Ethiopia Rising

Ethiopia Rising ጥላቻ፣ ዘውገኝነት፣ ቂ እና ጽንፈኝነት በፍቅር፣ ይቅርታ እና

ሮናልዶ እና ሜሲ የተካተቱበት የፊፍፕሮ የዓመቱ ምርጥ 11 ዕጩዎች የዓለም አቀፉ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ 11 ተጫዋቾች ዕጩዎች ይፋ ሆነዋል።26 ተጫ...
10/27/2025

ሮናልዶ እና ሜሲ የተካተቱበት የፊፍፕሮ የዓመቱ ምርጥ 11 ዕጩዎች

የዓለም አቀፉ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ 11 ተጫዋቾች ዕጩዎች ይፋ ሆነዋል።

26 ተጫዋቾች በዕጩነት በቀረቡበት የ2025 ምርጫ የአል ናስሩ አጥቂ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና የኢንተር ማያሚው አማካይ ሊዮኔል ሜሲ የተካተቱ ሆነዋል።

ፒኤሲጅ በርከታ ተጫዋቾችን በዕጩነት በማስመረጥ ቀዳሚው ሆኗል። የባሎን ዶር አሸናፊው ኡስማን ደምቤሌን ጨምሮ ጃኦ ኔቬስ፣ አችራፍ ሃኪሚ እና ኑኖ ሜንዴዝ ከተመረጡት መካከል ናቸው።

የአርሰናሉ ዊሊያም ሳሊባ፣ የሊቨርፑሉቹ ሙሀመድ ሳላ እና አሊሰን፣ የማድሪዱ ኬይሊያን ምባፔን ጨምሮ ሃለንድ፣ ላሚን ያማል እነወዲሁም ጁድ ቢሊንግሀም እና ኮል ፓልመር በዕጩነት ከቀረቡት መካከል ናቸው።

በ2005 መካሄድ የጀመረው የፊፍፕሮ ምርጥ 11 ሽልማት በዚህ ዓመት ለ21ኛ ጊዜ የሚደረግ ይሆናል።

የ8 ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊው ሊዮኔል ሜሲ 17 ጊዜ ምርጥ 11 ውስጥ በመግባት ቀዳሚው ተጫዋች ነው።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ 15 ጊዜ በመመረጥ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ሀገር የመገንጠል አጀንዳ ይዘው የኖሩ ፖለቲከኞች ግባቸው ምንድነው? ከልብ ያምኑበታል? ከልብ እንዲያምኑበት ያደረጋቸው ምክንያት ብየ ራሴን ጠየኩት። አሳማኝ ነገር ፈልጌ አጣሁኝ።እነሱ እንደሚ...
10/27/2025

ሀገር የመገንጠል አጀንዳ ይዘው የኖሩ ፖለቲከኞች ግባቸው ምንድነው? ከልብ ያምኑበታል? ከልብ እንዲያምኑበት ያደረጋቸው ምክንያት ብየ ራሴን ጠየኩት። አሳማኝ ነገር ፈልጌ አጣሁኝ።

እነሱ እንደሚሉት የኢትዮጵያ ሁሉም ክልሎች ሀገር ቢሆኑ ብዬ ሳስበው እንደ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያለን ተፅዕኖ ይቅርና በምስራቅ አፍሪካ ከጅቡቲና ከሶማሌ ላንድ የተሻለ ተፅዕኖ የማይኖረን ማንም ጆሮ የማይሰጠን ተሰሚነት የሌለን ኩታንኩት ሀገሮች ሆነን አገኘሁት።

እንደ ሲንጋፖር ( መከረኛዋ ሲንጋፖር 😁) በኢኮኖሚ ያደግን የበለፀግን እንሆናለን እያለ ገንጣይ አስገንጣይ የሚያወራው ሁሉ ከእነሱ አፍ በላይ የማይሻገር ተረት ነው።

ማንም ዞር ብሎ የማያያቸው ኩታንኩት ሀገሮች ሆነን ነው የምንቀረው። የአንድን ሀገር የገበያ ተፈላጊነት ከፍ በማድረግ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ተመራጭ ለመሆንና የፖለቲካ ተፅዕኖ ተሰሚ ለመሆን ትልቁ መሳሪያ የህዝብ ብዛት ነው። ስንገነጣጠል ትልቁ የምናጣው በህዝብ ብዛታችን የምናገኘውን ጥቅም ነው።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ በህዝብ ብዛት 2ኛ መሆናችን እና የነፃነት ታሪካችን በሰጠን እድል ተጠቅመን ለአፍሪካ ሀገሮች በሰራነው ሥራ በአፍሪካ ተደማጭ ያደረጉን ሀብቶቻችን ናቸው። ከዚህ ላይ ኢኮኖሚ ሲጨመርበት ወደፊት የሚኖረን ተፅዕኖ ከፍተኛ ይሆናል።

