Ethiopia Rising

Ethiopia Rising ጥላቻ፣ ዘውገኝነት፣ ቂ እና ጽንፈኝነት በፍቅር፣ ይቅርታ እና

የቀይ ባህር ዋና ዋና ጠቀሜታዎች መካከል ! አለም ያፋጠጠው ቀይ ባህር 4 ዋና ዋና አለም አቀፋዊ ጠቀሜታዎች አሉት እነሱም:-🔴 የአለም ንግድ 20% ዋንኛ መተላለፊያ አብሯ ጎዳና በመሆኑ ማን...
08/05/2025

የቀይ ባህር ዋና ዋና ጠቀሜታዎች መካከል !

አለም ያፋጠጠው ቀይ ባህር 4 ዋና ዋና አለም አቀፋዊ ጠቀሜታዎች አሉት እነሱም:-

🔴 የአለም ንግድ 20% ዋንኛ መተላለፊያ አብሯ ጎዳና በመሆኑ ማንም የሰፈር ጉልበተኛ ይሄንን ንግድና ጉዞ እንዲያስተጓጉል ስለሚፈለግ!

🔴 ከእስያ ወደ አውሮፓ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በማሳጠሩ!

(ከቻይና አውሮፓ በቀይ ባህር ጉዞ 25 ቀናት ብቻ የሚወስድ ሲሆን ይሄው ጉዞ በደቡብ አፍሪካ ቢሆን ተጨማሪ 10 ቀናት ይጨምራል)

🔴 የአለም የነዳጅ ጫኝ መርከቦች መተላለፊያና የትልልቅ ነዳጅ አምራች አገሮች የሚጋሩት ባህር መሆኑ::

🔴 አውሮፓን ከመካከለኛው ምስራቅ እና ከእስያ የሚያገናኘው የኢንተርኔት ፋይበር ኦብቲክስ በቀይ ባህር ውስጥ የተቀበረ በመሆኑ::

 🇪🇹"በበጀት አመቱ 13 አዳዲስ አውሮፕላኖችን አስገብተናል ከገቡት ውስጥ 4 ቱ ቦይንግ 3 ቱ ኤርባስ ናቸው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2017 ዓም በጀት አመ...
08/05/2025

🇪🇹

"በበጀት አመቱ 13 አዳዲስ አውሮፕላኖችን አስገብተናል ከገቡት ውስጥ 4 ቱ ቦይንግ 3 ቱ ኤርባስ ናቸው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2017 ዓም በጀት አመት እቅድ አፈጻጸሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ምን አሉ ?

" የአየር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደሩ ብዙ ክስተቶች የተመዘገቡበት አመት ነበር በተለይ መካከለኛው ምስራቅ የነበረው አለመረጋጋት፣ የሱዳን ጦርነት ፣የራሽያ እና ዩክሬን ጦርነት ፣ ዲሞክራቲክ ሪፕብሊክ ኮንጎ ጦርነት በመኖሩ በረራዎቻችን ተስተጓጉለው ነበር።

የአሜሪካ መንግስት የተለያዩ ህጎችን በማውጣቱ ምክንያት የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ እክል ፈጥሮ ቆይቷል።

በእዚህ ሁሉ ተጽዕኖ ውስጥም ቢሆን የአየር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪው በአጠቃላይ 5 ቢሊየን ደንበኞችን አጓጉዟል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጥቅሉ ሲታይ የተሻለ አፈጻጸም የነበረበት ነው ማለት ይችላል።

6 አዳዲስ መዳረሻዎችን በመክፈት አለም አቀፍ መዳረሻዎችን አስፍቷል።

እንበራለን ብለን አቅደን ከነበሩት አስመራ ፣ ፖርት ሱዳን እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ በረራችን ተስተጓጉላል።

በበጀት አመቱ 13 አዳዲስ አውሮፕላኖችን አስገብተናል ከገቡት ውስጥ 4 ቱ ቦይንግ 3 ቱ ኤርባስ ናቸው።

15.2 ሚሊየን የውጭ ደንበኞች ፣3.9 ሚሊየን የሃገር ውስጥ ደንበኞች በድምሩ 19 ሚሊየን ደንበኛች አጓጉዘናል።

785,323 ቶን ካርጎ ጭነት አጓጉዘናል።

አየር መንገዱ በበጀት አመቱ 7.6 ቢሊየን ዶላር ገቢ አግኝቷል ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 8 በመቶ ብልጫ አለው " ብለዋል።

