህ መልክ ገልፃለች።

ጥሩነሽ ዲባባ ስሟን ህያው ያደረገ ድል በጃፓን ኦሳካ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ካመጣች እንሆ 17 አመታት ተቆጥረዋል። ድሉ ጣፋጭ እና የአትሌቷን የፅናት ጥግ ያሳየ በመሆኑ ሁሌም በታሪክ ሲነሳ ይኖራል፡፡

በሸዋንግዛው ግርማ

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ  የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን...
09/10/2025

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

መልካም አዲስ አመት!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)

የ ብስራት ዜና !‎‎🌼 በአዲሱ አመት ዋዜማ ብስራቴ .🌼‎‎ ወንድም ሱሌማን አብደላ ሰላም ነው  ‎=============================‎  በርካታ ኢትዮጵውያን ወገኖቸ የህዳሴው ግድ...
09/10/2025

የ ብስራት ዜና !

‎🌼 በአዲሱ አመት ዋዜማ ብስራቴ .🌼

‎ ወንድም ሱሌማን አብደላ ሰላም ነው
‎=============================
‎ በርካታ ኢትዮጵውያን ወገኖቸ የህዳሴው ግድብ እውነተኛ ታጋይ የግብፅና የወዳጆቿ የራስ ምታት ጠላታቸው የወንድም ሱሌማን ጉዳይ እንዳሳሰባቸው የተለያየ ጥያቄ አዘል የሆነ መልዕክት አድርሰውኛል ። እነሆ በአዲስ አመት ዋዜማ ደስ የመሚለውን የመረጃ ብስራት ልንገራችሁ ።

‎ እውነት እውነት እላችኋለሁ ሱሌማን ሰላም ነው ። ሱሌማን አልታሰረም ። በአደጋ ላይም አይደለም ። ይህን የምላችሁ ትረጋጉ ዘንድ ከቶ አይደለም ። ዛሬ አነጋግሬዋለሁ ። እሱ ስራውን ሰርቶ አልፏል ። ከሳውዲ እስር ቤት በሰላም ወደ ሀገሩ ገብቶ ሰላማዊ ኑሮን እየኖረ ነው ✋።

‎ ሱሌማን ዛሬም ነገም ለሀገርና ለወገን በሰራው ስራ እናመሰግነዋለን 🙏 ይህው ነው ...

‎መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ 🌼

‎ነቢዩ ሲራክ
‎ጷግሜ 5 ቀን 2017 ዓም

ለህዳሴ ግድቡ 260 ሚ.ብር ያሰባሰቡት ኢትዮጵያዊት ባለሀብት በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ በስራ ፈጠራና በንግዱ ዓለም በስኬታማነታቸው የሚታወቁ ባለሃብት ናቸው፡፡   ወ/ሮ ጊዜሽወርቅ ተሰማ  ለታ...
09/10/2025

ለህዳሴ ግድቡ 260 ሚ.ብር ያሰባሰቡት ኢትዮጵያዊት ባለሀብት

በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ በስራ ፈጠራና በንግዱ ዓለም በስኬታማነታቸው የሚታወቁ ባለሃብት ናቸው፡፡


ወ/ሮ ጊዜሽወርቅ ተሰማ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ከግሉ ዘርፍ 260 ሚሊዮን ብር አሰባስበው ለሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ም/ቤት ገቢ በማድረግ ለሀገራቸውን ያላቸውን ፍቅር አስመስክረዋል።

በታላቁ የህዳሴ ግድብ የምረቃ በዓል ላይ ሆነን እኒህን ሃገር ወዳድ እንስት ለሃገራቸው ላከናወኑት ትልቅ ተግባር ማመስገንና ማክበር ተገቢነት አለው !!

Address

Los Angeles, CA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Rising posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share