ኢትዮጵያውያን መለያየት ለእድገታችን ለተሰሚነታችን ጠቃሚ ነው የሚሉ ሰዎች የፖለቲካ ድርቀት ያለባቸው ናቸው።

መለያየት አጀንዳ የሚያደርጉ ፖለቲከኞች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከዘላለማዊ ጠላታችን ከግብፅ ጋር የጥቅም ቁርኝት ያላቸው ናቸው። የመገንጠል ፖለቲካን የሚያራምዱ የሀገራቸውን የትውልዳቸውን መፃኢ ትልቅ የመሆን እጣፋንታ በጥቅም የሸጡ ናቸው።

  🇪🇹1️⃣ ኢትዮጵያ በአውሮፓ ኃይሎች ቅኝ ተገዝታ አታውቅም።2️⃣ ኢትዮጵያ ከአለም አንጋፋ ሀገራት አንዷ ስትሆን በሺህ የሚቆጠሩ አመታት ታሪክ ያላት ሀገር ነች።3️⃣ ኢትዮጵያ በዓይነቱ ል...
10/27/2025

🇪🇹

1️⃣ ኢትዮጵያ በአውሮፓ ኃይሎች ቅኝ ተገዝታ አታውቅም።

2️⃣ ኢትዮጵያ ከአለም አንጋፋ ሀገራት አንዷ ስትሆን በሺህ የሚቆጠሩ አመታት ታሪክ ያላት ሀገር ነች።

3️⃣ ኢትዮጵያ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ትጠቀማለች ይህም የኢትዮጵያ አቆጣጠር ከጎርጎሪያን አቆጣጠር ከሰባት እስከ ስምንት ዓመታት ገደማ ነው። 13 ወራት አሉት፣ እያንዳንዳቸው 12 ወራት ከ30 ቀናት እና 13ኛው ወር ከ5 ወይም ከ6 ቀናት።

4️⃣ ኢትዮጵያውያን የረቀቀ ሀገር በቀል ጥበብ ያላትና ለአለም ለዘመናዊ መድኃኒት ቅመማና ዘመናዊ ትምህርት አስተማሪ የሆነች የሰው ዘር መገኛ ናት።

5️⃣ በሀገሪቱ ከ85 በላይ ቋንቋዎች አሉ። ኦሮሞ፣ አማራ እና ትግራዋይ ከትልቅ ብሄር ብሄረሰቦች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

6️⃣ ኢትዮጵያዊው አበበ ቢቂላ በ1960 ኦሊምፒክ ወርቅ ያገኘ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ ነው።

7️⃣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር ዝቅተኛው ቦታ፣ የደናክል ዲፕሬሽን እንዲሁም በምድር ላይ በጣም ሞቃታማ የሆነው የኤርታሌ እሳተገሞራ ባለቤት ናት።

8️⃣ ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ የግእዝ ወይም የአማርኛ ፊደላት አላት፤ መነሻው ከጥንት ሴማዊ የአጻጻፍ ሥርዓት ነው።

9️⃣ ቡና በኢትዮጵያ ተገኘ ይባላል። ፍየሎቹን ያስተዋለ የካልዲ አፈ ታሪክ የቡና ፍሬዎችን ከበላ በኋላ የበለጠ ጉልበተኛ ሆኗል። አሁንም ቡና በሀገራችን በሰፊው ይታመረታል።

🔟 አዲስ አበባ የአፍሪካ ከፍተኛ ዋና ከተማ ነች። ከታላቁ ስምጥ ሸለቆ ጋር በሚያዋስኑ ደጋማ ቦታዎች ላይ የምትገኘው የአዲስ አበባ ዋና ከተማ ከባህር ጠለል በላይ 2,355 ሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች። ይህም ከአፍሪካ ከፍተኛው ነው ማለት ይቻላል። በደጀኔ ዝንቅ ሀሳቦች ገፅ ላይ የሚለቀቁ አስተማሪ ሃሳቦች በማንበብ ቤተሰብ ይሁኑ።



ከግድቡ ወደ ወደቡ⬆️

የአገልጋይ ሥነ ምግባራዊ አመራር 10 መሰረታዊ ባህሪያት🌿🌿🌿🌿🌿🌿1.ማዳመጥ፦በበሰራተኞችና በአመራሩ መካከል ያለ ተግባቦት መረጃዎች ማስተላለፍና መቀበል (መናገርና ማዳመጥ) የሚጨምር ነው፡፡ ...
10/27/2025

የአገልጋይ ሥነ ምግባራዊ አመራር 10 መሰረታዊ ባህሪያት
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

1.ማዳመጥ፦
በበሰራተኞችና በአመራሩ መካከል ያለ ተግባቦት መረጃዎች ማስተላለፍና መቀበል (መናገርና ማዳመጥ) የሚጨምር ነው፡፡

አገልጋይ አመራሮች የሚግባቡት መጀመሪያ በማዳመጥ ነው፡፡ ማዳመጥ የመማር ስነ-ስርዓት ሲሆን ማዳመጥንና ሌሎች የሚሉትን ተቀባይነት ያለው መሆኑን የሚቀበል ነው፡፡ በማዳመጥ ውስጥ አገልጋይ አመራሮች የተከታዮችን አቋም የሚቀበሉበትና እይታቸውን ዋጋ የሚሰጡበት ነው፡፡