አውሮፕላን ጣቢያ ለወልዲያና አካባቢውበፌድራል ትራንሰፖርትና ሎጂስትክ ሚኒስተር መሪ ዕቅድ መሠረት በቅርቡ መገንባት አለባቸው ተብለው ከሚጠበቁ የአውሮፕላን ጣቢያዎች መካከል ወልዲያና አካባቢው...
08/04/2025

አውሮፕላን ጣቢያ ለወልዲያና አካባቢው

በፌድራል ትራንሰፖርትና ሎጂስትክ ሚኒስተር መሪ ዕቅድ መሠረት በቅርቡ መገንባት አለባቸው ተብለው ከሚጠበቁ የአውሮፕላን ጣቢያዎች መካከል ወልዲያና አካባቢውን የሚያስተናግደው ጣቢያ ቀዳሚው ነው። ነገር ግን እስካሁን ግንባታውን ለማስጀመር ምንም ዓይነት ምልክት የለም። ከበጀት እጥረት ወይስ ሌላ ፍላጎት እንደሆነ ግልጽ አይደለም።

አውሮፕላን ጣቢያ የሚገነባው ከአትራፊነት አንጻር ከሆነ ከወልዲያና አካባቢው በላይ ተመራጭ ማን ሊሆን ይችላል?

👉 በዛሬው የብር ዋጋ ቢተመን በቢሊዮን ብሮች ወጭ ተደርጎ በወልዲያ ከተማ የተገነባው ዓለም አቀፍ ስታዲዬም ፤ በ2029(ጊዜውን እርግጠኛ ባልሆንም) ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ አገልግሎት እንዲሠጥ ከተፈለገ የአውሮፕላን ጣቢያው አሁኑኑ ግንባታው መጀመር ይገባዋል። መቼም የአዘጋጅነቱን ጥያቄ አገራችን ያቀረበችው እንደ ወልዲያው ዓይነት ስቲዲየምን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ ግልጽ ነው።

👉 ብዙዎች ስለ ወልዲያ ሲያስቡ የሚታያቸው የሰሜን ወሎ ዞን ብቻ ነው። ነገር ግን ወልዲያና አካባቢው ላይ የሚገነባው አውሮፕላን አገልግሎት የሚሠጠው ለምዕራባዊ የአፋር ክልል እና ለደቡባዊ የትግራይ አካባቢዎች ጭምር እንዲሁም ለደቡብ ወሎና ዋግኽምራ ዞኖች በከፊል ነው። ለምሳሌ

ከአፋር ክልል አካባቢወች ብንወስድ
👉 ጭፍራ
👉 ቴሩ
👉 እዋ
👉 ያሎ ወረዳ ወ.ዘ.ተ.
ከትግራይ ክልል አካባቢወች ብንወስድ
👉 ማይጨው
👉 መሆኒ
👉 እንዳ መሆኒ
👉 ራያ አዘቦ
ከሰሜን ወሎ ዞን ብንወስድ
👉 ራያ አላማጣ ወረዳ
👉 ባላ ወረዳ
👉 አላማጣ፣ ዋጃ፣ ጥሙጋ፣ ባላ ከተሞች
👉 ራያ ቆቦ ወረዳ
👉 ቆቦ፣ ሮቢት፣ ጎብዬ ወዘተ ከተሞች
👉 ጉባላፍቶ ወረዳ
👉 ሐራ፣ ሳንቃ ከተሞች
👉 ሀብሩ ወረዳ
👉 መርሳ፣ ሲሪንቃ፣ ውርጌሳ፣ ድሬሮቃ፣ ጊራና ወዘተ
👉 ግዳን ወረዳ
👉 ሙጃ፣ ዴንሳ፣ ወንዳች፣ አስቂት ወዘተ ከተሞች
👉 አንጎት ወረዳ
👉 አሁን ተገኝ፣ ቀበሮ ሜዳ ወዘተ ከተሞች
👉 ጋዞ ወረዳ
👉 ስታይሽና ወዘተ ከተሞች
👉 ሌሎቹ ለላልይበላ ይቀርባሉ በሚል ነው