2. የሌሎችን ስሜት መረዳት፦
ይህ ማለት አለምን በሌላ ሰው እይታ ሆኖ መመልከት ማለት ነው፡፡ ለሌሎች ስሜት ያላቸዉ አመራሮች በእውነት ተከታዮች ምን እንደሚያስቡና ምን እንደሚሰማቸው የተገነዘቡ ናቸው፡፡

አገልጋይ አመራር የሌሎችን ስሜት ሲረዳ ለተከታዮች ስሜታቸዉ ተቀባይነት እንዳገኘ ማረጋገጫ ይሆናል፡፡ ተከታዮች ልዩ እንደሆኑ እንዲሰማቸው ያደርጋል፡፡

3.ማዳን
በዚህ ዉስጥ ማዳን የሚለዉ ቃል የሚገልፀዉ ሙሉዕ ማድረግን ነው፡፡ አገልጋይ አመራሮች ለተከታዮቻቸው ደህንነት የሚያስቡና እንክብካቤ የሚያደርጉ ናቸው፡፡

የተከታዮች ግላዊ ችግሮች እንዲፈቱ በመርዳት ከጎናቸው መሆናቸውን ያረጋግጣሉ፡፡ በዚህ አባባል ውስጥ አመራሮች ተከታዮቻቸውን ሲደግፉ ከሰራተኞቻቸው ደግሞ ተመሳሳይ ድጋፍ ያገኛሉ፡፡ ይህ ደግሞ ባህሪን ሙሉዕ የማድረግ አስተዋጽኦው የላቀ ይሆናል፡፡

4.መገንዘብ
ሌላዉ የአገልጋይ ሥነምግባራዊ አመራር ልዩ መገለጫ የአከባቢያቸውን አካላዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሁኔታ በሚገባ መረዳት ነው፡፡

ይህ የሚጀምረው ራስን በመገንዘብ እና እኛነታችን በሌሎች ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽእኖ መረዳት ነው፡፡ አገልጋይ አመራሮች ወደታች ወረድ ብለው የራሳቸዉን እይታ ሰፊ ከሆነዉ አካባቢ ጋር ያዛምዱታል፡፡

5.ማሳመን
ማሳመን ግልጽና ዘላቂ የሆነ ተግባቦት ሲሆን ሌሎች እንዲቀየሩ የሚያደርግ ነው፡፡ የደረጃ ስልጣንን በመጠቀም ከመጨቆን በተቃራኒ ላላ ባሉ የማሳመን መንገዶች ለዉጥን እንዲፈጠር ማድረግ ነው፡፡

6. ጽንሰ ሃሳባዊነት እዉቀት
ጽንሰ ሃሳባዊ እዉቀት ማለት ለተቋማቸው ራዕይ የመቅረጽ፣ ግልጽ ግብና አቅጣጫዎችን የማቅረብ ችሎታን የሚገልጽ ነው፡፡ ይህ ባህሪ ከእለታዊ ተግባርን የመፈጸም አስተሳሰብ በመውጣት ትልቁ ስዕል ላይ ትኩረት ማድረግን ይመለከታል፡፡ ጽንሰ ሃሳባዊነት አገልጋይ አመራሮችን በማስታጠቅ ውስብስብ ተቋማዊ ችግሮችን በአዲስ መንገድ ለመፍታት፣ ከዘላቂ ግቦች ጋር በማያያዝ ዘርፈ ብዙ ተቋማዊ ግንኑነቶችን ለማጎልበት ይጠቅማል፡፡

7. አርቆ አስተዋይነት
አገልጋይ አመራሩ ወደፊት የማየት ችሎታን የሚገልጽ ነው፡፡ ቀደም ብሎ እና አሁን በተከሰተ ሁኔታ ላይ በመመስረት ወደፊት የሚመጣዉን የመተንበይ ችሎታ ነው፡፡

8. አደራ ጠባቂ
አደራ ጠባቂነት ማለት አመራር የመሆን ሃላፊነትን በአደራ የተቀበለ መሆኑን የተገነዘበ ነው፡፡ አገልጋይ አመራሮች ይህንን ሀላፊነት ተቀብለው በጥንቃቄ ሰዎችንና ተቋሙን በአግባቡ ይመራሉ፡፡ እንዲሁም ለአብዛኛው ጥቅም ሲሉ ተቋማቸው ታማኝነቱን ማረጋገጡን ይከታተላሉ፡፡

9. ለሰዎች እድገት ቁርጠኛ መሆን
የአገልጋይ አመራር ሌላው ትኩረት እያንዳንዱን ተከታይ ልዩ እንደሆነ የራሱ ውስጣዊ እሴቶች ያሉት፣ እና ለመስሪያ ቤቱ ስኬት አስተዋጽኦ እንዳለው በመገንዘብ በአግባቡ ማስተናገድ ነው፡፡