ከዋግ ኸምራ ዞን ብንወስድ
👉 ወፍላ ወረዳ
👉 ኮረም ከተማ
👉 ዛታ ወረዳ ወዘተ አካባቢዎች
👉 ሌሎቹ ለላልይበላ ይቀርባሉ በሚል ነው

ከደቡብ ወሎ ዞን ብንወስድ
👉 አምባሰል ወረዳ
👉 ውጫሌና ጢስአባሊማ ከተሞች
👉 ሌሎቹ ለኮምቦልቻ ይቀርባሉ በሚል ነው

👉 ከየትኛውም አካባቢ በላይ የማዳም ቅመምች የሚባሉትን😂 ወደ መካከለኛው ምስራቅ በመላክ እና ከፍተኛ የሆነ የሰው ፍሰት ያለበት አካባቢ ነው። በተጠቀሱት አካባቢዎች በእያንዳንዱ ቤተሠብ ውስጥ ከ 1-2 ሰው በአማካይ የቤተሠብ አባሉ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ያልሄደበት ሰው የለም። በዚህ ምክንያት በከፍተኛ ደረጃ የአየር ትራንስፖርትን የሚጠቀም አካባቢ ነው። አውሮፕላን ጣቢያው ቢከፈት በአንጻራዊነት ከቀድሞዎቹ በላይ ከፍተኛ የተጠቃሚ ፍሰት እንደሚያገኝ በቅደመ ዳሰሳ ጥናት ማረጋገጥ ይቻላል።

👉 ያለፉትን 7 ዓመታት የአገራችንን ሁኔታ ስናስተውል ከአገር ደህንነትም አንጻር ወልዲያ ከተማ የነበራትን ቀጠናዊ ማዕከልነት ታሳቢ በማድረግ ብቻ ሎጂስቲክና የሰው ሀይልን በፍጥነት ለማጎጓዝ፣ ከሰሜን ምስራቅ ወደ ሰሜን ምዕራብ ለመተላለፍ በወልዲያና አካባቢው የአውሮፕላን ጣቢያ አስፈላጊነቱ ጥያቄ ውስጥ አይገባም።

👉 አካባቢው ከፍተኛ የእንሰሳት ሀብት ያለበት ቀጠና በመሆኑ እና በተለይ በእርባታና ማድለብ ለሚሰማሩ አልሚወች እሴት በመጨመር የእንሰሳት ስጋን አርዶና አሽጎ ወደ መካከለኛው ምስራቅና ጎረቤት አገራት በፍጥነት ለማድረስ የአውሮፕላን ጣቢያው መከፈት አይነተኛ ሚና ይኖረዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ኢንቨስተሮችንም ለመሳብ ሰበብ ይሆናል።

እንዲሁም ሌሎች አስረጂ ምክንያቶችን በጥናት አስደግፎ ማቅረብ ይቻላል።







የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሩሲያ አውሮፕላኖችን ሊያከራይ ነውየአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ማዕቀብ ምክንያት የአቪዬሽን ችግር ለገጠማ...
08/04/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሩሲያ አውሮፕላኖችን ሊያከራይ ነው

የአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ማዕቀብ ምክንያት የአቪዬሽን ችግር ለገጠማት ሩሲያ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በኪራይ ለማቅረብ ውይይት እያደረገ ነው።

ባለፈው ወር በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ባለስልጣናት መካከል በተደረገ ስብሰባ ላይ፣ የሁለቱ ሀገራት የአቪዬሽን ትብብር እንዲስፋፋ ፍላጎት መኖሩ ተገልጿል። ከውይይቱ ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ለሩሲያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖችን በ"ዌት ሊዝ" (wet-lease) ስምምነት ማከራየት አንዱ ነበር።

ይህ የኪራይ ስምምነት፣ ኢትዮጵያ አውሮፕላኑን፣ የበረራ ሰራተኞችን፣ ጥገና እና ኢንሹራንስን ጨምሮ ሁሉንም ነገር ለሩሲያ የምታቀርብበት ሲሆን፣ ሩሲያ ደግሞ ለነዳጅ እና ለሌሎች ወጪዎች ብቻ ኃላፊነት የምትወስድበት ነው።

ሩሲያ ይህንን አማራጭ የምትፈልገው በምዕራባውያን ማዕቀቦች ምክንያት አዲስ አውሮፕላኖችን ወይም ለመለዋወጫ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ማግኘት ስለተቸገረች ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ120 በላይ ዘመናዊ አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን፣ ይህም የሩሲያን ፍላጎት ለማሟላት እንደሚያስችል የሲምፕል ፍላይት መረጃ ያሳያል።

ምንም እንኳን የውሉ ዝርዝር ጉዳዮች ይፋ ባይሆኑም፣ የሩሲያ መንግስት አየር መንገዶቹ ከውጭ ሀገራት አውሮፕላኖችን በኪራይ እንዲጠቀሙ መፍቀዱ ለዚህ ውይይት አዎንታዊ ምላሽ ሊሰጠው ይችላል ተብሎ ይታሰባል ሲል ካፒታል አስነብቧል።

የጠ/ሚ አክሊሉ ኃብተወልድ የ60 አመት ትዝታዬ !የዛሬ 60 አመት ገደማ አንድ አሜሪካዊ የፒስኮር ኮበሌ ወደ 20 ገደማ የምንሆን ተማሪዎች ካምፕ ላንጋኖ በሚል መጠሪያ ላንጋኖ ሀይቅ ዳርቻ በ...
08/04/2025

የጠ/ሚ አክሊሉ ኃብተወልድ የ60 አመት ትዝታዬ !

የዛሬ 60 አመት ገደማ አንድ አሜሪካዊ የፒስኮር ኮበሌ ወደ 20 ገደማ የምንሆን ተማሪዎች ካምፕ ላንጋኖ በሚል መጠሪያ ላንጋኖ ሀይቅ ዳርቻ በድንኳኖች አስፍሮን ነበር።

ምግባችን ነጋም ጠባም ፉርኖና ፓስታ በመሆኑ የሰለቸን ተሰባስበን ወደ ቅርብ የሆነችው ከተማ ቡልቡላ ሄደን የበግ ጥብሳችንን በእንጀራ እንክት አድርገን ስንመለስ በርቀት ይታየን የነበረውን ሻላን እግረ መንገዳችንን ለመጎብኘት ወሰን። እየተቃረብም ስንሄድ አንድ ብቸኛ ቆብ ያደረገና ያሳ ማውጫ ዘርግቶ ፒፓ የሚያጨስ ሰው አየን።

ከሩቁ ፈረንጅ መስሎን ነበር። ቀርበን ስናይ ጠሚ አክሊሉ መሆናቸውን አየን። ሰላምታ ተቀያየርንና መጀመሪያ ስለ አሳ ማስገር ተወያየን። የማስታውሰው አሳ ማጥመድ አሰልቺና ጊዜ አባካኝ ቢመስልም ከራስ ጋር መመካከሪያና የማሰቢያ ጊዜ ነው አሉን። ፒፖ ማጨሱስ ስንላቸው ሁሉ ነገር በመጠኑ ጠቃሚ ነው ሲበዛ ግን በሽታ ነው አሉን።

እየተለማመድን ስንሄድ አገራችንኮ በተለይ ፊውዳሊዝም አያዋጣም መቀየር አለበት ምን ይላሉ ስንላቸው እሱ በሂደት አይቀርም ነገር ግን በመንግሥት ግልበጣ ሳይሆን በምክክር ቢሆን ዘላቂ ይሆናል አሉን።

ጠሚ አክሊሉ ኃብተወልድና ወንድሞቻቸው የዘመናዊ ኢትዮጵያ መስራቾችና ባለውለታዎች ነበሩ። ሰብአዊነት ቢኖራቸውም ዝግመት ነበራቸው። ሰው በላው ደርግ በእናት አይምሬው ገዳይ ጥቁሩ ሙሶሊኒ መንግሥቱ ኃይለማሪያም እኛን ለማታለል “ያለ ምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም” እያለ እያስደለቀ ለውጥ ቢጀምርም አራጅ በመሆኑ ካለ ፍርድ እነ ጠሚ አክሊሉን 60ዎቹ በሚባል የሚታወቁትን ያገር አባቶች ረሽኖ ባንድ ጉርጓድ ቀበራቸው።