10. ማህበረሰብን መገንባት
አገልጋይ አመራር የማህበረሰብ ልማትን ያፋጥናል፡፡ ማህበረሰብ ማለት የጋራ ፍላጎት እና የአንድነት ስሜት ያላቸው ግለሰቦች ስብስብ ነው፡፡ ማህበረሰቦች ለራሳቸው ከሚሰጡት ዋጋ በላይ ትልቅ ለሆነ ተልእኮ መቆማቸውን እዲገነዘቡ ያደርጋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኤክስፖርት ተመራጭ አቦካዶ በኢትዮጵያ 🙏 በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኤክስፖርት ተመራጭ የሆነው የሀስ አቮካዶ ዝርያ፣ የችርቻሮ ዋጋው በኪሎ ግራም ከ4 እስከ 7 የአሜሪካ ዶላ...
10/27/2025

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኤክስፖርት ተመራጭ አቦካዶ በኢትዮጵያ 🙏

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኤክስፖርት ተመራጭ የሆነው የሀስ አቮካዶ ዝርያ፣ የችርቻሮ ዋጋው በኪሎ ግራም ከ4 እስከ 7 የአሜሪካ ዶላር ነው። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት አንድ ትልቅ የአቮካዶ ፍሬ እስከ አንድ የአሜሪካ ዶላር ድረስ ይሸጣል።

በዚህም የአቮካዶ ምርት በዓመት ከ18 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚንቀሳቀስበት ሰፊ የገበያ ፍላጎት ያለው ምርት ሆኗል።

በተለይ ካለፉት አስር ዓመታት ጀምሮ የዚህ ምርት ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎም እንደ ሜክሲኮ ላሉ የዓለማችን ቀዳሚ አምራች ሀገራት የአቮካዶ ምርት ሁነኛ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።

በዓመት ከ1.28 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ የሚሆን የአቮካዶ ምርት ወደ ውጭ የምትልከው ሜክሲኮ፣ እ.አ.አ. በ 2024 ዓ.ም ከ3.7 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ችላለች።

በኢትዮጵያም በተለይ ባለፉት 4 ዓመታት ይህን ምርት በስፋት ለማምረት ታቅዶ አመርቂ ውጤት የተገኘበት ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ብቻ ይውል የነበረውን የአቮካዶ ምርት ወደ ውጭ በመላክ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ማግኛ እየሆነ ነው።

ሆኖም ኢትዮጵያ ካላት አቅም አንጻር ከምርቱ ማግኘት ያለባትን ጥቅም ሳታገኝ በመቆየቷ፣ በቀጣይ 15 ዓመታት ሀገሪቱን የዓለማችን ቀዳሚ የአቮካዶ አምራችና ላኪ ሀገር ለማድረግ የሚያስችል ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ይፋ ተደርጓል።

በዚሁ መሠረት 38.5 ቢሊዮን ብር በጀት በመመደብ ወደ ሥራ መገባቱም ተገልጿል።

ፕሮግራሙ ምርቱን አሁን ካለበት 100 ሺህ ሄክታር ወደ 191 ሺህ ሄክታር ለማድረስ፣ አጠቃላይ ምርቱንም ከ400 ሺህ ቶን ወደ 3.8 ሚሊዮን ቶን ከፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ታውቋል።

3 ሚሊዮን ባለአነስተኛ ይዞታ አርሶ አደሮች ከፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ተመላክቷል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት የአቮካዶ ምርት ለምግብነት እና ለውበት መጠበቂያ ምርቶች መሥሪያ እንደ ዋንኛ ግብዓት ያገለግል የነበረ ሲሆን፣ አሁን ላይ ደግሞ ትላልቅ የአግሮ ፕሮሰሲንግ እና የመድኃኒት ፋብሪካዎች በግብዓትነት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ።

10/27/2025
ጥቅምት 17 ቀን 1904 ዓ.ም ከ 113 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ሀገራችን በወረረበት ወቅት በመዝመት ለፈፀሙት ታላቅ ገድል ታሪክ በወርቃማ ድል የሚያወሳቸው ጀግና...
10/27/2025

ጥቅምት 17 ቀን 1904 ዓ.ም



ከ 113 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ሀገራችን በወረረበት ወቅት በመዝመት ለፈፀሙት ታላቅ ገድል ታሪክ በወርቃማ ድል የሚያወሳቸው ጀግናዋ የሴት አርበኛ እመቤት ሆይ ከበደች ስዩም ከአባታቸው ልዑል ራስ ስዩም መንገሻ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ጀምበር በርሄ በትግራይ ጠቅላይ ግዛት በእንደርታ አውራጃ መቀሌ ከተማ ውስጥ የተወለዱበት ዕለት ነበር፡፡