ሌባውና ወራዳው መንግሥቱ አገራችን መሪ በነበረበት ዘመን የድሀውን ሀብት በመዝረፍ ዚምባብዌ ርስትና ንብረት ሲያካብት ኖሮ ግብረ አበሮቹን እንኳን ሳይሰናበት በሌሊት ወደ ንብረቱ ሸሽቷል። ፈጣሪ ይፍረደው። የጠሚ አክሊሉንና አብረው የተረሸኑት ሰማእታትን ነፍስ ቸሩ ፈጣሪ ይማርልን።

Via : Abebe Haregewoin (PhD)

የጂጂ ኢትዮጵያ እንዴት ያለች ናት?የአርሲ ነገሌው ወጣት ደራሲ ቢንያም አቡራ በእጅጋዬሁ ሙዚቃዎች ዙሪያ በፃፈው " ባለቅኔዋ ሶሪት " "ጂጂን እንደተረዳሁዋት" የተሰኘው መፅሐፍ ላይ ውይይት ...
08/04/2025

የጂጂ ኢትዮጵያ እንዴት ያለች ናት?

የአርሲ ነገሌው ወጣት ደራሲ ቢንያም አቡራ በእጅጋዬሁ ሙዚቃዎች ዙሪያ በፃፈው " ባለቅኔዋ ሶሪት " "ጂጂን እንደተረዳሁዋት" የተሰኘው መፅሐፍ ላይ ውይይት በማድረግ አምሽተናል::

ግሩም ድንቅ የሆነውን ትንታኔውን በ3 ከፍሎታል

1ኛ. የጂጂ ኢትዮጵያ

2ኛ. የጂጂ እግዜር

3ኛ. ፍቅር በጂጂ ቋንቋ

ፍሬአለም ሺባባው

በሚል በጣም አስደናቂ ትንታኔ ሰጥቶበታል::

ስንወያይም ቢንያም አቡራ በጣም ትልቅ አሳቢ መሆኑን እና የሷን ግጥሞች እንዴት ከታሪክ እና ከስነ ፅሁፍ ውበት አንፃር ከፍ ያለ ደረጃ እናዳለው ገልፆልን በሀሳብ ባህር ዋኝተናል::

ቢኒያም ስለ ድንቅ ትንታኔህ በእጅጋዬሁ እና በራሴ ስም እጅግ በጣም አመስግናለሁ:: ተገርሜአለሁ:: ምሽቱ ላይ ተገኝታችሁ ድንቅ ሀሳብ ያካፈላችሁን ወጣቶች ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ.

እናንተም በእነዚህ ጉዳዮች ላይ የራሳችሁ ሃሳብ ይኖራችሁዋል ብዬ አሰብኩኝ::

የጂጂ ኢትዮጵያ እንዴት ያለች ናት?

ምን ትላላችሁ?

ኡስታዝ ጀማል ማለት ምስጋናና ሹመትን ሳይጠብቅ፣ አጨብጭቡልን ሳይል እንዲሁ ግዴታዬ ነው ብሎ ለሀገሩ ዘብ ከመቆም ሰንፎ የማያውቅ ጀግና፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።Ustath Jemal...
08/03/2025

ኡስታዝ ጀማል ማለት ምስጋናና ሹመትን ሳይጠብቅ፣ አጨብጭቡልን ሳይል እንዲሁ ግዴታዬ ነው ብሎ ለሀገሩ ዘብ ከመቆም ሰንፎ የማያውቅ ጀግና፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
Ustath Jemal Beshir Ahmedን የምትወዱት እስኪ እንያችሁ?

  ወንድም ማርሎን ጃክሰን በመቀሌ አንዲት ውብ ሕፃን አቅፎ-ሐምሌ 1977 ዓ.ም
08/03/2025

ወንድም ማርሎን ጃክሰን በመቀሌ አንዲት ውብ ሕፃን አቅፎ-ሐምሌ 1977 ዓ.ም

"ሁሉን ነገር መፈለግ፣ ሁሉን መሻት፣ ያለገደብ ለመኖር ማሰብ የዚህ ዓለም ጣጣ፣ የድካም ምንጭ ነው። የምትጠቀምበትን ያክል ብቻ እወቅ፤ የሚያጠግብህን ያክል ብቻ ብላ፤ የሚያረካህን ያክል ብቻ...
08/03/2025