***********
ኢትዮ-ጣሊያናዊቷ ዘፋኝ ፣ ጸሐፊና ገጣሚ ጋብርኤላ ጌርማንዲ ስለታላቋ አርበኛ ክብርት ወ/ሮ ከበደች ስዩም የሚከተለውን ጽፋለች:-



***********
‹‹ አገራችን በጠላት ተይዛ ፣ ወገናችን በባርነት ቀንበር ተጠምዶ… ከጠላት ጋር መታረቅ አልችልም...!›› ጀግኒቷ አርበኛ ከበደች ሥዩም ፤ 1904 -- 1971

1) በማያገባህና አንተን በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ፣ የራስህን ኑሮ በደንብ አድርገህ እወቅና በጥበብ ኑር፣ 2) በማህበራዊ ሚዲያ ለምታየው ማንኛውም ልጥፍ ርዕሱን ብቻ አይተህ ቀድመህ መልስ...
10/27/2025

1) በማያገባህና አንተን በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ፣ የራስህን ኑሮ በደንብ አድርገህ እወቅና በጥበብ ኑር፣

2) በማህበራዊ ሚዲያ ለምታየው ማንኛውም ልጥፍ ርዕሱን ብቻ አይተህ ቀድመህ መልስ አትስጥ፣ አትፍረድ፣ አትፈርጅ። አስተያየት መስጠት ካለብህ በደንብ ካየህ በኋላ ስጥ። ያለበለዚያ ግልብ፣ ተናዳጅ፣ ፈራጅ፣ እና ምንም ግንዛቤ የሌለው ደደብ ሰው ተደርገህ እንድትሳል ያደርግሃል።

3) ስለ ምንም ነገር ይሁን ለመማር ዝግጁ ሁን፣ የሰውን ሀሳብ እንደየሁኔታው ለመቀበል፣ ወይም በልዩነት ለመስማማት ብልህነትን ተማር። የአንተ አላዋቂነት ድፍረት ለልጅህም እንደሚተላለፍ እወቅ። (ይህን ወደፊት በስፋት እነግርሃለሁ)

4) አንዳንድ ሰዎች በየትኛውም ነገር ላይ አውቃለሁ የሚሉ ናቸውና ራቃቸው። ከእንደዚህ አይነት ሰዎች ጋር አትከራከር ምክንያቱም ብዙ ደጋፊዎች አሏቸው።

5) ሰዎች ሁለት አይነት ማይንድሴት (ሥሪተ አዕምሮ) ያላቸው እንደሆኑ ተገንዘብ። አንደኞቹ አዳጊ አዕምሮ፣ ሌሎቹ ደግሞ ውስን(የተገደበ)። የውስን አዕምሮ ባለቤቶችን በጥበብና በሥልጠና ካልሆነ አትቀይራቸውምና ከነርሱ ጋር ስለ ለውጥ አትከራከር።

6) ራስህን ለውጥ፣ በገንዘብ፣ በሥራ፣ በአካባቢ እና በጓደኛ የተሻልክ ሁን። ለመለወጥ እንቅፋት የሆኑብህን ነገሮች ቀድመህ ለውጥ።

7) ልጅ በአጋጣሚ አትውለድ፣ ከወለድክም ብቸኛው ኃላፊነት ያለብህ አንተ (ወላጁ) ብቻ እንደሆንክ እመን። ትውልድን በተመለከተ አስተያየት ከመስጠትህ በፊት ከራስህ ልጅ ጀምር።

8) አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች በቡድን ሲሆኑ መጥፎዎች፣ በግለሰብ ደረጃ ደግሞ ጥሩዎች የመሆን እድላቸው ሰፊ ነው። ሰዎችን በግለሰብ ደረጃ ተመልከት።

9) የራስህን ኑሮ በእርጋታ ለመኖር ከሚጠቅሙህ ነገሮች አንዱ ግላዊ መሆን ነው። ለዚህም በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ግል ሚስጥርህ፣ ስለምታደርገው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ እየወጣህ አትለጥፍ፣ አትዘርዝር። አንዴ እንደዚያ ካደረግህ በኋላ መመለሻው ከባድ ነውና ተጠንቀቅ።

10) በልጅነትህ የደረሰብህ ቀውስ በማንኛውም መልኩ አሁን ላለህበት ሕይወት ወሳኝ ነውና ልጅህ ላይ ሌላ ቀውስ ከመፍጠርህ በፊት እሱን ችግር ለመፍታት ሞክር። በጊዜው ያልተፈታ ቀውስ ኋላ ላይ በአስቀያሚ ሁኔታ ይወጣልና።

በተጨማሪም ማህበረሰብ ከቤተሰብ እንደሚመሰረት፣ ሰዎች ደግሞ የቤተሰብ ውጤት መሆናቸውን አውቀህ ቤተሰብህ ላይ ሥራ።

ስለሰብአዊ መብቶች በጠቅላላየሰብአዊ መብቶች ጅማሮ ከጥንታዊ የግሪክ ፍልስፍና እና ከኃይማኖቶች አስተምህሮ እንደሆነ ፅሑፎች ያወሳሉ፡፡ ከ6ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ የተለያየ ይዘት ያላቸው የሰብአዊ...
10/27/2025