"ሁሉን ነገር መፈለግ፣ ሁሉን መሻት፣ ያለገደብ ለመኖር ማሰብ የዚህ ዓለም ጣጣ፣ የድካም ምንጭ ነው። የምትጠቀምበትን ያክል ብቻ እወቅ፤ የሚያጠግብህን ያክል ብቻ ብላ፤ የሚያረካህን ያክል ብቻ ጠጣ፤ ሁሉን ነገር ማጣት ሰቀቀን ቢሆንም ሁሉን ነገር ማግኘትም ዕዳ ይሆናል፡፡ ምንም አለማወቅ ባዶነት ቢሆንም ሁሉን ማወቅ ደግሞ ሸክምም ይሆናል።"

ምንጭ ፡- ዝጎራ በ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ

Best picture
08/03/2025

Best picture

“ኢትዮጵያ በቀጣይ በዓባይ ወንዝ ላይ ለመስራት ያቀደችውን የመንዳያ ግድብ ግብፅ በሙሉ ባለቤትነት በመገንባት ውሃውን ታስተዳድረው” — ግብጻዊ ተንታኝ  🇪🇹🤝🇪🇬በመጪው ዓመት ኢትዮጵያ በታላቁ...
08/03/2025

“ኢትዮጵያ በቀጣይ በዓባይ ወንዝ ላይ ለመስራት ያቀደችውን የመንዳያ ግድብ ግብፅ በሙሉ ባለቤትነት በመገንባት ውሃውን ታስተዳድረው” — ግብጻዊ ተንታኝ

🇪🇹🤝🇪🇬

በመጪው ዓመት ኢትዮጵያ በታላቁ የዓባይ ወንዟ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት በይፋ ታስጀምራለች። በመስከረም ወር መጨረሻ ሰኞ የምርቃት ሥነስርዓቱ የሚከናወነው የህዳሴ ግድብ fait accompli በመሆኑ የሚይዙት የሚጨብጡት የጠፋቸው ወደረኞቻችን ከተለመደ እብሪታቸው አንድ ደረጃ ዝቅ ብለው የመፍትሔ ሃሳብ የሚሉትን አማራጭ ይዘው ብቅ ብለዋል — በህዳሴ ግድብ እራስጌ ኢትዮጵያ በቀጣይ የምትገነባውንና ከ 40 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውሃ የሚይዘውን የመንዳያ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በእራሷ ሙሉ ወጭ በመገንባት የውሃ አጠቃቀሙን ትወስንበት የሚል !!

ዶክተር ሞሐመድ ሀፊዝ የተባለ ተንታኝ “ግብፅ ኢትዮጵያ ውስጥ በዓባይ ወንዝ ላይ የመንዳያ ግድብን በእራሷ ሙሉ ወጭ በመገንባት ግድቡን ልክ እንደ አስዋን ግድብ የግብጽ የውሃ ማጠራቀሚያ ሆኖ እንዲያገለግልና የውሃ ፍላጎቷ ከፍ ሲል በእራሷ ፍላጎት ልትለቀው ትችላለች...” ሲል ያትታል። በእሱ ሃሳብ ከህዳሴ እራስጌ የሚሰራውን የመንዳያ ግድብን የውሃ ፍሰት ግብፅ ተቆጣጠረች ማለት በተዘዋዋሪ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ በቀጣይ በዓባይ ወንዝ ላይ የሚሰሩትን ግድቦች በጥቅሉ የዓባይ ወንዝን ተቆጣጠረች¹ ማለት ነው። የዶክተር ሞሐመድ ሀፊዝ ምኞት ከንቱ ቅዠት ቢሆንም ቅሉ የግብጻውያን እብሪት በሂደት እየበረደ ስለመምጣቱ ወሳኝ ማሳያ ሆኖ ያገለግላል።

ኢትዮጵያ በቀጣይ በዓባይ ወንዝ ላይ የመንዳያ እንዲሁም በጊቤ ወንዝ ላይ የጊቤ ፭ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቦችን በይፋ ታስጀምራለች። ለግድቦቹ ግንባታ የሚውል አስተማማኝ ፋይናንስ ተገኝቷል። የማቢል ግድብ በዚህ ዙር የመካተት እድል ሊኖረው እንደሚችል አንዳንድ ምንጮቼ ጠቁመዋል።

¹- ከህዳሴ ግድብ ግርጌ በጋራ ፋይናንስ የሚደረግ ግድብ ወሳኝና ጠቃሚ ነው።

ብዙ ሽልማቶችን በማግኘት በአፍሪካ ብቸኛው ሰዉ !ክብር ለሚገባቸው 🙏‎‎"የአፄ ቴዎድሮስን ታሪክ ወደ ፊልም እስክሪፕት ቀየርኩና ፕሮዲዩስ እንዲደረግ ወደ ሆሊውድ ሄድኩ። አንድ ፕሮዲዩሰር ታሪ...
08/03/2025

ብዙ ሽልማቶችን በማግኘት በአፍሪካ ብቸኛው ሰዉ !