ስለሰብአዊ መብቶች በጠቅላላ

የሰብአዊ መብቶች ጅማሮ ከጥንታዊ የግሪክ ፍልስፍና እና ከኃይማኖቶች አስተምህሮ እንደሆነ ፅሑፎች ያወሳሉ፡፡ ከ6ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ የተለያየ ይዘት ያላቸው የሰብአዊ መብቶች ሰነዶች የነበሩ ቢሆንም የሰብአዊ መብት እንደ አንድ አጀንዳ (ጉዳይ) እራሱን ችሎ መቆም የቻለው ግን ከ18ኛው ክ/ዘመን (በዘመነ አብርሆት) ጀምሮ ነው፡፡ በአውሮፓ የአናሳ መብቶች ለመጠበቅ በሚደረግ ጥረት በሀገራት መካከል ተከታታይ ግጭቶች ይደረጉ ነበር፡፡ በእነዚህ ግጭቶች ምክንያት የዓለማቀፍ ጣልቃ ገብነት እንዲኖርና አለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ስርዓት እንዲዘረጋ አስገድዷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሑፍ ሰብአዊ መብቶችን የተመለከቱ ጠቅላላ ፅንሰ ሀሳቦች ማለትም ስለሰብአዊ መብቶች ምንነት፣ መገለጫ ባሕሪያት እንዲሁም ሰብአዊ መብቶችን ከማስከበር አኳያ የመንግስታት ኃላፊነት ምን እንደሚመስል እንዳስሳለን፡፡

የሰብአዊ መብቶች ምንነት
መብት የሚለውን ቃል የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማእከል ባሳተመው የአማርኛ መዝገባ ቃለት “አንድ ሰው አስፈላጊ ሆኖ ሲያየው ሊያገኘው የሚገባ ነገር፣ አገልግሎት፣ ጥቅም…” በማለት ተርጉሞታል፡፡ የሰብአዊ መብቶችም የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ምክንያት ያገኛቸው ጥቅሞች ናቸው ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ “ሰብአዊ መብት” የሚለው ሐረግ አንድን መብት ብቻ የሚመለከት ሳይሆን ከሕይወት የመኖር መብት ጀምሮ እስከ የባሕል መብት ድረስ ያሉትን በርካታ የመብት ዓይነቶችን አጠቃሎ የሚይዝ ጥቅል መጠሪያ ነው፡፡

የሰብአዊ መብት መለያ ባህሪያት፡-
ሰብአዊ መብቶች በርካታ መለያ ባህሪያት ያሏቸው ሲሆን ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
 ፈጥሮአዊነት (Inherent)፡- ሰብአዊ መብቶች በማንኛውም የመንግስት አካል ወይም በማንኛውም ሰው የሚሰጡ ሳይሆን የሰው ልጅ በተፈጥሮ የሚያገኛቸው በመሆኑ ተፈጠሮአዊ ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች የሚገኙት በስጦታ፣ በግዢ ወይም በውርስ ሳይሆን የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ ካለው ክብር እና ዋጋ የተነሳ ነው፡፡
 ሁሉን አቀፋዊነት (universality)፡- ሰብዓዊ መብቶች በመላው አለም ለሚገኙ ሰብዓዊ ፍጡራን ተመሳሳይ ክብርና እውቅና የሚሰጡ መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች ለሁሉም የዓለም ህዝቦች በሙሉ የተከበሩ እና እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን በማንኛውም መሰረት ልዩነት ሊደረግባቸዉ የማይችል የሰው ልጆች በሙሉ ሰው በመሆናቸው ሊጠቀሙባቸዉ የሚችሉ መብቶች ናቸዉ፡፡ ስለሆነም ሰብዓዊ መብቶች በዘር፣ በቀለም፣ በሀይማኖት፣ በፆታ፣ በልደት፣ በሀብት ደረጃ ወይም በሌላ ልዩነት ሳይደረግ መከበር አለባቸዉ፡፡
 የማይገፈፉ ወይም የማይገረሰሱ ናቸው (inalienable)፡- ሰብአዊ መብቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ጋር የተቆራኙ በመሆናቸው ከማንም ሰው ላይ ሊገፈፉ ወይም ሊገረሰሱ አይችሉም፡፡ ማንም ሰው የማንንም ሰው ሰብአዊ መብት ሊነጥቅ ካለመቻሉም በላይ ሰዎች እነዚህን መብቶችን አሳልፈው ሊሰጡም አይችሉም፡፡
 የማይነጣጠሉና ተደጋጋፊ ናቸው (indivisible and interdependent)፡- ሰብአዊ መብቶች እርስ በእርስ የተደጋገፉ እና የተያያዙ በመሆናቸው በሰብአዊ መብቶች ውስጥ ተዘርዝረው የሚገኙ ሁሉም መብቶች በአንድነት መከበር እና እውቅና ማግኘት አለባቸው፡፡ እነዚህን መብቶች ነጣጥሎ ማክበር ወይም እውቅና መስጠት አይቻልም፡፡ ሰዎች ሙሉ ሆነው ይኖሩ ዘንድ ሁሉም ሰብአዊ መብቶች ያለምንም መነጣጠል እና መሸራረፍ ሊከበሩላቸው ይገባል፡፡ ምክንያቱም የአንደኛው መብት መጣስ የሌላኛውንም መብት መጣስ ይዞ ስለሚመጣ እና ይህ መጣስ ከሰብአዊነት ክብር ዝቅ ያለ ኑሮን ስለሚያስከትል ነው፡፡ እንዲሁም ለአንዱ መብት መሟላት የሌላኛው መብት መከበር ወይም መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው፡፡
 መሰረታዊነት (Fundamental)፡- የሰብአዊ መብቶች መሰረታዊ በመሆናቸው የእነዚህ መብቶች አለመከበር የሰው ልጆች ክብርና ሕይዎት ትርጉም አልባ ይሆናል፡፡ ሰብአዊ መብቶች ተራ ፍላጎቶችና ምኞቶች ሳይሆኑ የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በክብር ይኖር ዘንድ ወሳኝ ናቸው፡፡
ሰብአዊ መብቶችን ከማክበር አንፃር የመንግስታት ኃላፊነት፡-
ሀገራት ለሰብዓዊ መብቶች ተፈፃሚነት ከፍተኛ ሚና እና ኃላፊነት ያለባቸው ሲሆን ኃላፊነታቸውን ወይም ያለባቸውን ግዴታ በአጠቃላይ በሶስት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡እነዚህም፡-
ሰብዓዊ መብቶችን የማክበር ግዴታ (obligation to respect)፡- በሰብዓዊ መብቶች ተጠቃሚነት ጣልቃ ከመግባት መቆጠብ አለባቸው፡፡ (refrain from interfering with the enjoyment of the right)
ሰብዓዊ መብቶችን የመጠበቅ ወይም የማስከበር ግዴታ (obligation to protect)፡- ሌሎች ሰዎች በሰዎች የሰብዓዊ መብት ተጠቃሚነት ጣልቃ እንዳይገቡ የመጠበቅ ወይም የመከላከል ግዴታ (prevent others from interfering with the enjoyment of the right)
ሰብዓዊ መብቶችን የማሟላት (obligation to fulfill)፡- የኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ባህላዊ መብቶችን ተፈፃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ እርምጃዎችን የመውሰድ ግዴታ አለባቸው፡፡ (adopt appropriate measures towards the full realization of economic, social and cultural rights)