ክብር ለሚገባቸው 🙏

‎"የአፄ ቴዎድሮስን ታሪክ ወደ ፊልም እስክሪፕት ቀየርኩና ፕሮዲዩስ እንዲደረግ ወደ ሆሊውድ ሄድኩ። አንድ ፕሮዲዩሰር ታሪኩን አንብቦ ወደደውና 'ለምን ዋና ታሪኩን ቴዎድሮስን ሊረዳ በመጣው ፈረንጅ ዙርያ እንዲያጠነጥን አናደርገውም?' አለኝ። እኔም እስክሪፕቱን ተቀብዬው ወጣሁ። ከዚያ በኋላ የሆሊውድን ደጅ ረግጬ አላውቅም!"

‎ፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ

‎አንድ አንድ ሰው ርዕዮተዓለም፣ ትውልድ፣ ዘመን፣ ማንነት፣ ወዘተረፈ የተሻገረ ስብዕና አለው። ከስንት አንድ እንደሚገኝ ዘመን አይሽሬ የኪነ ጥበብ ሥራ ዘመንም ትውልድም የሚሻገር ክላሲካል። አዎ እንደ ፕሮፌሰር ሐይሌ ገሪማ ያለ። ሶስት አራት ትውልድ የተሻገረ አገልጋይነት ዛሬም ድረስ የሌላ ሀገር ዜግነት ላለመቀበል የወሰነ የሃገር ፍቅር።

‎ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ በሰሯቸ ስራዎች በርካታ አለምአቀፋዊ ሽልማቶች የተቀዳጁ ሲሆን

‎• 2009 - Teza Over the course of his career, Gerima has received numerous awards and distinctions in film festivals

‎• 1982 - Grand Prix Award for Ashes and Embers-Lisbon International Film Festival

‎• 1983 - FIPRESCI Film Critics Award for Ashes and Embers-Berlin International Film Festival

‎• Outstanding Production Ashes and Embers - London Film Festival

‎• 1984 - Tribute Festival De la Rochelle, France

‎• 1987 - Long Metrage De Fiction-Prix de la Ville de Alger for Ashes and Embers

‎• 1993 - Best Cinematography Award for Sankofa, FESPACO, Burkina Faso

‎• 2003 - Lifetime Achievement Award, 4th Annual Independence Film Festival, Washington D.C.

‎• 2006 - Festival De Cannes Selection Official Cannes Classic -Harvest: 3,000 Years

‎• 2008 - Venice Film Festival Special Jury Prize and Best Screen Play Award - Teza

‎• 2009 - Jury Award at the 18th International Film Festival Innsbruck/Austria - Teza

‎• 2009 - Golden Stallion of Yennenga at the FESPACO African Film Festival -

‎• 2009 - Dioraphte Award Hubert Bals film in highest audience regard at the Rotterdam Film Festival

‎• 2009 - Golden Tanit/Best Film Award for its "modesty and genius," Best Music (Jorga Mesfin Vijay Ayers), Best Cinematography (Mario Massini), Best Screenplay (Haile Gerima), Best Supporting Actor Abeye Tedla at the Carthage/Tunisia Film Festival በ Teza

‎• 2009 - Golden Unicorn and Best Feature Film at the Amiens/France International Film Festival France በ Teza

‎• 2009 -The Human Value's Award at the Thessaloniki Film Festival in Greece በጤዛ Teza

‎• 2009 - Official Selection at the Toronto Film Festival በ Teza ፊልም በእጩነት ከመቅረባቸዉ በላይ በርካታ ሽልማቶችን በማግኘት በአፍሪካ ብቸኛ ሰዉ ናቸዉ።

Address

Los Angeles, CA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Rising posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share