ማጠቃለያ
ሰብአዊ መብቶች የሰው ልጆች ሰው በመሆናቸው ብቻ ያገኟቸው መብቶች እንደመሆናቸው ሳይሸራረፉ ሊከበሩ የግድ ነው፡፡ በመሆኑም ለመብቶቹ መከበር መንግስትም ያለበትን የማክበር እና የማስከበር ሀላፊነት ሊወጣ እንዲሁም ሁሉም ዜጋ የበኩሉን አስተዋፅኦ ሊያበረክት ይገባል፡፡

በፍትህ ሚኒስቴር በንቃተ ሕግ ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

ስለ ፖሊስ አባላት ማዕረግና ስለመጠሪያ ስሞቻቸዉ ስንቶቻችን እናዉቃለን ?
10/27/2025

ስለ ፖሊስ አባላት ማዕረግና ስለመጠሪያ ስሞቻቸዉ ስንቶቻችን እናዉቃለን ?

2ለ2 በተጠናቀቀ ጨዋታ 4 ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች!አንዳንድ የእግር ኳስ ታሪኮች፣ ሪከርዶችና አስገራሚ ገጠመኞች የሚደገሙ አይደሉም። ይህ በእግር ኳስ የዘመናት ታሪክ በልዩ ሁኔታ የሚታወስ አ...
10/27/2025

2ለ2 በተጠናቀቀ ጨዋታ 4 ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች!

አንዳንድ የእግር ኳስ ታሪኮች፣ ሪከርዶችና አስገራሚ ገጠመኞች የሚደገሙ አይደሉም። ይህ በእግር ኳስ የዘመናት ታሪክ በልዩ ሁኔታ የሚታወስ አጋጣሚም ወደፊትም ይደገማል ተብሎ የሚጠበቅ አይነት አይደለም።

በእግር ኳስ ታሪኮች ውስጥ ተጫዋቾች በራሳቸው መረብ ላይ ግብ ማስቆጠር ያለ የነበረና ወደፊትም የሚኖር ክስተት ነው። በርካታ ተጫዋቾች በራሳቸው መረብ ላይ ግብ አስቆጥረው ቡድናቸውን ዋጋ የሚያስከፍሉትን ያህል በራሳቸው ግብ ያስቆጠሩት ኳስ እልህ አስይዟቸው በተቃራኒ ቡድን መረብ ላይ በማስቆጠር የሚያካክሱም ተጫዋቾች ብዙ ናቸው።

ክሪስ ኒኮላስ ግን ከእንደዚህ አይነት ተጫዋቾች ትንሽ ለየት ያለ ታሪክ አለው። ይህ አንጋፋ ተጫዋች 2ለ2 በተጠናቀቀ ጨዋታ ላይ አራቱንም ግቦች በማስቆጠር የማይረሳ ታሪክ አለው። ጊዜው መጋቢት 1976 ነው፣ ጨዋታው ደግሞ አስቶን ቪላ ከሌስተር ሲቲ።

የቪላ ፓርኩ ተጫዋች ክሪስ ኒኮላስ ይህን ጨዋታ የጀመረው በራሱ መረብ ላይ ግብ በማስቆጠር ነበር። ብዙም ሳይቆይ ግን የአቻነቷን ግብ በተቃራኒ ቡድን መረብ ላይ በማሳረፍ የሰራውን ስህተት አካካሰ። ኒኮላስ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሮ የሰራውን ስህተት በተቃራኒ ቡድን ላይ በማስቆጠር እፎይ ከማለቱ ግን ደስታው ብዙ አልቆየም።

ዳግም በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሮ በራሱ እግር አቻ ያደረገውን ቡድን ራሱ ወደ ተመሪነት መለሰው። በዚህ ግን አልተደናገጠም ዳግም በተመሳሳይ መንገድ ክለቡን ወደ አቻነት መልሶ ለመካስ ጥረቱን ቀጠለ። በመጨረሻም ጥረቱ መና አልቀረም በተቃራኒ ቡድን ላይ ኳስና መረብ አገናኝቶ ቡድኑን ከሽንፈት መታደግ ቻለ።

ኒኮላስ 2 አቻ በተጠናቀቀው ጨዋታው ሁሉንም ግቦች በስሙ ካስመዘገበ በኋላ ያደረገው ነገርም ሜዳ ላይ ከፈፀመው በበለጠ አስገራሚ ነበር። በጨዋታው ሐትሪክ ሰርቻለሁ ብሎ ዳኛው ኳሱን እንዲሰጡት ጠይቋል።

"ዳኛው ኳሱን ይሰጡኝ እንደሁ ብዬ ጠይቄ ነበር፣ ግን አይሆንም አሉኝ፣ ይህ የመጨረሻ ጨዋታዬ ነበርና ኳሱን ብወስድ ደስተኛ ነበርኩ፣ ግን እድሌ ነው መሰለኝ አልተሳካልኝም፣ በአስቶን ቪላ ማለያ የመጀመሪያ ሐትሪኬን ነበር የሰራሁት፣ ነገር ግን ኳሱን መውሰድ አልቻልኩም" በማለት ኒኮላስ ስለነበረው ሁኔታ ያስታውሳል።😅

የባህር በር የሌላቸዉና እና ወደብ አልባ የሆኑ የአለም ሀገራት ዝርዝር!1 አፍጋኒስታን2 አንዶራ3 አርመንያ4 ኦስትሪያ5 አዘርባጃን6 ቤላረስ7 ቡታን8 ቦሊቪያ 9 ቦትስዋና10 ቡርኪናፋሶ11 ብ...
10/26/2025

የባህር በር የሌላቸዉና እና ወደብ አልባ የሆኑ የአለም ሀገራት ዝርዝር!

1 አፍጋኒስታን
2 አንዶራ
3 አርመንያ
4 ኦስትሪያ
5 አዘርባጃን
6 ቤላረስ
7 ቡታን
8 ቦሊቪያ
9 ቦትስዋና
10 ቡርኪናፋሶ
11 ብሩንዲ
12 ሴንትራል አፍሪካ ሪፓብሊክ
13 ቻጅ
14 ቼክ ሪፓብሊክ
15 #ኢትዮጵያ
16 ሃንጋሪ
17 ካዛኪስታን
18 ኪርጊስታን
19 ላኦስ
20 ሌሴቶ
21 ሊተንሽንይን
22 ሉክሱምበርግ
23 ማሶዴንያ
24 ማላዊ
25 ማሊ
26 ሞልዶቫ
27 ሞንጎልያ
28 ኔፓል
29 ኒጀር
30 ፓራጓይ
31 ሩዋንዳ
32 ሳንማሪኖ
33 ሰርቢያ
34 ስሎቫኪያ
35 ስዊዚላንድ
36 ታጂኪስታን
37 ኡጋንዳ
38 ኡዝቬኪስን
39 ቫቲካን ሲቲ
40 ዋስት ባንክ/ፊልስጢየም
41 ዛምቢያ
42 ዚምባቢዌ
43 ቱርከሚስታን
44 በመጨረሻም ደቡብ ሱዳን

ከነዚህ ወደብ አልባ ሀገሮች መካከል እጅግ የሚለየዉ የኢትዮጵያ ጉዳይ ነዉ:: 1ኛ ባህር በር የሌላቸዉ ወይም ወደብ አልባ ከሆኑ ሀገሮች መካከል ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር የያዘች ሀገር መሆኗ
2ኛ ከባህር በር በጣም አጭር ኪሎ ሜትር ማለትም ከባህር በ65 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆና ወደብ አልባ ሀገር መቆየቷ አግራሞትን ይፈጥራል::

Address

Los Angeles, CA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Rising posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share